TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት⬇️

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ከጥሪ እና በዓላት ጋር ተያይዞ የትራንስፖርት ችግር እንዳይገጥማቸው ዝግጅት ማድረጉን ትምህርት ሚንስቴር አስታወቀ።

እንደሚታወቀው አዲሱን የትምህርት ዘመን ተከትሎ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል ያሉ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት #ለነባር እና #አዳዲስ ተማሪዎች ጥሪ የሚያቀርቡበት ነው።

ይህንንም ተከትሎ በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ያሉ አዲስ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን የሚቀላቀሉት እና ነባር ተማሪዎች ወደ ተመደቡባቸው ዩኒቨርስቲዎች የሚጓዙ ሲሆን በዚህ ወቅትም ተማሪዎች ለከፍተኛ የትራንስፖርት ችግር ይዳረጋሉ።

ችግሩንም ለመቅረፍም የዩኒቨርስቲዎቹን የጥሪ ጊዜ እና ዩኒቨርስቲዎቹ የሚገኙባቸው አከባቢያዊ በዓላትን ያገናዘበ ስርዓት በትምህርት ሚንስቴር እና በትራንስፖርት ባለስልጣን በመዘርጋቱ ከአምና ጀምሮ ችግሩን መፍታት ማቻሉን ተገልጿል።

በዚህ ዓመትም ይህንን ያገናዘበ አሰራር እንደሚተገበር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት መደረጉን በትምህርት ሚንስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚንስትር ዲኤታ ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ አስታውቀዋል።

በዚህም መሰረት ዩኒቨርስቲዎቹ ተማሪዎቻቸውን የሚጠሩበት ወቅት የተለያየ እንዲሆን እና ጥሪውም በዚህ ወቅት ላይ የሚከበሩ በተለይ ደግሞ ዩኒቨርስቲዎቹ የሚጠሩበት ወቅት በዛው አከባቢ በስፋት ከሚከበሩ ሃይማኖታዊ እና ባህላዊ በአላት ጋር እንዳይጋጩ
ተደርጓል።

እንዲሁም በትራንስፖርት እጥረት ምክንያት ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርስቲዎቻቸው ገብተው አስፈላጊውን ዝግጅቶች በማድረግ ትምህርት የሚጀምሩበትን ጊዜ እንዳይዘገይ ለማድረግ፤ የአጭር ርቀት ጉዞ ብቻ የተፈቀደላቸው ተሽከርካሪዎች በጊዜያዊነት የረጀም ጉዞ እንዲፈቀድላቸው ተደርጓል፡፡

በተጨማሪም ከዚህ ቀደም የነበረው የኪሎ ሜትር ገደብ መነሳቱንም በትራንስፖርት ባለስልጣን የየብስ ትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥ ማረጋገጫ ዳይሬክተር አቶ ተስፋየ በላቸው ተናግረውል።

ምንጭ፦ ፋና
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዳዲስ ክልሎች‼️

የጋና የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ስድስት #አዳዲስ ክልሎችን ለመፍጠር የምርጫ ድምጽ እያሰጠ ነው፡፡ ጋናውያን በምዕራብ አፍሪካ ሀገራት ስድስት አዳዲስ ክልሎችን ለመፍጠር በተደረገው ሕዝበ ውሳኔ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍሎች ድምጽ ይሰጣሉ፡፡ የምርጫ ኮሚሽኑ ከትላንት በስቲያ የድምፅ መስጫ መሳሪያዎችን በተገቢው ቀጠናዎች ላይ ያሰማራ ሲሆን ድምጽ የመስጠት ውሳኔው ትላንት ተከናውኗል፡፡

ምንጭ፦አፍሪካ ኒውስ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ የተሰጠው ሙሉ መግለጫ፦

"በ10ኛው የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባኤ ትኩረት ተሰጥቶ እንዲሰራ አቅጣጫ ከተቀመጠላቸው ጉዳዮች አንዱ #አዳዲስ_ክልል ሆኖ #የመደራጀት ጥያቄ ነው፡፡ ስለሆነም ይህ ጥያቄ በክልላችን አሁን ያለበት ደረጃና በጉባኤው በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት እየተፈፀመ ስለመሆኑ በዝርዝር ተገምግሟል፡፡ ዘላቂ መፍትሄውን በተመለከተ፤ በሰከነ እና ሃላፊነት በተሞላ መንገድ ማየት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ማእከላዊ ኮሚቴው ትኩረት ሰጥቶ ተወያይቶበታል፡፡ በመሆኑም በክልላችን እየተነሱ ያሉ ክልል ሆኖ የመደራጀት ጥያቄዎች የህዝቦችን ትስስርና አንድነት በሚያጠናክር፣ የድርጅት ቀጣይነትና የሁሉንም ህዝቦች ተጠቃሚነት በሚያረጋግጥ አኳኋን በደኢህዴን መሪነት እንዲፈፀም ልዩ ትኩረት ሰጥተን እንሰራለን፡፡"

https://telegra.ph/ከደኢህዴን-ማዕከላዊ-ኮሚቴ-የተሰጠው-ሙሉ-መግለጫ-02-26
" ከተፈታኝ መምህራኑ 49 በመቶ የሚሆኑት ከ50% በታች ዉጤት በማስመዝገባቸው ወደ ማስተማር እንዳይገቡ ተደርጓል " - የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ

የቤንች ሸኮ ዞን ትምህርት መምሪያ በዞኑ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመምህራን የመግቢያ ፈተና መስጠቱ ተሰምቷል።

ለመጀመርያ ጊዜ በዞኑ ትምርት መምሪያ ተዘጋጅቶ በተሰጠዉ የመግቢያ ፈተና ከአጠቃላይ ተፈታኞች 51 በመቶ ተፈታኞች ብቻ ናቸው 50% እና በላይ በማምጣት ያለፉት።

ከተፈታኝ መምህራኑ 49 በመቶ የሚሆኑት ከ50% በታች ዉጤት በማስመዝገባቸው ወደ ማስተማር ስራ እንዳይገቡ መደረጉንም መምሪያው አስታውቋል፡፡

ወደ ማስተማር አይገቡም የተባሉት ተፈትነው ከ50% በታች ያመጡ መምራን በቀጣይ ዕጣ ፋንታቸው ምንእንደሆነ በግልፅ አልተነገረም።

ፈተናውን ማለፍ ባልቻሉ መምህራን ክፍተት እንዳይፈጠር #አዳዲስ_መምህራን እየተመዘኑ እንዲቀጠሩ ይደረጋል ተብሏል፡፡

የዞኑ ትምህርት መምርያ በመምህርነት የተመረቁትን ለመጀመርያ ጊዜ የመግቢያ ፈተናን በመፈተን ወደ መማር ማስተማሩ ስራ እንዲገቡ መደረጉንና ይህ አሰራር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብሏል።

የተማሪ ዉጤትና ስነ ምግባርን ለማሻሻል ከሚሰሩ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መካከል የሰው ሀይል ልማትና ብቃት ወሳኝ በመሆኑ በቀጣይነት አዲስ የሚቀጠሩ መምህራን ለሚያስተምሩት የትምህርት እርከን የሚመጥንና ከመማር ማስተማሩ ጋር ተያያዠነት ያለዉ የመግቢያ ፈተና እየተሰጠ ብቁ የሰዉ ሀይል የትምህርት ዘርፉን እንዲቀላቀል በትኩረት ይሰራል ብሏል።

ምንም እንኳ ስራዉ ዘንድሮ የተጀመረ ቢሆንም በቀጣይነት የተቋሙ አሰራር ሁኖ እንዲፈፀም በትምህርት መምርያዉ ማኔጅመት ተወስኖ ወደ ስራ መገባቱን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚዛና ፋና ኤፍ ኤም / ከቤንች ሸኮ ዞን ኮሚኒኬሽን ያገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#FDREDefenseForce

የኢትዮጵያ ጦር ኃይሎች ምክትል ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጄኔራል አበባው ታደሠ ምን አሉ ?

" ለኢትዮጵያ ዕድገት እንቅፋት ለመፍጠር የሚጥሩ በአካባቢያችን ያሉ #ታሪካዊ_ጠላቶቻችን እና #አዳዲስ_ኃይሎች እየተሰባሰቡ እንዳለ እያየን ነው።

እነኝህ ጠላቶች ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉ በቅርበት እየተከታተልን እንገኛለን።

ሀገራችን ኢትዮጵያ የማንንም ሃገር ብሔራዊ ጥቅም መንካት ተገቢ አለመሆኑን በማመን በዘመኗ የሌላ ሀገር ብሔራዊ ጥቅም ነክታ አታውቅም አሁንም አትነካም ታሪኳም አይደለም።

የሌላን ሀገር ብሔራዊ ጥቅም እንደማንነካው ሁሉ እኛም የሃገራችንን ብሔራዊ ጥቅም አሳልፈን አንሰጥም።

ለሃገራችን ሁለንተናዊ ብሔራዊ ጥቅም እንደወትሮው ሁሉ ዛሬም ዘብ እንቆማለን። "

ጄነራሉ ይህን የተናገሩት " አዋሽ አርባ " የሚገኘውን የኢትዮጵያ ሀገር መከላከያ ሜካናይዝድ ጦርን እና እየወሰደ ያለውን ስልጠና ከጎበኙ በኃላ ነው።

ሰልጣኞቹ በስነ-ልቦና ዝግጁነት ብቁ በመሆን ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ጥቅም እና ክብር መረጋገጥ ሲባል የሚወስዱትን ሙያዊ ስልጠና በፍጥነት ማጠናቀቅና ለሚሰጣቸው #ማንኛውም_ግዳጅ ዝግጁ መሆን እንዳለባቸው #አፅንኦት ሰጥተዋል።

#FDREDefenseForce

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በኢራን የሂሊኮፕተር አደጋ የሞቱት እነማን ናችው ? - የኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ - የኢራን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆሴን አሚር አብዶላሂያን - የተብሪዝ መስጂድ ኢማም አያቶላህ አልሃሸሚ - የምስራቅ አዘርባጃን ግዛት አስተዳዳሪ ማሊክ ራህማቲ - የፕሬዝዳንቱ ጥበቃ ኃላፊ ማሄዲ ሙሳቪ - የሄሊኮፕተሩ አብራሪ፣ - የሂሌኮፕተሩ ረዳት አብራሪ - ቦዲጋርድ - የበረራ አስተናጋጅ በትላንቱ የሂሊኮፕተር…
#ኢራን

" ...አሜሪካ በአቪየሽን ዘርፍ ላይ የጣለችው ማዕቀብ ለአደጋው መንስዔ ነው " - ሙሐመድ ጃቫር ዛሪፍ

የኢራን የቀድሞው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሙሃመድ ጃቫር ዛሪፍ ፣ የኢራን ፕሬዝዳንት እና ሌሎች ከፍተኛ የኢራን ባለስልጣናት ላይ ለደረሰው የሄሊኮፕተር አደጋ አሜሪካን ተጠያቂ አድርገዋል።

ሙሃመድ ጃቫር ዛሪፍ ፣ " #አሜሪካ በአቪየሽን ዘርፍ የጣለችው ማዕቀብ ለአደጋው መንስዔ ነው " ብለዋል፡፡

ከኢራን ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጋር ቆይታ ደረጉት ዛሪፍ ፣ " ማዕቀቡ ኢራን #አዳዲስ የአቪየሽን ምርቶችን መግዛት እንዳትችል አድርጓታል " ሲሉ ተናግረዋል፡፡

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ጥሩ የሚባል ግንኙነት እንደሌላት ይታወቃል።

ትላንት የኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ እና ሌሎች ባለልስጣናት ግድቦችን መርቀው ከከፈቱ በኋላ ወደ ታብሪዝ እያመሩ ሳሉ የነበሩበት ሂሊኮፕተር ከተራራ ጋር ተጋጭቶ ሁሉም ህይወታቸው አልፏል።

አደጋው በደረሰበት አካባቢ ላይ እጅግ አስቸጋሪ የአየር ሁኔታ እንደነበርም ተገልጿል።

More ➡️ @thiqaheth