TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አክቲቪስት #ጃዋር_መሀመድ በሰሞኑ የሀረር ጉዞ ከህዝብ ጋር ባደረገው ውይይት ከተናገረው በጥቂቱ የተተረጎመ…

(በዘሪሁን ገመቹ)

"ቄሮ ነኝ..ከዚህ በፊት ታግዬ ነበረ... ታስሬ ነበር ስለዚህ አሁን ደሞዜ ሊከፈለኝ ይገባል ብሎ #ዘረፋ ውስጥ የሚገባ..ስልጣን ይገባኛል ብሎ የሚያስፈራራ እሱ ቄሮ ሳይሆን ወያኔ ነው። መኖሪያውም ከሜቴክ ባለስልጣን ጋር ቃሊቲ ነው መሆን ያለበት። ለህዝባችን ነፃነት እንጂ #ለግል ኑሮአችን አልታገልንም። የታገልነውም #መስዋዕትነት የከፈልነውም #ህዝባችን ለምኖን ወይም አስገድዶን ሳይሆን በራሳችን ፍላጎት ነው። ስለሆነም ከ ህዝብ የተለየ ነገር ማግኘት አለብን ብላችሁ የመጠየቅ መብት የላችሁም። ወላጆችም ልጆቻችሁ ለከፈሉት መስዋዕትነት ከማመስገንና ተገቢውን ክብር ከመስጠት ባለፈ ከህግ ውጭ እንዲሆኑ #ፊት_አትስጧቸው...ካለበለዚያ #አሸባሪ ነው የሚሆኑባችሁ። ቄሮ ማንኛውንም መኪና ኮንትሮባንድ የጫነ ነው ብሎ ሲጠረጥር ለፓሊስ እና ለህግ አካላት #መጠቆም እንጂ #የመፈተሽ_ስልጣን_የለውም። እንደዛ ማድረግ በቄሮ ስም ለሚነግዱ #ዘራፊዎች ሁኔታዎችን እያመቻቸሁላቸው ስለሆነ አካሄዱ መስተካከል አለበት። ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመት መንግስታችን አንድ ነው ። አሁን ስልጣን ላይ ያለው። አዲስ አበባ ተመዝግቦ መጥቶ ፅ/ቤት የሚከፍት ማንኛውንም ፓርቲ ተቀበሉት፣ቢሮውን እንዲከፍት አግዙት፣ ኑሯችሁን እንዴት ለማሻሻል እንዳሠበ ቁጭ ብላችሁ ስሙ..ከዛ ቀኑ ሲደርስ የተሻለውን #ትመርጣላችሁ..ካዛ ውጭ ግን ዛሬ አዲስ:አበባ ተቀምጦ #ፓለቲካ_እያወራ እዚህ መሳሪያ #እንድትታኮሱ የሚጠይቃችሁ ካለ እሱ #ጠላታችሁ ስለሆነ ከተማችሁ ሳይገባ በሩቁ ተከላከሉት። የነፃነትን #መጠጥ በልኩ ጠጥቶ #መደሰት አግባብ ነው…ተገኘ ተብሎ ከመጠን በላይ በመጠጣት መስከር ግን ጥፋት ነው። ሪፎርሙ #ከከሸፈ በፊት ወደነበርንበት አንመለስም...እንደሱማሌ እና ዪጎዝላቪያ #በመፈረካከስ ተጫርሰን #እናልቃለን።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia