TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የውሸት መረጃ⬆️በዛሬው ዕለት በአምቦ በነበረው የተማሪዎች ምርቃት ፕሮግራም ላይ ቦምብ ሊጥል ሲል እጅ ከፍንጅ ተያዘ የተባለው ወጣት ወሬ ሀሰት ነው፡፡ ልጁ የተያዘው በኪስ አውላቂነት ተጠርጥሮ መሆኑን #ጃዋር_መሀመድ በፌስቡክ ገፁ ላይ አስፍሯል።

•ወዳጆቼ በተቻለ መጠን የሚደርሱንን መረጃዎች እንደወረዱ ከመቀበል፣ ሼር ከማድረግ፣ ሰዎች ላይ ከመፍረድ፣ ይልቅ ቀድመን እውነታውን ልናጣራ ይገባል፡፡

*አንዳንዶች የልጁ ብሄር ይሄ ነው እያሉም ሲፅፉ ነበር። ይህ አግባብነት የለውም። እባካችሁ ለጅቦች ራሳችንን አሳልፈን አንስጥ። ያጠፉ ሰዎችን መፈረጅ ምንም ማለት አይደልም፣ ያጠፉ ሰዎችን መውቀስ ምንም አይደልም፣ ስለ አንድ ቡድን ጥፋት እና ክፉ ስራ መናገር ችግር የለውም ስህተቱ በነዛ ሰበብ ሁሉንም ማጠቃለሉ ላይ ነው። ይህንን ፈጣሪም አይወደውም። ሰዎች ወደው ባላመጡት ብሄር እና ዘር ሊሰቃዩ በፍፁም አይገባም።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!
ከዶክተር አብይ ጋር ወደፊት!
#TEAMLEMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጥንቃቄ⬆️አዲስ አበባ ከተማን ፍፁም የብጥብጥ አውድማ ለማስመሰል በርካታ ሰዎች በፌስቡክ እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ ከነዚህም መሀል በአክቲቪስት #ጃዋር_መሀመድ ስም #የሀሰት ገፅ ተከፍቶ ህዝቡን ለማበጣበጥ የሚሰሩ ሰዎች ስላሉ ጥንቃቄ ይደረግ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ሻሸመኔ⬇️

በሻሸመኔ ከተማ ሰው በመግደልና ዘቅዝቆ በመስቀል ወንጀል የተጠረጠሩ 14 ግለሰቦች በቁጥጥር ስል አውሎ በስድስቱ ላይ #ክስ እንደሚመሰርት የከተማው ፓሊስ መምሪያ አስታወቀ።

ግለሰቦቹ ነሃሴ 6 ቀን 2010 ዓመተ ምህረት የኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ ዳይሬክተር አቶ #ጃዋር_መሀመድ አቀባበል ስነ ስርዓት ላይ ግርግር በመፍጠር አንድ ግለሰብን #በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሎ በመስቀል ወንጀል ጠርጠራቸውን የአቃቤ ህግ መዝገብ ይጠቁማል።

የከተማው ፓሊስ መምሪያ አዛዝ ኮማንደር መኮንን ታደሰ ለጣቢያችን እንዳሉት፥ ከተያዙት ተጠርጣሪዎች መካከል በስድስቱ ላይ አቃቤ ህግ ክስ ለመመስረት የሚያስችል በቂ ማስረጃ በማግኘቱ ክስ ለመመስረት መዘጋጀቱን  ተናግረዋል።

ተጠርጣሪዎቹ በዛሬው እለት በሻሸመኔ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፊት እንደሚቀርቡም አስታውቋል።

ነሃሴ 6 ቀን 2010 ዓመተ ምህረት በተፈጠረው ግርግርና ግፊያ የ3 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ የከተማው ፓሊስ ተሽከርካሪ ቃጠሎ እንደደረሰበት ይታወሳል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሰላ🔝አክቲቪስት #ጃዋር_መሀመድ በዛሬው ዕለት በአሰላ ከተማ (አሰላ ስታዲየም) ደማቅ አቀባበል ተደርጎለታል። ከከተማው ነዋሪዎችም የተለያዩ ስጦታዎች ተበርክቶለታል።

©JE(አሰላ TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አክቲቪስት #ጃዋር_መሀመድ በሰሞኑ የሀረር ጉዞ ከህዝብ ጋር ባደረገው ውይይት ከተናገረው በጥቂቱ የተተረጎመ…

(በዘሪሁን ገመቹ)

"ቄሮ ነኝ..ከዚህ በፊት ታግዬ ነበረ... ታስሬ ነበር ስለዚህ አሁን ደሞዜ ሊከፈለኝ ይገባል ብሎ #ዘረፋ ውስጥ የሚገባ..ስልጣን ይገባኛል ብሎ የሚያስፈራራ እሱ ቄሮ ሳይሆን ወያኔ ነው። መኖሪያውም ከሜቴክ ባለስልጣን ጋር ቃሊቲ ነው መሆን ያለበት። ለህዝባችን ነፃነት እንጂ #ለግል ኑሮአችን አልታገልንም። የታገልነውም #መስዋዕትነት የከፈልነውም #ህዝባችን ለምኖን ወይም አስገድዶን ሳይሆን በራሳችን ፍላጎት ነው። ስለሆነም ከ ህዝብ የተለየ ነገር ማግኘት አለብን ብላችሁ የመጠየቅ መብት የላችሁም። ወላጆችም ልጆቻችሁ ለከፈሉት መስዋዕትነት ከማመስገንና ተገቢውን ክብር ከመስጠት ባለፈ ከህግ ውጭ እንዲሆኑ #ፊት_አትስጧቸው...ካለበለዚያ #አሸባሪ ነው የሚሆኑባችሁ። ቄሮ ማንኛውንም መኪና ኮንትሮባንድ የጫነ ነው ብሎ ሲጠረጥር ለፓሊስ እና ለህግ አካላት #መጠቆም እንጂ #የመፈተሽ_ስልጣን_የለውም። እንደዛ ማድረግ በቄሮ ስም ለሚነግዱ #ዘራፊዎች ሁኔታዎችን እያመቻቸሁላቸው ስለሆነ አካሄዱ መስተካከል አለበት። ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመት መንግስታችን አንድ ነው ። አሁን ስልጣን ላይ ያለው። አዲስ አበባ ተመዝግቦ መጥቶ ፅ/ቤት የሚከፍት ማንኛውንም ፓርቲ ተቀበሉት፣ቢሮውን እንዲከፍት አግዙት፣ ኑሯችሁን እንዴት ለማሻሻል እንዳሠበ ቁጭ ብላችሁ ስሙ..ከዛ ቀኑ ሲደርስ የተሻለውን #ትመርጣላችሁ..ካዛ ውጭ ግን ዛሬ አዲስ:አበባ ተቀምጦ #ፓለቲካ_እያወራ እዚህ መሳሪያ #እንድትታኮሱ የሚጠይቃችሁ ካለ እሱ #ጠላታችሁ ስለሆነ ከተማችሁ ሳይገባ በሩቁ ተከላከሉት። የነፃነትን #መጠጥ በልኩ ጠጥቶ #መደሰት አግባብ ነው…ተገኘ ተብሎ ከመጠን በላይ በመጠጣት መስከር ግን ጥፋት ነው። ሪፎርሙ #ከከሸፈ በፊት ወደነበርንበት አንመለስም...እንደሱማሌ እና ዪጎዝላቪያ #በመፈረካከስ ተጫርሰን #እናልቃለን።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ማዕከላዊ እስር ቤት⬆️

"ዛሬ ጠዋት ጀምሮ እስከ ረፋድ ድረስ በርካታ ሰዎች ማዕከላዊ እስር ቤትን እየጎበኙ የሚገኝ ሲሆን ከነዚህም መካከል አቶ #ጃዋር_መሀመድ የተገኙ ሲሆን ኦቦ #በቀለ_ገርባ ለOMN ሚዲያ ሠዎች እና በቦታው ለተገኙ ጎብኚዎች ስለ ቦታውና በዚያ ስላሳለፉአቸው አስከፊ ጊዜያት ገለፃ ሲያደርጉና ሲያስጎበኙ ነበር።"

📸በርካታ የTIKVAH-ETH የቤተሰብ አባላት ማዕከላዊን በመጎብኘት የሚያዩትን ነገር በፎቶ እያስቀሩ እየላኩን ይገኛሉ!


Via #Fasil/TIKVAH-ETH/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Breaking

"#ጃዋር_መሀመድ በሚቀጥለው ምርጫ እንደሚሳተፍ/እንደሚወዳደር ከደቂቃዎች በፊት ሰምቻለሁ።" ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት/Associated Press/

@tsegabwolde @tikvahethiopia