#update የኢትዮጵያ አየር መንገድ በረራ ቁጥር 302 ቦይንግ 737 ማክስ አውሮፕላን አደጋ #ምርመራ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት #በቅርቡ እንደሚለቀቅ የውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃል አቀባይ #ነቢያት_ጌታቸው ለሮይተርስ ተናግረዋል፡፡ ሪፖርቱን ይፋ የሚያደርገው ትራንስፖርት ሚንስቴር ነው፡፡ ውጤቱ ለአውሮፕላኑ የተገጠመለት (MCAS) ሶፍትዌር #ከካፒቴኑ ቁጥጥር ውጭ አውሮፕላኑ አፍንጫውን ቁልቁል ዘቅዝቆ እንዲከሰከስ እንዳደረገው እንደሚገልጽ ይጠበቃል፡፡ #ቦይንግ ኩባንያ ሶፍትዌሩን አሻሽያለሁ ብሏል፤ በሚዲያ ዘመቻ ራሱን ለመከላከል እየሞከረ ነው፡፡

Via ሮይተርስ(በዋዜማ)
@tsegabwolde @tikvahethiopia