TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሞስኮ

የሩስያ ፖሊስ በዋና ከተማዋ ተቃውሞ የወጡ ከአንድ ሺ በላይ ሰልፈኞችን ማሰሩ ተሰማ። ሩስያ ለምርጫ መወዳደደር የሚያበቃቸውን ፊርማ አላሰባሰቡም ስትል ተቃዋሚ ተወዳዳሪዎችን ከምርጫው ማገዷ ይታወቃል፡፡ ይህን ተከትሎም በሞስኮ ከተማ ከፍተኛ ቁጥር ያለው ነዋሪ ለተቃውሞ ሰልፍ መውጣቱን ቢቢሲ አስነብቧል፡፡

ነገሩ ያልጣመው የሩስያ ፖሊሲም ተቃዋሚ ሰልፈኞችን አንዲበተኑ አድርጓል ይላል ዘገባው፡፡ ለምን ይታገዳሉ ሲሉ ሰልፍ ከወጡት መካከልም ፖሊስ ከአንድ ሺ በላይ ማሰሩንም ቢቢሲ ጨምሮ አስነብቧል፡፡ ተፎካካሪዎቹ ለምርጫ የማያበቃቸውን ፊርማ ስላልሰበሰቡ ሳይሆን ፖለቲካ ትርፍ ለማግኘት ሲባል ነው ክምርጫው እንዲወጡ የተደረገው ሲሉ ሰልፈኞቹ ተቃውሟቸውን አሰምተዋል፡፡

ሰልፉን ለመበተን ፖሊስ የሄደበት መንገድ በጣም አደገኛ አገሪቱን ወደ ችግር የሚወስዳት እንደሆነ የቢቢሲ ዘገባ ያመለክታል፡፡ ሩስያ እኤአ መስከረም ስምንት 2019 የምታካሂደውን ምርጫ ተከትሎ ጥቂት ከምርጫው የታገዱ ተቃዋሚ ተወዳዳሪዎችን ማሰሯ ታውቋል፡፡ እስካሁንም 30 ተፎካካሪዎች በቂ ፊርማ ባለማሰባሰባቸው ከምርጫው ታግደዋል ይላል የቢቢሲ ዘገባ፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#RUSSIA

ሩሲያ በአንድ ቀን ብቻ 9,623 ሰዎች በኮቪድ-19 መያዛቸው ተረጋገጠ። አብዛኞቹ በዋና ከተማዋ #ሞስኮ የሚኖሩ ናቸው። ይህ ቁጥር ወረርሽኙ ሩሲያ ከደረሰ በኋላ ከተመዘገቡት ሁሉ ከፍተኛው ነው።

በሌላ በኩል ባለፉት 24 ሰዓታት 57 ሰዎች ሕይወታቸውን አጥተዋል። በመላ አገሪቱ ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ የሞቱ ሰዎች ቁጥር ወደ 1,222 ማሻቀቡን ወረርሽኙን ለመቆጣጠር የተቋቋመው ኮሚቴ አስታውቋል።

የሞስኮ ከተማ ከንቲባ የሆኑት ሰርጌይ ሶብያኒን የከተማው ነዋሪዎች ራሳቸውን በመኖሪያ ቤታቸው ለይተው እንዲያቆዩ ተማፅነዋል።

በኮሮና ቫይረስ በጽኑ የታመሙ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መሆኑን የተናገሩት ከንቲባው እጅግ የከፋ ደረጃ አለመድረሱን ገልጸዋል። ሁኔታው ከከፋ በሞስኮ ከተማ ለመንቀሳቀስ የሚሰጥ ፈቃድ ሊቀነስ እንደሚችልም ከንቲባው ገልጸዋል።

በሞስኮ ከተማ ነዋሪዎች ከመንግሥት ልዩ ፈቃድ ካላገኙ በቀር ከቤታቸው መውጣት የሚችሉት ዕቃ ለመሸመት፣ ውሾቻቸውን ለማንሸራሸር እና ቆሻሻ ለመጣል ብቻ ነው።

#DW
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopi
#ሞስኮ

ዛሬ አርብ ታጣቂዎች በሩስያ ፣ ሞስኮ ወደሚገኝ ህዝብ ወዳለበት ትልቅ የሙዚቃ ኮንሰርት አዳራሽ በመግባት አውቶማቲክ የጦር መሳሪያ በመተኮስ በርካታ ሰዎችን መግደላቸው ተሰምቷል።

የአካል ጉዳት የደረሰባቸውም አሉ።

አንዳንድ ሪፖርቶች እስካሁን ድረስ ባለው በትንሹ 40 ሰዎች መገደላቸውን እና ከ100 በላይ ሰዎች መቁሰላቸውን ጠቁመዋል።

በአዳራሹ ውስጥ ሰዎች ተሰባስበው የነበረው ለአንድ የሙዚቃ ድግስ ነበር።

ታጣቂዎቹ ቦንብም ሲወረውሩ ነበር የተባለ ሲሆን አዳራሹ ያለበት ህንፃ በእሳት ሲያያዝ ታይቷል።

የሩሲያ ሀገር ውስጥ ስለላ አገልግሎት ከጥቃቱ በኋላ #ሞት እና #የአካል_ጉዳት መድረሱን አረጋግጧል ፤ የሟቾች ቁጥርን ግን አልገለጸም።

የሩስያ ጤና ሚኒስቴር የተጎዱ ሰዎች ሆስፒታል መግባታቸውን አሳውቋል።

በስፍራው የነበረ አንድ ጋዜጠኛ ፥ ታጣቂዎቹ አውቶማቲክ መሳሪያ እየተኮሱ መግባታቸውን ፤ የእጅ ቦምብ / ተቀጣጣይ ቦምብ ሲወረውሩም እንደነበር ገልጿል።

ጋዜጠኛው ፤ " በአዳራሹ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ለ15 እና 20 ደቂቃዎች እራሳቸውን ከጥይት ለመከላከል ወለል ላይ ተኝንተው እንደነበር በኃላ ሁኔታው ጋብ ሲል እና የፀጥታ ኃይል ሲመጣ መውጣታቸውን አስረድቷል።

የሩስያ ዕንባ ጠባቂ ተቋም ድርጊቱን " የሽብር ተግባር " ብሎታል።

እስካሁን ለጥቃቱ ኃላፊነት የወሰደ ወይም ሩስያ ይህ አካል ነው ያለችው የለም።

ቪድዮ ፦ ከሩስያ የማህበራዊ ሚዲያዎች

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Video
#Update

ትላንት ታጣቂዎች በሩስያ ፣ #ሞስኮ በሚገኘው የክሮከስ አዳራሽ የሙዚቃ ዝግጅት ለመታደም በተሰበሰቡ በርካታ ሰዎች ላይ በከፈቱት ተኩስ የተገደሉ ሰዎች 115 የደረሱ ሲሆን 100 ሰዎች መቁሰላቸውን የሩሲያ የደኅንነት አገልግሎት አስታውቋል።

ከተገደሉት ውስጥ ህፃናትም እንደሚገኙበት ተነግሯል።

4 ታጣቂዎችን ጨምሮ 11 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የሩስያ ባለስልጣናት አሳውቀዋል።

የሩሲያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተፈፀመውን ድርጊት " #የሽብር_ጥቃት_ነው " ሲል ጠርቶ አውግዟል።

ለጥቃቱ #IS ኃላፊነቱን መውሰዱን በበይነ መረብ የወጣ አንድ ያልተረጋገጠ መግለጫ አመልክቷል።

የአሜሪካ ባለሥልጣናት ፤ IS ሩሲያን ለማጥቃት እንደሚፈልግ የሚያሳይ መረጃ ማግኘታቸውን ተናግረዋል።

አሜሪካ በሞስኮ ከተማ " ሕዝብ በሚበዛባቸው ስፍራዎች " ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ሊደርስ እንደሚችል በዚህ ወር መጀመሪያ ላይ ሩሲያን አስጠንቅቃ ነበር።

ከ2 ሳምንታት በፊት በሩሲያ የሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ዜጎቹ በርካታ ሰዎች በሚሰባሰቡባቸው ሕዝባዊ ስፍራዎች እንዳይሄዱ ማስጠንቀቂያ አስተላልፎ ነበር።

በማስጠንቀቂያው ላይ " ጽንፈኞች በሞስኮ ሕዝብ በሚሰባሰቡባቸው ስፍራዎችን (የሙዚቃ ኮንሰርትን ጨምሮ) የጥቃት ዒላማ ለማድረግ ዕቅድ አላቸው " የሚል ሪፖርትን እየተከታተልኩ ነው ሲል ገልጾ ነበር።

ኤምባሲው ትላንት ምሽት ባወጣው መግለጫ ጥቃቱ ወደደረሰበት ስፍራ ዜጎቹ ዝር እንዳይሉ ምክር ማስተላለፉን ቢቢሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia