TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ከየካቲት 7 እስከ 13 #በጅግጅጋ ከተማ በሚካሄደው ሀገር አቀፍ የከተሞች ፎረም አስመራ፣ ጅቡቲ፣ ሀርጌሳ እና ሞቃዲሾ መጋበዛቸውን የከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ከተሞቹ የተጋበዙት ከጎረቤት ሀገራት ጋር የበለጠ ግንኙነት ለመፍጠር በኢትዮጵያ በተያዘው ስትራቴጂ መሰረተ የተከናወነ መሆኑም ተገልጿል፡፡

Via EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጅግጅጋ🔝 በትላንትናው ዕለት የጥምቀት በዓል #በጅግጅጋ ከተማ በሰላም ተከብሯል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
መልካም ተግባር🔝

#የአገር_መከላከያ_ሰራዊት አባላት እና የሶማሌ ክልል #ልዩ_ሀይል አባላት ዛሬ #በጅግጅጋ_ከተማ የፅዳት ስራ ላይ ተጠምደዋል።


#TIKVAH_ETH ~ የመከላከያ ሰራዊት እና የልዩ ሀይል አባልት እየሰራችሁ ላለው መልካም ስራ ታላቅ #ምስጋና ያቀርባል!

ፎቶ፦ ሚኪያስ (ጅግጅጋ TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 17/2011 ዓ.ም.

ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ የሚከበረው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቀን በአየር ኃይልና በኦሮሚያ ክልል መንግሥት ትብብር #በአዳማ ከተማ እንደሚከበር፣ የኢፌዴሪ መከላከያ ኢንዶክትሪኔሽንና የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት አስታውቋል፡፡ በዓሉም የካቲት 7 ቀን 2011 ዓ.ም. እንደሚከበር ተገልጿል፡፡
.
.
ዛሬ ማለዳ በተካሄደው የዱባይ ማራቶን ጌታነህ ሞላ የቦታውን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፏል። በሴቶች ኬንያውያን እኤአ ከ2006 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አሸንፈዋል፡፡
.
.

አቶ #በረከት_ስምዖንና አቶ #ታደሰ_ካሳ በተጠረጠሩበት የጥረት ኮርፖሬት የሀብት ብክነት ጉዳይ ዛሬ በባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡
.
.
#የአገር_መከላከያ_ሰራዊት አባላት እና የሶማሌ ክልል #ልዩ_ሀይል አባላት ዛሬ #በጅግጅጋ_ከተማ የፅዳት ስራ አከናውነዋል።
.
.
በነጭ ሣር ፓርክ ላይ ለጊዜው ባልታወቀ ምክንያት እሳት ተነስቶ 1 ሺ ሄክታር የሚሆን የፓርኩ ክፍል ወድሟል።
.
.
በድሬዳዋ ከተማ #የተቀሰቀሰው_ተቃውሞ ዛሬ ጥር 17/2011 ዓ.ም. ቀጥሎ ውሏል። የኢንተርኔት አገልግሎት ተዘግቷል።
.
.
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2 ዙር በተካሄደ ነፃ የስራ ዘመቻ 3.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ስራ መሰራቱን ተናግሯል።
.
.
የኢፌዲሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የ100 ቀናት እቅዱን በአርባምንጭ ከተማ ገምግሟል።
.
.
በሱማሌ ክልል በተፈጠረው ግጭት እጃቸውን በማስገባት ወንጀል ሰርተው ከሀገር የወጡ ባለስልጣናትን ወደሀገር #በመመለስ በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ከተሸሸጉባቸው ሀገራት ጋር ስምምነት ላይ መደረሱን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አስታውቋል።
.
.
በሳኡዲ አረቢያ በተለያየ ምክንያት ታስረው የነበሩ 368 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ወደ አገራቸው ገብተዋል።
.
.
በድሬዳዋ ከተማ የተፈጠረው የሰላም መደፍረስ የሕዝቡን አብሮነት እና ተቻችሎ የመኖር እሴት የሚሸረሽር በመሆኑ ሰላምን በማወክ ተግባር የተሰማሩ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የከተማ አስተዳደሩ አሳስቧል።
.
.
በኢትዮጵያ #የመጀመሪያ የሆነ የሚዲያ ኤክስፖ በኤግዚብሽን ማዕከል ዛሬ ተከፍቷል።
.
.
የቀድሞ የደህንነት ኃላፊ አቶ #ጌታቸው_አሰፋን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከክልሉ መንግሥት ጋር እየሰራ እንደሆነ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጿል።
.
.
በጉጂ ዞን ይንቀሳቀሱ የነበሩ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር /ኦነግ/አባላት ከጫካ ወጥተው #በሰላማዊ መንገድ ለመታገል መወሰናቸውን ገልፀዋል።
.
.
የሱማሌ ክልል መሪ--አቶ #ሙስጠፋ_ኡመር-የፌዴራል ገንዘብ ሚኒስትሩን አቶ #አህመድ_ሺዴን-በይፋ በክልሉ መንግስት ላይ "ዓመፃ-ክህደት በመፈፀም" እጅግ ከባድ ወንጀል #ከሰዋል

