TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Update አራት ኪሎ በግንባታ ላይ ያለ ህንጻ #ተደርምሶ በሰዎች ላይ ጉዳት ደረሰ።

በተለምዶ አራት ኪሎ እሪ በከንቱ በሚባለው አካባቢ በግንባታ ላይ ያለ ህንጻ መጠነኛ የመደርመስ አደጋ ደርሶበት በሰራተኞች ላይ #ጉዳት ደረሰ።

ዛሬ ከሰዓት በኋላ በደረሰው በዚሁ አደጋ በግንባታ ስራው ላይ በነበሩ #ስድስት ሰራተኞች ላይ ጉዳት ደርሶ ወደሆስፒትል መወሰዳቸው ታውቋል።

የአካባቢው ፓሊሶች ለኢትዮጵያ ፕሬሥ ድርጅት እንደገለጹት በአደጋው ህይወቱ ያለፈ ሰው የለም። የአደጋውም መንስኤ እየተጣራ ነው።

ምንጭ :- የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
ፎቶ እና ቪድዮ፦ TikvahEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሳዛኝ ዜና‼️

በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ ከተማ ኮተቤ ዩኒ ቨርሲቲ አካባቢ በግንባታ ላይ የነበረ #ድልድይ አርማታ #ተደርምሶ 12 ሰዎች #ጉዳት ደረሰባቸው፡፡ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ወደ #ሆስፒታል ተወስደዋል። በአደጋው #ህይወቱ ያለፈ ሰው ስለመኖሩ #የታወቀ ነገር የለም።

Via EBC
ፎቶ፦m & jes(tikvahethiopia)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update በአዲስ አበባ ከተማ ኮተቤ ዩኒቨርስቲ አካባቢ በግንባታ ላይ የነበረ ድልድይ #ተደርምሶ በሰዎች ላይ ጉዳት ደረሰ።

via etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የትምህርት ቤት መፀዳጃ ቤት #ተደርምሶ የ3 ታዳጊ ተማሪዎች ህይወት ተቀጠፈ።

ዛሬ በትግራይ ምስራቃዊ ዞን የጉሎመኻዳ ወረዳ በሚገኘው " መረታ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት " መፀዳጃ ቤት ተደርምሶ 3 ተማሪዎች ወዲያው ህይወታቸው አልፏል።

የመደርመስ አደጋው በእረፍት ጊዜ ከረፋዱ በ4:00 ሰአት የደረሰ ሲሆን የሴቶች የጋራ መፃዳጃ ቤት ሲጠቀሙ ከነበሩ 6 እንስት ተማሪዎች 3ቱ ወድያውኑ ሲሞቱ 3ቱ ቆስለው ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል።

ትምህርት ቤቱ ፤ ለመፀዳጃ ቤቱ መደርመስ መንስኤው በአከባቢው የዘነበ ከባድ ዝናብ እና መፀዳጃ ቤቱ ለረጅም ጊዜ ማገልገሉ እንደሆነ ገልጿል።

አደጋው በት/ቤቱ ተማሪዎች ፣ መምህራን እና ወላጆች ላይ ከፍተኛ ድንጋጤና ሃዘን መፍጠሩን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ያገኘው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia