TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የብድር_ገደብ

ብሔራዊ ባንክ የጣለው የብድር ገደብ በባንኮች እና ተበዳሪዎች ላይ ተግዳሮት መፍጠሩ ተነግሯል።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ / #NBE ከጥቂት ወራት በፊት ያወጣው የገንዘብ ፖሊሲ ወደ ትግበራ ገብቷል፡፡

የዋጋ ንረትን ለመቆጣጠር ዋነኛ ዓላማ ያደረገው ይህ ፖሊሲ ፣ የባንኮች የብድር ምጣኔ ካለፈው ዓመት ከ14 በመቶ በላይ እንዳይበልጥ ገደብ የጣለ ነው፡፡

በተለይ ባንኮች የሚሰጡት ብድር በገንዘብ ፖሊሲው ከተጣለባቸው ገደብ ጋር ለማጣጣም በማሰብ ቀደም ብለው የፈቀዷቸውን ብድሮች ጭምር ከመልቀቅ እንዲቆጠቡ ወይም መሰል አሠራርን እንዲከተሉ እያደረጋቸው ስለመሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡ 

ከመመርያው መውጣት ቀደም ብለው የተፈቀዱ ብድሮች ሊለቀቅላቸው እንዳልቻለ የተለያዩ ባለሀብቶችና የንግድ አንቀሳቃሾች ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ገልጸዋል።

በዚህም የተፈቀደላቸውን ብድር ታሳቢ በማድረግ የገቧቸው የቢዝነስ ስምምነቶች እየተፋረሱባቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ቤትና ተሽከርካሪ ግዥ ውሎች ሳይቀሩ በእንጥልጥል እንዲቆዩ ማድረጉንም ከተበዳሪዎች መገንዘብ ተችሏል፡፡ 

ብድር እንዲለቀቅላቸው #ማረጋገጫ አግኝተው የነበሩት ተበዳሪዎች አሁን ላይ ብድሩን ማግኘት ለምን እንዳልቻሉ ለሚያቀርቡት ጥያቄ የሚያገኙት ምላሽ " አዲሱ የገንዘብ ፖሊሲ የጣለው የብድር ዕቀባ " መሆኑን ያስረዳሉ።

አንዳንዶቹም የተፈቀደላቸውን ብድር በትዕግሥት እንዲጠብቁ እንደተነገራቸው ያመለክታሉ፡፡

ቤት ለመግዛት ተዋውለው ከሚገለገሉበት ባንክ የፈቀደላቸውን ብድር እየተጠባበቁ የነበሩ አንድ ተበዳሪ ብድሩ እንደሚያገኙት በተገለጸላቸው ወቅት ሊለቀቅላቸው ባለመቻሉ የቤት ሽያጭ ውላቸው ሊፈርስባቸው እንደሆነ ገልጸዋል። እንዲህ ያለው ችግር በአብዛኛው በግል ባንኮች አካባቢ የሚስተዋል ነው፡፡

ያንብቡ 👇
https://telegra.ph/Reporter-Newspaper-10-17

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች መታሰራቸው ተሰምቷል።

የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ታምሩ ገምበታን ጨምሮ ቁጥራቸው ለጊዜው ያልታወቁ ሰዎች በሙስና ወንጀል ተጠርጥረው መታሰራቸውን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ሰሞኑን መሆኑንና አቶ ታምሩ ገምበታ ግን ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. መሆኑ ተገልጿል።

የምክትል ዳይሬክተሩ ቤት በፍርድ ቤት የብርበራ ፈቃድ መበርበሩንና ዛሬ ጥቅምት 7 ቀን 2015 ዓ.ም. ፍርድ ቤት ሊቀርቡ እንደሚችሉ ተጠቁሟል፡፡

የመንግሥት አስተዳደር ለውጥ ከተደረገ ጀምሮ የኢሚግሬሽንና ዜግነት ጉዳይ አገልግሎት ተቋም ውስጥ የተለያዩ ለውጦች (ሪፎርም) የተደረገ ቢሆንም፣ አንዳንድ የተቋሙ ሠራተኞች በድለላ ሥራ የተሰማሩ አካላት ጋር በመመሳጠር የሙስና ወንጀል ፈጽመዋል ተብለው በቁጥጥር ሥር ውለው በምርመራ ላይ እንዳሉም ተመላክቷል።

አገልግሎቱን በዋና ዳይሬክተርነት ይመሩ የነበሩት አቶ ብሩህተስፋ ሙሉጌታ፣ ምክትል ዳይሬክተር የነበሩት አቶ ፍራኦል ጣፋና አቶ ታምሩ ገምበታን ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ከ3 ወራት በፊት ሐምሌ መጀመሪያ ሳምንት አካባቢ ከኃላፊነት ማንሳታቸው ይታወሳል፡፡

ተቋሙ ከፓስፖርትና መሰል አገልግሎቶች ጋር በተያያዘ ቅሬታ ሲቀርብበት መቆየቱ ይታወቃል።

በተጨማሪ ከዜጎች ከፍተኛ ገንዘብ በመቀበል በሕወጥ መንገድ ወደ ውጭ አገር ሲልኩ ነበር የተባሉ 16 የተቋሙ ሠራተኞች፣ እንዲሁም 5 በአሠሪና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲ ስም ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ሰዎችም ከዚህ ቀደም በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

በተያዘው ሳምንት በቁጥጥር ሥር መዋላቸው የተሰማው ምክትል ዳይሬክተሩን ጨምሮ ሌሎች ሰዎችም ከሙስና ጋር በተያያዘ መጠርጠራቸው ተገልጿል፡፡

ምንጭ፦ #ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia
የሀገር_ውስጥ_ተፈናቃዮች_የሰብአዊ_መብቶች_ሁኔታ_ዓመታዊ_ሪፖርት.pdf
3.8 MB
#ኢሰመኮ

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) 2ኛውን በአገር ውስጥ ተፈናቃዮች የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ ላይ የሚያተኩር ዓመታዊ ሪፖርት በቀናት በፊት ይፋ አድርጓል፡፡

በሪፖርቱ ምን አለ ?

- ዜጎችን ከመደበኛ የመኖሪያ ቦታቸው ያፈናቀሉ፣ የሰው ሕይወት ያጠፉ፣ ሀብት ያወደሙ፣ አካላዊ ጉዳት ያደረሱ ቡድኖችና ግለሰቦች በሕግ ተጠያቂ ለማድረግ በቂ ዕርምጃዎች ባለመወሰዳቸው የሕግ በላይነት፣ ተጠያቂነትንና የተፈናቃዮችን ፍትሕ የማግኘት መብት የሚነፍግ ነው።

- በዘፈቀደ ለሚደረጉ የማፈናቀል ድርጊቶች አስተማሪ ዕርምጃዎች እየተወሰዱ አይደሉም።

- ዘላቂ የመፍትሔ አማራጮች አተገባበርም የመፈናቀል ምክንያት የሆኑትን የደኅንነት ሥጋቶች ባስወገደ፣ ተፈናቃዮችንና ተቀባይ ማኅበረሰብን ባሳተፈ፣ የተፈናቃዮችን ፍላጎት ባገናዘበ፣ እንዲሁም ተፈናቃዮችን በዘላቂነት በሚያቋቁም ሁኔታ ባለመሆኑ፣ ለዳግም መፈናቀል የሚያጋልጥ ነው።

- አብዛኛዎቹ ተፈናቃዮች ዘላቂ መፍትሔ ሳያገኙ በመጠለያ ጣቢያዎችና ከተቀባይ ማኅበረሰብ ጋር ተቀላቅለው መኖር ከጀመሩ በትንሹ ሦስት ዓመታት አልፏቸዋል።

- ተገቢው ጥበቃ የማይደረግላቸው፣ እንዲሁም የሲቪልነት ባህሪን ያልጠበቁ በወታደራዊ ካምፖች አካባቢ የሚኖሩ ተፈናቃዮች የሚገኙባቸው መጠለያ ጣቢያዎች መኖራቸው፣ የተፈናቃዮች የደኅነነት ሁኔታ አደጋ ላይ መሆኑን እንደሚያሳይ፣ በተጨማሪም መንግሥት በካምፓላ ስምምነት መሠረት የተጣለበትን ግዴታ በአግባቡ አለመወጣቱን የሚጠቁም ነው።

- መንግሥት ፈርሞ የተቀበለውን የካምፓላ ስምምነትን ለማስፈጸም የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ፀድቆ ሥራ ላይ አለመዋሉና የተፈናቃዮችን ጉዳይ በባለቤትነት የሚያስተዳድር ተቋማዊ አደረጃጀት የለም።

- መፈናቀልን ለመከላከል ለተፈናቃዮች የሚደረጉ የጥበቃና ድጋፍ ሥራዎች፣ እንዲሁም የዘላቂ መፍትሔ ማፈላለግ ሒደቶች ላይ የሚስተዋሉ ክፍተቶች አሁንም አሳሳቢነታቸው ቀጥሏል።

- የተፈናቃዮች ምዝገባና ሰነድ የማግኘት ሥርዓቱ ላይ ያለው ክፍተት ለተፈናቃዮች የሚደረገው ድጋፍ በአግባቡ እንዳይከናወን አሉታዊ ተፅዕኖ አሳድሯል። በተጨማሪ ተፈናቃዮች ሌሎች የመንቀሳቀስና የማኅበራዊ አገልግሎት የማግኘት መብቶቻቸውን ለመጠቀም እንዳይችሉ አድርጓል።

- በኢትዮጵያ 80 በመቶ የሚሆነው መፈናቀል ኃይል በተቀላቀለባቸው ግጭቶች ምክንያት የሚከሰት በመሆኑ መፈናቀልን ለመከላከልና በዘላቂነት መፍትሔ ለመስጠት፣ በዋናነት ግጭቶችን ወቅታዊ በሆነ ሁኔታ በሰላማዊ መንገድ መፍታት ያስፈልጋል፡፡ #ሪፖርተር

(ከኢሰመኮ የተላከ ሙሉ ሪፖርት ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ተመዝጋቢዎች ወስኖ የነበረው ፍርድ፣ በፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገ መንግሥት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ መሻሩን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

የፌዴሬሽን ምክር ቤት መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ባደረገው የሦስተኛ ዓመት የአንደኛ መደበኛ ጉባዔ ላይ በወሰነው መሠረት፣ ፍርድ ቤቶች ያስተላለፉትን ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ ተመዝጋቢዎች ቤቶች እንዲሰጡ የሚለው ውሳኔ የተወሰኑ የሕገ መንግሥቱ ድንጋጌዎችን የሚጥሱና ተቀባይነት የላቸውም በማለት በሙሉ ድምፅ ሽሮታል።

በምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ አቶ አገኘሁ ተሻገር ተፈርሞ ኅዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም. ለከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የተጻፈው ደብዳቤ፣ በ2005 ዓ.ም ወጥቶ የነበረውን የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን የዕጣ ድልድል ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ ቅድሚያ የሚሰጠው መመርያ የሕገ መንግሥት ትርጉም እንደሚያስፈልገው በምክር ቤቱ ታምኖ እንዲታይ ይገልጻል፡፡

" ሕገ መንግሥታዊ የአካታችነትና የፍትሐዊነት መርህን የጣሰ " ሲል የመመርያውን አንድ አንቀጽ የገለጸው የፌዴሬሽን ምክር ቤት ደብዳቤ፣ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቁጠባ ቤቶች ዋነኛ ዓላማ 40 በመቶ የቆጠቡ ተመዝጋቢዎች ከባንክ በተመቻቸ 60 በመቶ ክፍያ በመደገፍ እንዲያገኙ ማስቻል እንደሆነ ነው የሚያስረዳው፡፡

ሆኖም አንደኛው የመመርያ አንቀጽ ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ ቅድሚያ እንዲሰጣቸው የሚያደርግ ሲሆን፣ ይህም ድንጋጌ መግባቱ ‹
" የመመርያውን ግልጽ ዓላማና መንፈስ ያልተከተለ " ሲል ደብዳቤው ያስረዳል፡፡

" ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ ቅድሚያ መስጠት በመርሐ ግብሩ ለተመዝጋቢዎች እኩል ዕድል ለማሰጠት የታለመውን መሠረታዊ ዓላማ የጣሰ ነው፤ " ሲል ደብዳቤው ያብራራል፡፡

የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች መርሐ ግብርን የሚያስፈጽመው መመርያ በሰጣቸው መብት መሠረት ሙሉ ለሙሉ የሚጠበቅባቸውን ቁጠባ ከቆጠቡ በኋላ፣ ቅድሚያ እንደሚሰጣቸው የጠበቁ 761 ቆጣቢዎች በዕጣ ማውጣት መርሐ ግብሩ ላይ ቅድሚያ ሳይሰጣቸው 40 በመቶ ከቆጠቡት ጋር እኩል ነበር የተሳተፉት፡፡

ለዚህም ነበር 761 ተመዝጋቢዎች የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝን በመክሰስና እስከ ሰበር ድረስ በመድረስ ሊፈረድላቸው የቻለው፡፡

በፍርድ ቤቶች ተወስኖ የነበረው እየተገነቡ ያሉና ዕጣ ያልወጣላቸውን ቤቶች፣ ከዚህ በኋላ ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ ተመዝጋቢዎች እንዲተላለፉ ነበር፡፡

በውሳኔው ቅር ተሰኝቶ የነበረው የከተማ አስተዳደሩ የቁጠባ ቤቶች ኢንተርፕራይዝ ከአንድ ዓመት በፊት ለሕገ መንግሥታዊው ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔ አቤቱታ አቅርቦ፣ ጉባዔው ጉዳዩን በመመርመር በዚህ ዓመት መስከረም ወር ምክር ቤቱ ሲከፈት ውሳውን አሳልፏል፡፡

የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን መርሐ ግብር ለማስፈጸም ወጥቶ በነበረው መመርያ ሙሉ ለሙሉ ለቆጠቡ ተመዝጋቢዎች ቅድሚያ የሚያሰጠውን አንቀጽ፣ ከመስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ " ኢሕገ መንግሥታዊ " በመባሉ እንደማይሠራ ምክር ቤቱ ወስኗል፡፡

የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴርም አውጥቶት የነበረው የዚህ መመርያ ድንጋጌ፣ ደብዳቤው ከደረሰው ከኅዳር 3 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ በአንድ ወር ውስጥ እንዲያሻሽልና ውጤቱን ለምክር ቤቱ እንዲያሳውቅ ያሳስባል፡፡ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ደብዳቤውን በግልባጭ ለሁሉም የክልልና የከተማ አስተዳደሮች አሳውቋል።

#ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia
" የተሸለምኩትን 100 ሺህ ብር በትግራይ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ ሠጥቻለሁ " - ዕበ ለገሠ

የግሉን አውሮፕላን ሠርቶ በሰማይ ላይ መንሳፈፍ የልጅነት ምኞቱ ነበር ፣ በሽረ እንደሥላሴ ከተማ ነዋሪ የሆነው ዕበ ለገሠ።

ሐሳቡን ወደ ተግባር ለመለወጥ እልህ አስጨራሽ ጉዞ ማድረጉን ይናገራል። ከበርካታ ጥረቶች በኋላ ለሦስት ደቂቃ ያህል መብረር የምትችል ሔሊኮፕተር መስራቱን እንደቻለ ገልጿል።

በስምንት ወራት ውስጥ ተሠርታ የተጠናቀቀችው ሔሊኮፕተሯ፣ ከ1.5 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ እንደተደረገባት ዕበ ተናግሯል።

ለአብራሪው ብቻ የሚሆን ቦታ ቢኖራትም፣ እስከ አራት ሰው ወይም አራት ኩንታል ጭነትን ተሸክማ መብረር እንደምትችል ተናግሯል፡፡

ሔሊኮፕተሯ ተጠናቃ ወደ ሥራ ስትገባ፦
- ድንገተኛ የእሳት ቃጠሎዎችን ለማጥፋት፣
- የአንበጣ መንጋን ለመከላከልና ቅኝት ለማድረግ ታገለግላለች፡፡ ሰዎች ለትራንስፖርት ሊጠቀሙበትም ይችላሉ ብሏል።

ባለፈው ሳምንት በአዲስ አበባ ተካሂዶ በነበረ የአቪዬሽን ኢኖቬሽን ውድድር፣ ሔሊኮፕተር ሠርቶ በማቅረብ አንደኛ በመውጣት 100 ሺህ ብር ተሸላሚ ሆኗል።

የሽልማቱን ገንዘብ በትግራይ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች ድጋፍ እንደሰጠ ዕበ ጠቁሟል፡፡

ሔሊኮፕተሯ ተሻሽላ ገበያ ላይ መዋል የምትችልና የተሠራችበት ቁሳቁስ ሙሉ በሙሉ በአካባቢ የሚገኙ መሆናቸው ዕበን ለአሸናፊነት አብቅቶታል፡፡

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ፈጠራውን ለማገዝ ቃል እንደገባለት የገለጸው ዕበ፣ በቀጣይ ከዚህ የተሻለ ነገር ይዞ ለመቅረብ እንደሚሠራ ተናግሯል፡፡ #ሪፖርተር

Via @tikvahuniversity
#ጥናት

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የጋራ መኖሪያ ቤቶች (ኮንዶሚኒየም) ጥራታቸው ተጠብቆ ባለመገንባታቸው፣ በዕጣ የቤት ባለቤት የሆኑ ዕድለኞች ለከፍተኛ ወጪ እየተዳረጉ መሆናቸውን የአፍሪካ ከተሞች የምርምር ጥምረት (ACRC) እና ፎረም ፎር ሶሻል ስተዲስ (FSS) በጋራ ባደረጉት ጥናት ማረጋገጥ መቻላቸውን አስታውቀዋል።

ሁለቱ ተቋማት ጥናቱን ለአንድ ዓመት ያህል ነው ያደረጉት።

በጥናቱ ከ6 በላይ ከፍተኛ ተመራማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን በኢኮኖሚ፣ በመዋቅራዊ ሽግግርና በወጣቶች አቅም ግንባታና በመኖሪያ ቤቶች ላይ የተደረገ ነው።

ጥናቱ ምን ይላል ?

- በአዲስ አበባ ከተማ ከመነሻውም የጋራ መኖሪያ ቤቶች ሲገነቡ ደረጃቸውን የጠበቁ አይደሉም፡፡

- መንግሥት 40/60 ወይም የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶችን በዕጣ ለደረሳቸው ሲያቀርብ ጥራታቸውን በጠበቀ መንገድ ስለማይገነቡ፣ ዕድለኞች መልሰው አፍርሶ ለመሥራት ይገደዳሉ ለከፍተኛ ወጪ ይዳረጋሉ።

- የጋራ መኖሪያ ቤት የደረሳቸው ዕድለኞች ፦
* ለኤሌክትሪክ ኃይል ዝርጋታ፣
* የሲራሚክ ንጣፍ፣
* ለመፀዳጃ ቤት መስመር፣
* ግድግዳ እንደገና ለመሥራትና ሌሎች የጎደሉ ነገሮች ለማሟላት ለከፍተኛ ወጪ ይዳረጋሉ።

- እነዚህ ጉዳዮች ከፍተኛ ትኩረት የሚፈልጉ በመሆናቸው፣ መንግሥት ለጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታ ከግብዓት ጀምሮ እስከ ባለሙያ ድረስ ጥራታቸውን በመጠበቅ ማቅረብ ይኖርበታል።

በተጨማሪ ...

በአዲስ አበባ ከተማ በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች ለሥራ ተስማሚ የሆኑ ነገሮች እንደሌላቸው ታይቷል። ወጣቶች በኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ፣ በኢመደበኛ ዘርፍና በጤና ላይ ያላቸውን በጎ ተግባራትና ያሉባቸው ችግሮች ተለይተው በጥናቱ ተካተዋል።

በኢትዮጵያ ከዚህ በፊት አብዛኛውን የቤት አቅርቦት ተፈጻሚ የሚሆነው በመንግሥት ሲሆን በአሁኑ ወቅት የተለያዩ ቤት አልሚ ድርጅቶች ተቋቁመው የማኅበረሰቡን የቤት ጥያቄ እየመለሱ መሆናቸው የሚበረታታ ነው።

በቤት አቅርቦት ላይ ለውጦች እየመጡ ቢሆንም አሁንም የመሬት አቅርቦት፣ እንዲሁም በዝቅተኛና በመካከለኛ ገቢ ላይ የሚገኙ ሰዎች ቤት ለመሥራት ቢፈልጉ የፋይናንስ አቅርቦት ችግር እየገጠማቸው ነው።

👉 በአጠቃላይ ጥናት የተደረገባቸው ጉዳዮች ላይ ያሉትን ችግሮች ለመፍታትና በጥናቱ የቀረቡ ግኝቶች መሬት ወርደው ተግባራዊ እንዲሆኑ፣ ለፖሊሲ አውጪዎች የሚቀርቡ ይቀርባሉ ተብሏል።

#ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

ለነዳጅ ማደያዎች ማስጠንቀቂያ ተሰጣቸው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ በአዲስ አበባ ከተማ ለሚገኙ የነዳጅ ማደያዎች በሙሉ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያ መስጠቱን ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

ቢሮው በተለያዩ ባለሙያዎች እያደረገ ባለው የመስክ ሥራ አማካይነት በከተማዋ ሕገወጥ የነዳጅ ንግድ በመስፋፋቱ ምክንያት ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን፣ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የቢሮው ባልደረባ ተናግረዋል።

እኚሁ ባልደረባ ምን አሉ ?

- ቢሮው ያስተላለፈውን ማስጠንቀቂያ ተላልፎ የሚገኝ ማንኛውም የነዳጅ ማደያ መመርያው በሚያዘው መሠረት ታሽጎ ክስ ይመሠረትበታል።

- በተለያዩ ሱቆች፣ በመኖሪያ ቤት፣ በመንገድ ላይና ሕጋዊ የነዳጅ ማደያ ቦታ ባልሆኑ አካባቢዎች ነዳጅ በዕቃ በመቅዳት ሽያጭ እየተከናወነ በመሆኑ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል።

- በቢሮው መመርያ መሠረት ሕጋዊ ደብዳቤ ከተጻፈላቸው ድርጅቶች ውጪ፣ በቀንም ሆነ በሌሊት ምንም ዓይነት የበርሜል ሽያጭ ማካሄድ አይቻልም።

- መመርያውን መሠረት በማድረግ ለነዳጅ አዳዮች በተደጋጋሚ ግንዛቤ በማስጨበጥ፣ እንዲሁም ደብዳቤ እንዲደርሳቸው በማድረግ ሕገወጥ ድርጊቶች እንዳይፈጸሙ ጥረት እየተደረገ ነው።

- በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት ሕጋዊ ደብዳቤ ከሚጻፍላቸው የንግድ ድርጅቶችና ነዳጅ ከሚጠቀሙ ተሽከርካሪዎች በስተቀር፣ በዕቃና በበርሜል የነዳጅ ሽያጭ የተከለከለ ነው፡፡

- የነዳጅ ማደያዎቹ በዕቃ እንዲሸጡ የሚፈቅደውን በየስድስት ወራት የሚታደሰውን ደብዳቤ መያዝ ግዴታ ነው።

- ያለ ደብዳቤ ነዳጅ በመግዛት ሕገወጥ ሽያጭ የሚፈጽሙ ነጋዴዎች ማደያ መግባት ለማይችሉ አነስተኛ ባጃጆች፣ እንዲሁም የነዳጅ እጥረት በሚኖርበት ወቅት በተጋነነ ዋጋ ለመሸጥ ነው።

- በአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባ የቤንዚን ዋጋ 77.65 ብር ሲሆን፣ በዕቃ በመቅዳት ውጪ የሚሸጠው እስከ 80 ብር ድረስ ነው።

- በዕቃ ተቀድቶ የሚሸጠው የዋጋ ጭማሪ በማድረግ ከመንግሥት ታሪፍ ውጪ ከመሸጥም በላይ፣ እንደ ቤንዚን ያሉ ምርቶች ደግሞ ወዲያውኑ አገልግሎት ላይ ማዋል እንጂ ማስቀመጥ ለደኅንነት አሥጊ ናቸው።

- ይህ እየታወቀ የነዳጅ ማደያ ድርጅቶች ስህተት እንዳይፈጽሙ ቅድመ ማስጠንቀቂያ መስጠት አስፈላጊ በመሆኑ፣ እንዲሁም ቢሮው ባደረገው የመስክ ምልከታ በየመንገዱ ሲሸጥ የተገኘውን በመመልከት ሽያጭ እንዳያካሂዱ ክልከላ ብቻ ያደረገ በመሆኑና እስካሁን የቅጣት ዕርምጃ ባለመወሰዱ፣ ሕገወጥ ድርጊቱ ሳይስፋፋ ዕርምጃ ለመውሰድ የተሰጠ ማስጠንቀቂያ ነው።

የንግድ ቢሮው ዕርምጃ መውሰድ የሚችለው በንግድ ስም የተቋቋሙ ድርጅቶች ላይ ብቻ በመሆኑ፣ ሕገወጥ ድርጊት የሚከናወነው በመኖሪያ ቤት ከሆነ ከደንብ ማስከበር፣ ከፖሊስ፣ ከሕገወጥና ኮንትሮባንድ ግብረ ኃይል ጋር በመሆን ምርቱ እንዲወረስና ክስ እንዲመሠረት ይደረጋል ተብሏል። #ሪፖርተር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ድርቅ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድርቅን በተመለከተ በሰጡት ማብራሪያ " አሁን የተከሰተው ከ77ም ያልተናነሰ ነው " በሚል ከዚህ ቀደም የተሰጡ አስተያየቶችን ኮነኑ። " የሚታረስ መሬት እያለን የሰው ጉልበት እያለን ድህነንት እና ልመናን ጌጥ አናድርገው " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ አህመድ " ተቸግረዋል ሊያልቁ ነው ሲሉን እንደ ሽልማት አንውሰደው ኮሮና መጣ ሊረግፉ ነው አሉ ረገፍን እንዴ ? አልረገፍንም ሟርት ነው።…
#OxfamInternational

ኦክስፋም ኢንተርናሽናል በትግራይ ክልል ጦርነትና የዝናብ እጥረት ያስከተለውን የከፋ የሰብዓዊ ቀውስ ጠቅሶ፣ " ሰው ሲራብ ቆሞ መመልከት የሞራልና የፖለቲካ ኪሳራ ነው " ሲል አስታወቀ፡፡

ኦክስፋም ፤ በረሃብ የተጠቁ ቤተሰቦች ችግሩን ለማምለጥና በሕይወት ለመትረፍ ሲሉ የመጨረሻ ተስፋ አስቆራጭ ዕርምጃዎችን እየወሰዱ መሆናቸውን አስታውቋል፡፡

ኦክስፋን አነጋገርኳቸው ያላቸው በአንድ ትምህርት ቤት ከተጠለሉ ቤተሰቦች መካከል  ፦
- እናቶች፣ ልጆቻቸው ተርበው ቀኑን በሙሉ የሚያበሏቸው ነገር ማጣታቸውን፣
- እናቶች ልጆቻቸው ረሃቡን ሊቋቋሙ ባለመቻላቸው የረሃብ ሕመምን ለማስታገስ ለረጅም ሰዓታት እንዲተኙ እንደሚያስገድዷቸው
- ሰዎች ለእንስሳት የሚሆኑ ሥራ ሥሮችን ለመመገብ መገደዳቸውን መናገራቸውን ገልጿል፡፡

ነፍሰ ጡርና የሚያጠቡ እናቶች በረሃብ እየተሰቃዩ መሆናቸውንም አክሏል፡፡

የኦክስፋም የኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር አቶ ገዛኸኝ ፤ " አሁን የሚታየው የችግሩ ጫፍ  ነው " ብለዋል።

በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች አስከፊ የሆነ ረሃብ ውስጥ ሊገቡ እንደሚችሉና ዜጎች ቀጣዩን ምግባቸውን ማግኘት ከባድ የሆኑ መንገዶችን እያለፉ መሆኑን አስረድተዋል፡፡

በዓለም አቀፍ ደረጃ አስከፊ ከሆኑ የሰብዓዊ ቀውስ ክስተቶች አንዱ ለሆነው የሰሜን ኢትዮጵያ የዕርዳታ አቅርቦት፣ ይጠበቅ ከነበረው 4 ቢሊዮን ዶላር ማግኘት የተቻለው 34 በመቶ ብቻ መሆኑን ኦክስፋም ጠቁሟል፡፡

አፋጣኝ የሰብዓዊ ዕርዳታ አቅርቦት ካልተደረገ የበርካታ ዜጎች ሕይወት አደጋ ውስጥ መሆኑን ዋና ዳይሬክተሩ አቶ ገዛኸኝ ተናግረዋል፡፡

በተመሳሳይ ኮንሰርን ወርልድ ዋይድ የተሰኘው ዓለም አቀፍ ድርጅት ባወጣው ሪፖርት፣ በኢትዮጵያ ተከስቷል ያለው ረሃብ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን አስታውቋል፡፡

በአፋር፣ በአማራ እና በትግራይ ክልሎች የተከሰተው የተመጣጠነ ምግብ እጥረት በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና ከተሰጣቸው መሰል ክስተቶች እጅግ የላቀ መሆኑን ድርጅቱ በሪፖርቱ አመላክቷል።

የሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም በቅርቡ ይፋ ባደረገው ሪፖርት በትግራይ እና በአማራ ድርቅ ባስከተለው ረሃብ ምክንያት 372 ሰዎች መሞታቸውን ፤ 23 ህፃናት በአልሚ ምግብ እጥረት ምክንያት ተገቢዉን ዕድገት ባለማግኘታቸዉ ሞተው መወለዳቸውን ማረጋገጡ ማሳወቁ ይታወሳል።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሰጡት ማብራሪያ " ድርቅ ለኢትዮጵያውያን ልክ እንደ ባህላችንና እንደ ዓድዋ ድል ለ100 ዓመታት ሲጎበኘን የቆየ ጉዳይ በመሆኑ፣ እንደ አዲስ ሊወራ የሚችል ነገር አይደለም " ብለው ነበር።

" ድርቁን መንግሥት አላመጣውም " ያሉት ጠ/ሚኒስትሩ፤ " ድርቅን እንደ ፖለቲካ ማየት የለብንም፡፡ የአየር ንብረት ለውጥ ችግር አለ፣ ችግኝ እንትከል ሲባል ችግኝ ምን ያደርጋል ? ድርቅና ረሃብ አለ ስንዴ እናምርት ሲባል ስንዴ ምን ያደርጋል? ካልን በኋላ ድርቅ መጣ ብለን ብንጮኸ ትርጉም የለውም " ሲሉ አስረድተዋል፡፡

" ድርቁን ለፖለቲካ መጠቀም ጥፋት ነው " ብለው፤ ባለፉት 4 ወራት 500 ሺሕ ኩንታል እህል በመንግሥትና በተራድኦ ድርጅቶች ትብብር ለተረጂዎች መላኩን ተናግረዋል፡፡

" ይህ ሀብት በቂ ካልሆነ ደግሞ የኢትዮጵያ መንግሥት አቅም እያለው በረሃብ የሚሞት ሰው ዓይተን ዝም አንልም " ብለዋል፡፡

" እስካሁን ባለኝ መረጃ በረሃብ ምክንያት የሚሞት ሰው የለም " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ  " መንግሥት ትናንት እንዳደረገው ዛሬም የሚራብ ሰው ካለ ፕሮጀክት ሁሉ አጥፎ በረሃብ እንዳይሞት ከሕዝቡ፣ ከባለሀብቶችና ከክልል መንግሥት ጋር በመሆን የሚችለውን ሁሉ ይሰራል " ብለዋል።

#ሪፖርተር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
በአዲስ አበባ የመሬት አገልግሎቶች ታገዱ። በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የመዋቅራዊ አደረጃጀት ጥናት ተከናውኖ በአዳስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ ጸድቆ ወደ ተግባር እንዲገባ የተወሰነውን ውሳኔ መሰረት በማድረግ የሠራተኞች የባህሪ እና የቴክኒክ ፈተና ተሰጥቶ ውጤቱ ይፋ መደረጉ ይታወቃል። በዚህም አዲስ በተጠናው መዋቅራዊ አደረጃጀት ጥናት መሰረት የሰራተኞች ድልድል ተሰርቶ እስኪጠናቀቅ ድረስ ከዛሬ…
" ዓርብ መጋቢት 6 ምሽት ወደ ትግበራ እንዲገባ ይታወጃል " - ዶ/ር ጣሰው ገብሬ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ሠራተኞችና አመራሮች የብቃት ማረጋገጫ ፈተና ወስደው የወደቁ ከ7,500 በላይ ሠራተኞች ከደረጃ ዝቅ ተደርገው የተመደቡበት የሥራ ዕርከን ድልድል መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ይፋ ይደረጋል ተብሏል።

የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ጣሰው ገብሬ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ፤  " ፈተና ያላለፉት ከደረጃ ዝቅ ብለው ነው የሚሠሩት። ድልድሉ ስለተጠናቀቀ ደብዳቤው በየተቋሙ ይሰጣል " ብለዋል።

" ከሰኞ የካቲት 25 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ለ5 ቀናት የሚቆይ የአቅም ግንባታ ሥልጠና እየሰጠናቸው ነው " ያሉት ኃላፊው " 2ኛው ዙር ሥልጠና ከመጪው ሳምንት ሰኞ መጋቢት 2 እስከ ዓርብ መጋቢት 6/ 2016 ዓ.ም. ይሰጣል። ዓርብ መጋቢት 6/ 2016 ዓ.ም. ምሽት ወደ ትግበራ እንዲገባ ይታወጃል፣ ሥልጠናው እንዳለቀ ወደ ትግበራ ነው የሚገባው " ብለዋል።

በሌላ በኩል ፤ የሠራተኞች ድልድል እንደ አዲስ ተካሂዶ እስኪጠናቀቅ ድረስ በከተማው ሁሉም ክ/ከተሞች " ማናቸውም የመሬት አገልግሎቶች " ለአጭር ጊዜያት መታገዳቸው ይታወሳል።

ታዲያ በመጪው ሳምንት ድልድሉ ይፋ ሲሆን የመሬት አገልግሎቶች መሰጠት ይቀጥላሉ ወይ ? ተብለው ከጋዜጣው የተጠየቁት ዶ/ር ጣሰው ፤ በጉዳዩ ላይ ምንም ዓይነት አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል። 

ጋዜጣው ግን ከመጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም. አዲስ የሥራ ዕርከን ድልድል በኋላ የመሬት ሥራ አገልግሎት በቅርብ እንደሚጀመር በዘርፉ ከተሰማሩ ምንጮች መስማቱን አመላክቷል። #ሪፖርተር

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AU #Fraud #CBE

ቀሲስ በላይ መኮንን ከአፍሪካ ኅብረት ኦፊሳላዊ የክፍያ ሰነድ ጋር ተመሳስለው የተዘጋጁ የተለያዩ ሐሰተኛ የክፍያ ሰነዶችን በመጠቀም ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍሪካ ኅብረት የባንክ ሒሳብ ወደ ሌላ የባንክ ሒሳብ #ከ6_ሚሊዮን_ዶላር_በላይ (367 ሚሊዮን ብር) ለማዘዋወር ሲሞክሩ ነው በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

ፍድር ቤት ቀርበውም ለፖሊስ ተጨማሪ ቀን ተሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዜዳንት አቶ አቤ ሳኖ ምን አሉ ?

" በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካለው የአፍሪካ ህብረት ሒሳብ የወጣ ገንዘብ የለም።

አንድ ሰው ሀሰተኛ ሰነዶችን ተጠቅሞ ለማውጣት ቢሞክርም እዛው በቦታው ላይ ተይዟል።

የማጭበርበር ሃሳብና ገንዘብ ለመውሰድ ጥረት ቢደረግም ማክሸፍ ችለናል። ይህንን የሞከሩት ሰዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ናቸው። እኔ የማውቀው ይህን ብቻ ነው።

በመሰረቱ ጥሬ ገንዘብ በውጭ ምንዛሪ ሊሰጥ አይችልም። አጭበርባሪው መጥቶ  ሲጠይቅ ይህን እንኳን አያውቅም ነበር።

ሰውዬው እዚህ ሀገር የዶላር አካውንት ከሌለው ገንዘቡ ቢተላለፍም የትም ውስጥ ሊገባ አይችልም።

አጭበርባሪዎች በየቀኑ ነው ወደ ባንካችን የሚመጡት ፤ ባንክ ስለምንሰራ ይህ የተለመደ ነው። ነገር ን ሁሌም የማጭበርበር ድርጊቶቹ ከመሳካታቸው በፊት እንደርስባቸዋለን። ለፍርድም እናቀርባቸዋለን።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፥ የደንበኞቹን ሒሳቦች የመጠበቅ ኃላፊነት አለበት ያንን እያደረግን ነው። የአፍሪካ ህብረት እስካሁን ድረስ በይፋ ቅሬታ አላቀረበብንም። "

ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የአፍሪካ ኅብረት ምንጭ ምን አሉ ?

"የእኛ ሒሳብ ላይ መሰል ማጭበርበር ሲያጋጥም ይህ ለሶስተኛ ጊዜ ነው።

አሁን ላይ ማጭበርበሩ #በተከበሩ_ሰዎች አማካኝነት እየተሞከረ ነው። ይህ ደግሞ በጣም አስጨንቆናል። አንድ ቀን ባለስልጣናት ተመሳሳይ ነገር ላለማድረጋቸው ምንም አይነት ዋስትና የለንም።

እምነት እያጣን ነው። ስለዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ ለደሞዝ አነስተኛ መጠን ያለው ፎሬክስ (የውጭ ምንዛሬ) ለመያዝ ወስነናል።

ይህን መሰሉ ሁኔታ የድርጅቱን ገንዘብ በውጭ ማቆየት እንድናስብ እያስገደደን ነው። "

https://telegra.ph/The-Reporter-04-21 #ሪፖርተር_ጋዜጣ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Ethiopia

ትላንትና ማክሰኞ #ከሀዋሳ ወደ #አዲስ_አበባ በመብረር ላይ እያለ የደኅንነት ችግር ሊያስከትል የሚችል ክስተት በገጠመው የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን በረራ ቁጥር #ET154 ላይ የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን ባለሥልጣን ጥልቅ የሆነ የደኅንነት ምርመራ ሊያደርግ እንደሆነ ሪፖርተር ጋዜጣ አስነብቧል።

ትላንት ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ በመጓዝ ላይ የነበረ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ላይ ከፍተኛ ጭስ መከሰቱን፣ ነገር ግን በመንገደኞች ላይም ሆነ በአውሮፕላኑ ላይ ምን ዓይነት እክል ሳይፈጠር ቦሌ ኤርፖርት በሰላም ማረፉ መገለጹ ይታወሳል።

አውሮፕላኑ ውስጥ ለጊዜው በምን ምክንያት እንደተነሳ ያልታወቀው ጭስ መንገደኞችን ከፍተኛ ድንጋጤና ፍርኃት ውስጥ አስገብቷቸው ነበር።

የአውሮፕላኑ ዋና አብራሪ ባስተላለፉት የደኅንነት ጥንቃቄ ዕርምጃ መሠረት ሁሉም ተሳፋሪዎች በአውሮፕላኑ ላይ የተገጠመውን የአየር መሳቢያ የፊት ጭምብል (oxygen mask) እስከማድረግ ደርሰው ነበር።

የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን የበረራ ደኅንነት ክፍል እክል የገጠመው አውሮፕላን ቀጣይ በረራ እንዳያደርግ በማገድ በበረራ ወቅት ያጋጠመውን የደኅንነት ክስተት እንደሚያጣራ ሪፖርተር ጋዜጣ ስማቸው ያልተገለጹ የተቋሙን ምንጮች ዋቢ በማድረግ አስነብቧል።

እኚሁ ምንጮ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አየር መንገዱ በሚሰጠው የአገር ውስጥ የበረራ አገልግሎት ላይ የደኅንነት አደጋ ሊያስከትሉ የሚችሉ ክስተቶች ደጋግመው መከሰታቸውን አስታውሰው የኢትዮጵያ ሲቪል አቪዬሽን አጠቃላይ የደኅንነት ፍተሻ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

ባለፈው ጥር ወር 2016 ዓ/ም ላይ ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ ሲበር የነበረ አንድ የመንገደኞች አውሮፕላን በመቐለ አሉላ አባ ነጋ አውሮፕላን ማረፊያ ለማረፍ በሚሞክርበት ወቅት ከማረፊያው አስፋልት ውጪ የመውጣት እክል ገጥሞት እንደነበር ይታወሳል።

ሌላው የመንገደኞች አውሮፕላን በተመሳሳይ በአርባ ምንጭ አውሮፓላን ማረፊያ ከማረፊያ መስመሩ (ራንዌይ) የመውጣት እክል ገጥሞት እንደነበር ተስምቷል።

በአጠቃላይ በአንድ ዓመት 4 የደኅንነት እክሎች የተመዘገቡ መሆኑን ጋዜጣው ምንጮቹን ዋቢ በማድረግ ጠቁሟል።

ከሀዋሳ ወደ አዲስ አበባ ከተማ ሲበር የነበረውን ጨምሮ እክል ያጋጠማቸው አውሮፕላኖች ' #Q400 ' በመባል የሚታወቁት አየር መንገዱ በአገር ውስጥ እና ወደ ጎረቤት አገሮች ለሚደረጉ በረራዎች የሚገለገልባቸው ናቸው።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ካሉት 178 አውሮፕላኖች መካከል 33 የሚሆኑት Q400 በመባል የሚታወቁት ለመካከለኛ ርቀት የሚጠቀምባቸው አውሮፕላኖች ናቸው። #ሪፖርተር

@tikvahethiopia
#AddisAbaba⛽️

በአዲስ አበባ የሚታየው የነዳጅ እጥረት በቀጣይ ቀናት እንደሚፈታ የኢትዮጵያ የነዳጅ አቅራቢዎች ድርጅት አሳውቋል።

የነዳጅ እጥረት በከተማዋ መከሰቱን የገለጸው ድርጅቱ " እጥረቱ ያጋጠመው በዒድ አል አድሃ አረፋ በዓል ምክንያት እሑድ ሰኔ 9 በማግሥቱ ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓ/ም ነዳጅ ከጂቡቲ ባለመጫኑ ነው " ብሏል።

የነዳጅ ማጓጓዝ ሒደቱ አምስት እና ስድስት ቀናትን የሚወስድ መሆኑንና አሁን የሚስተዋለው እጥረት በመጪዎቹ ቀናት እንደሚፈታ አሳውቋል።

ከሱሉልታ መጠባበቂያ ቤንዚን ከአዋሽ መጠባበቂያ ደግሞ ናፍጣ እየተጓጓዘ መሆኑንም በማመልከት የነዳጅ ችግሩ በእርጠኝነት በ2 ቀናት እንደሚፈታ ተናግሯል።

በየተለያዩ የነዳጅ ማደያዎች ላይ ከሚታየው የነዳጅ እጥረት ባለፈ ማደያዎች ነዳጅን ከተጠቃሚዎች እንደሚደብቁ አሽከርካሪዎች ለሪፖርተር በሰጡት ቃል ገልጸዋል፡፡

ሕገወጥ በሆነ መንገድ በውኃ ፕላስቲኮች ጭምር የሚሸጡ መኖራቸውንም ተናግረዋል፡፡

በዚህም ምክንያት ባለፉት ሳምንታት በመዲናዋ ነዳጅ ለመቅዳት የሚጠብቁ ረዣዥም የተሽከርካሪ ሠልፎች መታየታቸውንና አሁንም እጥረቱ እንዳለ አክለዋል፡፡ #ሪፖርተር

@tikvahethiopia