ምንጭ፦ አዲስ ስታንዳርድ፣ fbc፣ ኢዜአ፣ ኢ.ፕ.ድ.፣ elu፣ ቢቢሲ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት

.
.
አመሰግናለሁ! ሰላም እደሩ!!
ሀገራችን ቸር ትደር!!
ጥር 17/2011 ዓ.ም.
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ግምታዊ ዋጋው 400 ሺህ ብር የሚያወጣ የባህርዛፍ አጠና ያለምንም ህጋዊ ሰነድ ከአገር ሊወጣ ሲል #በጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት መያዙን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ። የኮንትሮባንድ ዕቃው በሰሌዳ ቁጥር 79780/00054 በሆነ ተሳቢ መኪና ተጭኖ ሊወጣ ሲል ቶጎጫሌ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በጉምሩክ ባለሙያዎችና በመከላከያ ሰራዊት አባላት የጋራ ጥረት ሊያዝ ችሏል፡፡ በተያያዘም በቀን 20/05/11 ከምሽቱ 3፡30 ላይ በሌላ ተጠርጣሪ 2 ግራም የሚሆን ሜርኩሪ መሰል ማዕድን በሶማሌ ክልል አድርጎ ወደ ሶማሌ ላንድ ሊያስወጣ ሲል በቁጥጥር ስር መዋሉም ተገልጿል፡፡

via epa
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ከጭናግሰን ከተማ የማርያምን ክብረ በዐል አክብረው ይመለሱ በነበሩ ምዕመናን ላይ ወጣቶች መንገድ መዝጋታቸውን ተከትሎ #በጅግጅጋ_ከተማ ተፈጥሮ የነበረው ግጭት መረጋጋቱ ታወቀ። በግጭቱ የአንድ ሰው ህይወት አልፏል።

via ELU

በጅግጅጋ የሚኖሩ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት የሟች ቁጥር 2 እንደሆነ ገልፀው መንግስት መፍትሄ እንዲፈልግ ጠይቀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 21/2011 ዓ.ም.

የኢትዮጵያ መንግስት “የጤፍ ባለቤት ነኝ” ያለውን የሆላንድ ድርጀት በዓለም አቀፉ የግልግል ፍርድ ቤት ሊከስ ነው።
.
.
በደቡብ ክልል አማሮ ወረዳ ሁለት አርሶ አደሮች በኦሮሞ ነፃ አውጪ ግንባር "ኦነግ ታጣቂዎች" መገደላቸውንና አንድ አርሶ አደር መቁሰሉን የአከባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል።
.
.
በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር የሴፍቲና ሲኬዩሪቲ ዲፓርትመንት ባለሙያዎች በባቡሩ ላይ #ድንገተኛ የእሳት አደጋ ቢከሰት እንዴት መቆጣጠር እንደሚቻል የሚያሳይ ልምምድ አካሂደዋል።
.
.
ጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ በዛሬው እለት የቀጠለውን የሚኒስትርና ተጠሪ መስሪያ ቤቶችን የ100 ቀን እቅድ አፈፃፀም ግምገማ መርተዋል።
.
.
የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፓሬሽን/ሜቴክ/ይቅርታ መጠየቅና #እርቅ ማውረድ ካለበት አካል ጋር ሁሉ እንደሚያደርግ የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ብርጋዴር ጀነራል #አህመድ_ሀምዛ አስታውቀዋል።
.
.
በሰቆጣ ከተማ ሦስት #ፓኪስታናውያን በሕገ ወጥ የሞባይል ሽያጭ ተሰማርተው እጅ ከፈንጅ ተይዘዋል።
.
.
በአዲስ አበባ ከተማ የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ሰርተፍኬት፣ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ፣ የልደትና ሞት ሰርተፍኬት እንዲሁም የጋብቻ እና ፍቺ ሰርተፍኬቶች በዲጂታል ሰርተፍኬት ሊቀየሩ ነው ተብሏል።
.
.
ኢ/ር #ታከለ_ኡማ ቦሌ አራብሳ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ የፈረሰውን መስጂድ በመጎብኘት የአከባቢውን የሙስሊም ማህበረሰብም አነጋግረዋል፡፡
.
.
#የፌዴራል_መንግሥት አመራሮች የድሬዳዋ ነዋሪዎችን በከተማዋ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ አወያይተዋል፡፡
.
.
በተፈጥሮ ሀብት ጥበቃና በማህበራዊ ፍትህ ላይ ያተኮረ የመጀመሪያውን አረንጓዴ የፖለቲካ ፓርቲ (Green Party) ለማቋቋም ጊዜያዊ አስተባባሪ ፓርቲ መሰየሙን ዋዜማ ራድዮ ዘግቧል።
.
.
ከሳውዲ አረቢያ ጋር በተደረገው የሁለትዮሽ ስምምነት መሰረት በህጋዊ መንገድ ለሚሄዱ ሰራተኞች የቪዛ አገልግሎት መሰጠት መጀመሩን የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚንስቴር አስታውቋል።
.
.
ግምታዊ ዋጋው 400 ሺህ ብር የሚያወጣ የባህርዛፍ አጠና ያለምንም ህጋዊ ሰነድ ከአገር ሊወጣ ሲል #በጅግጅጋ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት መያዙን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታውቋል።
.
.
ከጥር 19 እስከ 21 ለተከታታይ ሦስት ቀናት #በሀዋሳ_ከተማ ሲካሄድ የቆየው የኢህአዴግ ወጣቶች ሊግ 4ኛ ድርጅታዊ ጉባዔውን ሊቀመንበርና ምክትል ሊቀመንበሩን በመምረጥ ተጠናቋል።
.
.
ከጭናግሰን ከተማ የማርያምን ክብረ በዐል አክብረው ይመለሱ በነበሩ ምዕመናን ላይ ወጣቶች መንገድ መዝጋታቸውን ተከትሎ #በጅግጅጋ_ከተማ ተፈጥሮ የነበረው ግጭት መረጋጋቱ ታውቋል። በግጭቱ የ2 ሰው ህይወት አልፏል።
.
.
ቀዳማዊት እመቤት #ዝናሽ_ታያቸው የአንደኛ ደረጃ ትምህርታቸውን ለተከታተሉበት የጎንደሩ ጻዲቁ ዮሐንስ 1ኛ ደረጃ ሙሉ ሳይክል ትምህርት ቤት የኮምፒዩተር ድጋፍ አድርገዋል፡፡
.
.
#በድሬዳዋ_ከተማ የትራንስፖርትና የግብይት #አድማ ለማድረግ ያቀዱ ነዋሪዎች ከድርጊታቸው ይቆጠቡ ዘንድ #የምስራቅ_ዕዝ_ጠቅላይ_መምሪያ አስጠነቅቋል።
.
.
አቃቤ ሕግ የቀድሞ #የሜቴክ የስራ #ሀላፊዎች በነበሩት ሻለቃ #ክንደያ_ግርማይና ሌተናል ኮሎኔል #አሰፋ_ዮሐንስ ላይ ክስ መስርቷል።
.
.
የኦጋዴን ብሄራዊ ነፃነት ግንባር (ኦብነግ) በዚህ ሳምንት ሐሙስ በይፋ ትጥቅ ይፈታል።
.
.
በቅርቡ በመንግስት እና ኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) መካከል በአምቦ በተደረገው ስምምነት መሠረት እርቁን ተግባራዊ ለማድረግ የተመረጠው የቴክኒክ ኮሚቴ ሥራውን በተግባር መጀመሩን የቴክኒክ ኮሚቴው አባል አቶ #ጀዋር_መሀመድ አስታውቀዋል።
.
.
ቀዳማዊት እመቤት ወይዘሮ #ዝናሽ_ታያቸው ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምናና የኢንፎርሜሸን ቴክኖሎጂ መሳሪያዎችን ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታልና ለሁለት ትምህርት ቤቶች ድጋፍ አድርገዋል።
.
.
#የኢፌዲሪ_አየር_ሃይል በሶማሊያ ከባይደዋ በስተምስራቅ 75 ኪሎ ሜትር ላይ ቡርሃይቤ በተባለ የአልሻባብ ይዞታ ላይ ጥር 16 ቀን 2ዐ11 ዓ.ም ድብደባ በመፈፀም ከፍተኛ ሰብአዊና ቁሳዊ ኪሳራ ማድረሱን የኢፌዲሪ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።
.
.
ሰሞኑን በድሬዳዋ ከተማ የተከሰተዉን #አለመረጋጋት ተከትሎ የከተማዉ ፖሊስ ኮሚሽን 308 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር አዉሎ ምርመራ እያካሄደ ነዉ፡፡

ምንጭ፦ ዋዜማ ራድዮ፣ etv፣ fbc፣ VOA፣ ኢዜአ፣ ኢ.ፕ.ድ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት፣ የጠ/ሚ ፅ/ቤት፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ አብመድ
.
.
ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፀጥታ ሁኔታው አስተማማኝ ነው~ጅግጅጋ!
.
.
ስምንተኛውን የከተሞች ፎረም #በጅግጅጋ ለማካሄድ ዝግጅቱ መጠናቀቁንና ምንም አይነት የፀጥታ ችግር አለመኖሩን የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ካሳሁን ጎፌ ተናገሩ።

ዝግጅቱን አስመልክቶ በጅግጅጋ መግለጫ የሰጡት ሚኒስትር ዴኤታው ጅጅጋ ላይ የፀጥታ ሁኔታው አስተማማኝ ነው"፤ የክልሉ ፖሊስ ከፌዴራል የፀጥታ አካላት ጋርም በቅንጅት እየሰራ ነው ብለዋል።

በከተማዋ አስተማማኝ የፀጥታ ሁኔታ መኖሩን የገለፁት ሚኒስትር ዴኤታው ተሳታፊ ከተሞች ወደጅግጅጋ ገብተው ዝግጅታቸውን ጀምረዋል ብለዋል።

ዝግጅቶችን በተመለከተ ከነገ ጀምሮ እስከ ረቡዕ ከሚኖሩ ዝግጅቶች መካከል በጅግጅጋ ስቴዲየም የመክፈቻ ስነስርዐት፣ በከተሞች የስራ ዕድል ፈጠራ ኢንተርፕራይዞች ልማት፣ በመሬት ልማት ማኔጅመንት፣ በዘርፉ አጀንዳዎች ማለትም በከተማ ልማት፣ አረንጓዴ ልማትና አካባቢ ጥበቃ፣ በቤቶችና ኮንስትራክሽን እንዲሁም ተያያዥ ዘርፎች ዙሪያ ጥናታዊ ፅሁፎች ይቀርባሉ።

አቶ ካሳሁን ከተሞች ራሳቸውን የሚያስተዋውቁበት ኤግዚቢሽን የሚካሄድ ሲሆን ከዚህ በፊት በተደረጉ ፎረሞች የተስተዋለው የድምፅ ብክለት በዚህ አመት እንዳይኖር ከከተሞች ጋር መግባባት ላይ ተደርሷል ብለዋል።

ሀሙስ በሚኖረው የማጠቃለያ ስርዓት ለሞዴል ኢንተርፕራይዞች፣ ለሴት ስራ ፈጣሪዎች፣ በሁሉም ክልሎች ካሉ የሴክተር ተቋማት በአፈፃፀም ብልጫ ላገኙ እንዲሁም ለዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ስራ ፈጣሪዎች እውቅናና ሽልማት ይሰጣል ተብሏል።

በተመሳሳይ የዘጠነኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም አዘጋጅ በእለቱ ይፋ ይደረጋል፤ የዋንጫ ርክክብም ይኖራል ብለዋል ሚኒስትር ዴኤታው።

ስምንተኛውን የከተሞች ፎረም የተለየ ለማድረግ ከማሌዥያ አለምአቀፍ የከተሞች ፎረም ልምድ ተወስዷል ያሉት አቶ ካሳሁን ፎረሙ ለመጀመሪያ ጊዜ በታዳጊ ክልል መካሄዱም ልዩ ያደርገዋል ብለዋል።

የሱማሌ ክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ሀላፊ ዶ/ር #አብዱልፈታህ_ሸክቢሂ በበኩላቸው ክልሉ ፎረሙን ለማስተናገድ ዝግጅቱን አጠናቋል፤ ተሳታፊ ከተሞችም ወደ ጅግጅጋ እየገቡ ነው ብለዋል።

ቢሮ ሀላፊው በጥቂት ግለሰቦች ከወራት በፊት ተከስቶ የነበረው ችግር ገፅታችንን አበላሽቶ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ምንም የፀጥታም ይሁን የደህንነት ችግር የለም ብለዋል።

ዶ/ር አብዱልፈታህ ስምንተኛው የከተሞች ፎረም የክልላችንን ብሎም የከተማችንን አስተማማኝ ሰላም የምናረጋግጥበትና በተግባርም የምናሳይበት እንዲሆን ሰፊ ስራ ሰርተናል ውጤቱንም እያየን ነው ብለዋል።

ስምንተኛው የኢትዮጵያ ከተሞች ፎረም ከየካቲት 9-14/2011 ''መደመር ለኢትዮጵያ ከተሞች ብልፅግና'' በሚል መሪ ቃል በጅግጅጋ ይካሄዳል።

ምንጭ፦ EPA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጅግጅጋ🔝

ስምንተኛው #የኢትዮጵያ_ከተሞች_ፎረም የመክፈቻ ስነ ስርዐት #በጅግጅጋ ስቴዲየም --''መደመር ለኢትዮጵያ ከተሞች ብልፅግና'' ከየካቲት 9-14/2011 ዓ.ም.

@tsegabwolde @tikvagethiopia
#ጅግጅጋ

በነገው እለት #በጅግጅጋ ለሚደረገው የኦሮሚያ ክልልና የሱማሌ ክልል ህዝቦች የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት መድረክ ላይ ለመሳተፍ በኦሮሚያ ክልል ምክትል ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ አብዲሳ የሚመራ የኦሮሚያ ክልል ተወካዮች ቡድን ዛሬ ጅግጅጋ ገብቷል፡፡ ቡድኑ ጅግጅጋ ሲደርስ ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል፡፡ የሁለቱ ህዝቦች የወንድማማችነት መድረክ ከዚህ ቀደም በአዳማ ከተማ መደረጉ ይታወሳል፡፡

Via #ebc
@tsegabwolde @tikvahethiopia