#Update አራት ኪሎ በግንባታ ላይ ያለ ህንጻ #ተደርምሶ በሰዎች ላይ ጉዳት ደረሰ።

በተለምዶ አራት ኪሎ እሪ በከንቱ በሚባለው አካባቢ በግንባታ ላይ ያለ ህንጻ መጠነኛ የመደርመስ አደጋ ደርሶበት በሰራተኞች ላይ #ጉዳት ደረሰ።

ዛሬ ከሰዓት በኋላ በደረሰው በዚሁ አደጋ በግንባታ ስራው ላይ በነበሩ #ስድስት ሰራተኞች ላይ ጉዳት ደርሶ ወደሆስፒትል መወሰዳቸው ታውቋል።

የአካባቢው ፓሊሶች ለኢትዮጵያ ፕሬሥ ድርጅት እንደገለጹት በአደጋው ህይወቱ ያለፈ ሰው የለም። የአደጋውም መንስኤ እየተጣራ ነው።

ምንጭ :- የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
ፎቶ እና ቪድዮ፦ TikvahEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia