TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ በመግለጫቸው " 5 ትምህርት ቤቶች ያስፈተኗቸው ተማሪዎች ሙሉ ለሙሉ አሳልፈዋል፡፡ " ብለዋል። ሌሎች 5 ትምህርት ቤቶች ድግሞ ካስፈተኗቸው ውስጥ 95 ከመቶ ተማሪዎቻቸውን እንዳሳለፉ ገልጸዋል። ከፍተኛ አፈጻጻም ያሳዩ አስር ትምህርት ቤቶች (በደረጃ)፦ 1. አዲስ አለማየሁ አዳሪ ትምህርት ቤት (ደብረማርቆስ) 2. ደሴ አዳሪ ትምህርት ቤት 3. ባህርዳር ስቴም ትምህርት…
#አማራ

በ2015 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች ሙሉ በሙ ካሳለፉ 5 ትምህርት ቤቶች 3ቱ በአማራ ክልል የሚገኙ ናቸው።

ሶስቱ ትምህርት ቤቶች ፦
- ደሴ ልዩ የአዳሪ ትምህርት ቤት፣
- ሐዲስ ዓለማየሁ ልዩ የአደሪ ትምህርት ቤት
- ባሕር ዳር ስቴም ትምህርት ቤት ናቸው።

በሀገር አቀፍ ደረጃ በማኅበራዊ ሳይንስ ከፍተኛውን ውጤት ያስመዘገበው ተማሪም የሐዲስ ዓለማየሁ አዳሪ ትምህርት ቤት ተማሪ ነው።

እንደ አማራ ክልል ትምህርት ቢሮ መረጃ በሐዲስ ዓለማየሁ አዳሪ ትምህርት ቤት እና በደሴ ልዩ የአዳሪ ትምህርት ቤት በድምሩ 32 ተማሪዎች 600 እና ከዚያ በላይ ውጤት አስመዝግበዋል፡፡

አማራ ክልል በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ክልሎች ባለፉት አመታት በሰላም እጦት ክፉኛ እየተጎዳ ቢሆንም መሰል ትልልቅ ውጤቶች መመዝገባቸው ለቀጣይ ተስፋ ሠጪ ነው ተብሏል።

የአማራ ክልል ተማሪዎች የጥይት ድምጽ እየሰሙ ተምረዋል፤ የጥይት ድምጽ እየሰሙ ተፈትነዋል፡፡ አብዘኛዎቹ የክልሉ ተማሪዎች በጦርነት ምክንያት በወደሙ እና በተዘረፉ ትምህርት ቤቶች ለመማር ተገድደዋል፡፡ በፈተና ወቅት በተፈጠረ አለመረጋጋት ፈተናውን አቋርጠው የወጡ ተማሪዎችም ነበሩ።

ይህ ሁሉ ቢሆንም በሀገር አቀፉ ፈተና የተገኘው ውጤት አጥጋቢ ባይሆንም፣ ሰላም ከተረጋገጠ፣ የተረጋጋ እና የተስተካከለ ትምህርት መሥጠት ከተቻለ ግን ተስፋ ሰጪ ውጤቶች ያሳየ እንደሆነ የክልሉ ትምህርት ቢሮ ገልጿል።

ቢሮው እንደ ሀገር የተዘመገበው ውጤት ዝቅተኛ መሆኑን ገልጾ በትምርት ስርዓቱ ላይ በርካታ ስራ መስራት ያስፈልጋል ብሏል።

ከታች ጀምሮ መሥራት ከተቻለ ውጤት ማምጣት የሚችሉ ልጆች አሉንም ሲል ገልጿል።

በአማራ ክልል ጦርነት እና ግጭት በፈጠሩት ሥነ ልቦናዊ ጫና ውስጥ ሆነው የተፈተኑ ተማሪዎች መኖራቸው ያስታወሰው የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ተማሪዎች ጫናውን ተቋቁመው ያስመዘገቡት ውጤት ጥሩ መሆኑን አመልክቷል።

ወደ ፊት መሥራት ከተቻለ ተስፋ የታየበት መሆኑንም ገልጿል።

ቢሮው በአዳሪ ትምህርት ቤቶች ላይ እየተመዘገበ ያለው ውጤት ትምህርት ሰጭ ነው ያለ ሲሆን የተሻለ ዜጋ ለማፍራት አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ማስፋት ያስፈጋል ብሏል። በክልሉ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ለማስፋፋት እየተሰራ መሆኑንም አሳውቋል። #AMC

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" እውነቱን ለመናገር ነዋሪዎቹ እርቧቸዋል። እያለቀሱ ነው የተናገሩት። ድረሱልን እያሉ ነው " - አቶ ምሕረት መላኩ የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር  የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋሰትና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምህረት መላኩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል የአማራ ክልል መንግሥት ድርቅ በተከሰተባቸው ቦታዎች የዕለት ድጋፍ ለማድረስ ቢስማማም በጸጥታ ችግር መድረስ እንዳልቻለ ገልጸዋል። ኃላፊው ከ1.2…
#አማራ

• " ከ13,000 በላይ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው የከፋ ችግር ውስጥ ናቸው " - የዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ፅ/ቤት

• " በሰሃላ ወረዳ 94 በመቶ ነፍሰጡሮችና የሚያጠቡ እናቶች፣ 45 በመቶ ከአምስት ዓመት በታች ሕጻናት በምግብ እጥረት ተጎድተዋል " - የዞኑ ጤና መምሪያ ቢሮ

በአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን በአበርገሌና ፃግብጅ ወረዳዎች ከሰሜኑ ጦርነት ጀምሮ ተፈናቅለው ከነበሩ ከ79,000 በላይ ነዋሪዎች መካከል እስካሁን (ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ) ወደየቄያቸው መመለስ ያልቻሉ ሰዎች በከፋ ችግር ውስጥ መሆናቸውን የዞኑ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና መምሪያ ጽሕፈት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የዞኑ አደጋ መከላከልና ቅድመ ማስጠንቀቂያ ቡድን መሪ ወ/ሮ ዝናሽ ወርቁ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ማብራሪያ፣ " ከ13,000 በላይ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው የከፋ ችግር ውስጥ ናቸው " ብለዋል።

ተፈናቃዮቹ ወደቤታቸው ያልተመለሱበትን ምክንያት ሲያብራሩም ወ/ሮ ዝናሽ፣ " በፃግብጅ ወረዳ 5፣ በአበርገሌ ወረዳ 12 ቀበሌዎች ከሕወሓት ታጣቂዎች ነጻ ስላልወጡ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

አክለውም፣ በዚህም ምክንያት በአበርገሌ ወረዳ 5,087፣ በፃግብጅ ወረዳ 8,233 ተፈንቃዮች በዞኑ ዋና ከተማ በኅብረተሰቡ ተጠልለው እንደሚገኙ አስረድተው፣ " ወይ ሰላም ሆኖ ወደ ቤታቸው አልገቡ ወይ ድጋፍ እየተደረገ በመጠለያ ጣቢያ በመንግሥት ውስጥ አልሆኑም፣ ችግራቸውን ሙሉ ለሙሉ ቀርፈናል ብለን አናስብም። በሚያሳዝን ደረጃ ላይ ነው ያለት " ሲሉ ገልጸዋል።

በዞኑ የተከሰተው ድርቅ በተመለከተ ነዋሪዎች ያሉበትን ሁኔታ እንዲያብራሩ ሲጠየቁም፣ ረሃቡ እየበረታባቸው መሆኑን፣ የጸጥታ ችግር፣ ድርቅ ባለባቸው ወረዳዎች ወረርሽኝ እንዳለም አስረድተዋል።

ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ተመሳሳይ ጥያቄ የቀረበላቸው የዞኑ ጤና መምሪያ ቢሮ ኃላፊ ተወካይ አቶ ሙሉዓለም ወንድሙ በበኩላቸው፣ " ድርቁ ያስከተለውን ጉዳት በተመለከተ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጥናት እያጥኑ ነው " ብለዋል።

አክለውም፣ እስካሁን ባለው ጥናት ግኝት መሠረት ብቻ፣ " በሰሃላ ወረዳ 94 በመቶ ነፍሰጡሮችና የሚያጠቡ እናቶች፣ 45 በመቶ ከአምስት ዓመት በታች ሕጻናት በምግብ እጥረት ተጎድተዋል " ብለዋል።

የሕጻናቱ በምግብ እጥረት መጎዳት ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ በጥናት መረጋገጡን ሲያስረዱም አቶ ሙሉዓለም፣ " ቢያንስ የሚጠበቀው በጣም ከፍተኛ ቢሆን 15 በመቶ ነበር። ይሄ ግን 30 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። ይህን የመሰለ አስከፊ ጉዳት ነው ያለው " ሲሉ ገልጸዋል።

" የጸጥታ ችግር ባለባቸው ወረዳዎችም የመድኃኒት እጥረት አለ " ያሉት ተወካዩ፣ " ከጎንደር የመድኃኒት አቅርቦት ድርጅት ነው መድኃኒት የሚቀርብ የነበረው፣ ካለው የጽጥታ ችግር ጋር ተያይዞ ከድርቁ ጋር ለሚከሰቱ ወረርሽኞችም ሆነ ከድርቁ በፊት ለተከሰተው የወባ በሽታ ወረርሽኝ መድኃኒት መቅረብ አልቻለም " ብለዋል።

የተከዜ ድልድይ መሰበሩን ተከትሎ በሰሃላ ወረዳ ላሉ ሰዎች የምግብ ድጋፍ ማድረስም እንዳልተቻለ ገልጸው፣ " በሚገርም ሁኔታ እንደዚህ አይነት አስቸጋሪ ወረዳ በኢትዮጵያ ውስጥ አለ ብዬ አላስብም " ሲሉም ተናግረዋል።

በመጨረሻም፣ መንግሥት፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

ዘገባው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
እርዳታ ለሚፈልጉ ወገኖች ምን ያህል ድጋፍ እየተደረገ ነው ? በኦሮሚያ ክልል በወለጋ ዞን፦ - ኪረሙ፤ - ሁሙሩ እና አጋምሳ፣ - ቤጊ፤ - ጊዳሚ፤ - ቆንዳላ፤ - ሆሮ ሊሙ በተሰኙ ቦታዎች፣ በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር፣ ዋግኽምራ ብሔረሰብ ዞን አስተዳደር እንዲሁም በትግራይና በአፋር ክልሎች የተከሰተውን ድርቅ ተከትሎ ዜጎች ለከፍተኛ ረሃብ መጋለጣቸው፣ በሰዎችና በእንስሳት ላይ ሕልፈተ ሕይወት መድረሱ…
#አማራ #ዋግኽምራ

" ሰው ሁሉ ግራ ተጋብቶ የሚበላውንም አጥቶ ነው ያለው፤ ታይቶም ተሰምቶ የማይታወቅ በጣም የሚዘገንን ድርቅ ነው ያጋጠመን  " - የዋግኽምራ ምሽሃ ቀበሌ ነዋሪ

በአማራ ክልል፣ ዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ፤ ሰሀላ ሰየትም ወረዳ ውስጥ ስላለው አስከፊ የድርቅ ሁኔታ በተደጋጋሚ መነገሩ ይታወሳል።

በአካባቢው ስለሚገኙ ዜጎች ሁኔታ ፣ የሰብዓዊ ድጋፍ ጉዳይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተደጋጋሚ መልዕክቶችን ማጋራቱም ይታወሳል።

አሁንም ችግሩ በከፋ ሁኔታ ላይ ሲሆን በርካታ ወገኖች በድርቁ ችግር ውስጥ ይገኛሉ። ወደ ሚሊዮን የሚጠጉ እንስሳትም መኖ ፍለጋ ወደ አጎራባች ወረዳዎች ተሰደዋል።

በዚሁ አካባቢ ስላለው አስከፊ የድርቅ ሁኔታ ከሰሞኑን ቃላቸውን ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ የሰጡ ወገኖች " ቀጣይ ኑሯችን ተስፋም የለው " ብለዋል።

አርሶ አደር ደሴ ፈንቴ ፤ የምሸሃ ቀበሌ ነዋሪ ሲሆኑ ባለፈው ክረምት በቀበሌው ምንም አይነት ዝናብ ባለመጣሉ እርሳቸውም ሆኑ ከብቶቻቸው የሚበሉት እንደሌላቸው ተናግረዋል።

በድርቁ ምክንያት የጎረቤቶቻቸው ህይወት እንዳለፈም የገለፁት አርሶ አደሩ ፤ የቤት እንስሳቶቻቸው በመሞታቸው ቀጣይ ኑሯቸው ተስፋ እንደሌለው ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ሌላው የ01 ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ነጋሽ ጎበዙ ፤ " 2015 ለ2016 ምንም አይነት ሳርም ሆነ ሌላ ነገር ያልበቀለበት ፤ ታይቶም ተሰምቶ የማይታወቅ በጣም የሚዘገንን ድርቅ ነው ያጋጠመን። ሰው ሁሉ ግራ ተጋብቶ የሚበላው አጥቶ እስሳቱንም ትቶ፣ ሰውም በየቦታው እየሞተ፣ እንስሳቱም እየሞቱ በጣም የከፋ ሁኔታ ላይ ነው ደርሰን ያለነው። በጣም በጣም አስከፊ ነው። " ብለዋል።

እሳቸው የነበራቸው በርካታ ከብቶች እና ፍየሎች በረሃብ ሞተውባቸው እንዳለቁ ተናግረው ፤ " የከብቱስ ይሁን እሳሳት ናቸውና እጅግ የሚያሳዝነው የሰዎች ህይወት እያለፈ መሆኑ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

በዚህ ሳምንት እሳቸው ባሉበት አካባቢ 2 ህፃናት እና 3 አዛውንቶች በአጠቃላይ 5 ሰዎች ህይወታቸው እንዳለፈ ተናግረዋል።

ከሰሞኑን በዋግኽምራ ድርቅ ያስከተለውን ጉዳት ከመንግስታዊና 18 ከሚደርሱ መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት የተውጣጣ የባለሞያዎች ቡድን በአካል ተገኝቶ ጥናት ማድረጉ ተነግሯል።

በዚህም ጥናት በሰው እና እስሳት ሞት ላይ ዳሰሳ ተደርጓል።

ምንም እንኳን የክልሉ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ኮሚሽን ለድርቅ ተጎጂዎች በሚል የዕለት እርዳታ እንደላከ ቢያሳውቅም የዋግኽምራ አደጋ መከላከል እና ምግብ ዋስትና ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ድጋፉ በቂ እንዳልሆነ አሳውቋል።

ያለው ችግር የእንስሳት መኖ እጥረት፣ የሰዎች ሰብዓዊ ድጋፍ እጥረት ...ሌሎችም ዘርፈ ብዙ ችግሮች እንደሆነ የገለፀው ፅ/ቤቱ " የክልሉ መንግስት 600 ኩንታል ስንዴ፣ ፌዴራል መንግስት 675 ኩንታል ስንዴ አቅርበዋል፣ ረጂ ድርጅቶች 42 ሚሊዮን ብር የሚሆን በካሽ የሚከፈል አቅርበዋል። አሁን ላይ ለአንድ ወር የሚሆን 25,834 አካባቢ ሰዎችን ሊያግዝ የሚችል ድጋፍ አግኝተናል ይህ ግን ካለው ችግር አንፃር በቂ አይደለም " ብሏል።

ተጨማሪ ድጋፍ ካልተደረገ ተጨማሪ ጥፋት ሊደርስ ይችላል ሲልም ፅ/ቤቱ መግለፁን ቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
#አማራ

በአማራ ክልል፤ ሰሜን ጎንደር ዞን ፤ የተከሰተውን አስከፊ ድርቅ ተከትሎ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጭ የመሆን ዕድላቸው ሰፊ መሆኑን የዞኑ አመራሮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

የዞኑ አደጋ መከላከልንና ምግብ ዋስችና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰላምይሁን ሙላት በገለጹት መሠረት፣ " ድርቅ ባለባቸው አካባቢዎች ወደ 105 የትምህርት ተቋማት ወደ 51 ሺሕ ለሚሆኑ ተማሪዎች ምገባ ይሰጥ ነበር " ብለዋል።

" ነገር ግን ከወራት በፊት 202 ሺሕ ዜጎች የቅድሚያ ቅድሚያ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ተብለው ተለይተው ነበር። አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ድጋፍ ተደራሽ እየተደረገ ያለው ቅድሚያ ለሚያስፈልገው የማኅበረሰብ ክፍል ነው" ያሉት  ኃላፊው፣ " ለተማሪዎች እገዛ ማድረግ ያስፈልጋል፣ ነገር ግን ድጋፍ ተጠናክሮ ካልቀጠለ ምግብ ካላገኙ ሊማሩ አይችሉም " ሲሉ አስረድተዋል።

አክለውም፣ " የትምህርት ተቋማት ችግር ላይ ነው ያሉት፣ ቁሳቁስ ያስፈልጋቸዋል። የጤና ተቋማት መድኃኒት ያስፈልጋቸዋል። እስከ 2017 የምርት ዘመን 452, 950 የሚሆኑ ዜጎች እርዳታ ያስፈልጋቸዋል። ለግብርናው ዘርፍም የማዳበሪያና የዘር ድጋፍ ያስፈልጋል " ብለዋል።

አቶ ሰላምይሁን ዞኑ ተደራራቢ ችግር እንዳለበት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ማብራሪያ፣ " በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ተፈናቅለው ከነበሩት ሰዎች መካከል ከ104 ሺሕ በላይ ዜጎችን ወደየቄያቸው መልስናል። ነገር ግን በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ ከትግራይና ከኦሮሚያ ክልሎች የመጡ ከ41 ሺሕ በላይ፣ ከሱዳን የተመለሱ ከ4ሺሕ በላይ፣ ከ20ሺሕ በላይ የኤርትራ ተፈናቃዮች በዞኑ አሉ። እነዚህ ከድርቁ ጋ በተያያዘ ችግሩን ክብደት የሰጡት ጉዳዮች ናቸው " ነው ያሉት።

የሰሜን ጎንደር ዞን ትምህርት መምሪያ ኃላፊ አቶ ክቡር አሰፋ በበኩላቸው፣ " በተለያዩ አካላት የተጀመሩ ድጋፎች አሉ፣ በዚህ ካልቀጠለ 51, 336 ተማሪዎች ትምህርት ያቋርጣሉ " ብለዋል።

" በሦስት ወረዳዎች ማለትም ጃንአሞራ፣ በየዳና ጠለምት አካባቢዎች አንደኛ ደረጃ ላይ ወደ 105፣ ሁለተኛ ደረጃ ላይ ሰባት ትምህርት ቤቶች፣ በአጠቃላይ ከ51 ሺሕ በላይ ተማሪዎች ለድርቁ ተጋላጭ ናቸው " ሲሉ አብራርተዋል።

አክለውም፣ " ተማሪዎች በመጀመሪያ የመምጣት አዝማሚያ ነበራቸው፣ ድርቁ በጣም በባሰባቸው አካባቢዎች (ለምሳሌ ጃን አሞራ ወረዳ 13 ቀበሌዎች አሉ፣ ከእነዛ  ውስጥ ወደ ሰባት ቀበሌዎች ላይ ድርቁ የከፋ ነው " ብለዋል።

ድጋፍ ካልተደረገ ተማሪዎች ወላጆቻቸው ጋር ይፈናቀላሉ የሚል ሥጋት እንዳለ የተናገሩት ኃላፊው፣ " ድርቅ ባለባቸው አካባቢዎች ያሉት ተማሪዎች እርግጠኛ ነኝ ትምህርት ቤት ይመጣሉ የሚል እምነት የለንም " ነው ያሉት።

በመሆኑም፣ መንግሥትን ጨምሮ ሁሉም ድጋፍ አድራጊዎች ለወላጆች የኢኮኖሚ፣ ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፋቸውን በመቀጠል ትምህርት እንዳይቋረጥ ከፍተኛ ሚና እንዲጫዎቱ ጠይቀዋል።

አቶ ሰላምይሁን በበኩላችሁ፣ ከ104 ሺሕ ሕጻናት መካከል በጠለምት 49 በመቶው የከፋ ችግር ላይ እንደሆኑ፣ ጃንአሞራ 33 በመቶ የሕመም ችግር እንዳለባቸው፣ የድጋፍ ችግር ያለባቸው እናቶች የምግብ ፍላጎት ወደ 30 በመቶ እየደረሰ መሆኑን ገልጸዋል።

በመጨረሻም መንግሥት፣ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማት፣ ቲክቫህ ኢትዮጵያን ጨምሮ ሁሉም ሚዲያዎች በቦታው በመገኘት እንዲዘግቡ፣ ድጋፍም እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

ዘገባው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia
#አማራ : ለወራት የቀጠለው የትጥቅ ግጭት ዐውድ እና አሉታዊ የሰብአዊ መብቶች እንድምታው

" ተፋላሚ ኃይሎች ሲቪል ሰዎችንና ንብረቶችን፣ የሕዝብ አገልግሎቶችን እና መሠረተ ልማቶችን ዒላማ ከማድረግ ሊቆጠቡ፣ መንግሥት የማኅበራዊ አገልግሎቶች እዲቀጥሉ አስቻይ ሁኔታ ሊፈጥር ይገባል። "

በአማራ ክልል ጉዳይ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዛሬ የተላከልን መግለጫ ከላይ ተያይዟል።

መግለጫው በክልሉ በተለያዩ ጊዜ በድሮን / አየር ጥቃት በርካታ ሰዎች መገደላቸውን ፣ በርካታ ሰዎች ግጭት ሽሽት አካባቢያቸውን ጥለው መሸሻቸውን፣ ከፍርድ ውጭ የሚፈፀመው ግድያ መቀጠሉን፣ የመንግሥት ኃላፊዎች ላይ ግድያም መፈፀሙን ያስረዳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ : ለወራት የቀጠለው የትጥቅ ግጭት ዐውድ እና አሉታዊ የሰብአዊ መብቶች እንድምታው " ተፋላሚ ኃይሎች ሲቪል ሰዎችንና ንብረቶችን፣ የሕዝብ አገልግሎቶችን እና መሠረተ ልማቶችን ዒላማ ከማድረግ ሊቆጠቡ፣ መንግሥት የማኅበራዊ አገልግሎቶች እዲቀጥሉ አስቻይ ሁኔታ ሊፈጥር ይገባል። " በአማራ ክልል ጉዳይ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ዛሬ የተላከልን መግለጫ ከላይ ተያይዟል። መግለጫው በክልሉ በተለያዩ…
#አማራ

በአማራ ክልል ለወራት ከቀጠለው የትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ በርካቶች በድሮን ጥቃት መገደላቸው እና በክልሉ ከፍርድ ውጭ ግድያዎች መቀጠላቸውን ዛሬ ከኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከተላከልን መግለጫ መረዳት ችለናል።

ከኢሰመኮ በደረሰን መግለጫ ፤ ከሐምሌ ወር 2015 ዓ.ም. ጀምሮ ባለው ጊዜ ውስጥ የአማራ ክልል ሁሉም ዞኖች በተለያየ ደረጃና ጊዜ የትጥቅ ግጭት ተካሂዶባቸዋል።

በተጨማሪም እነዚህ አካባቢዎችና ወረዳዎች በአንድ ወቅት ላይ በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች በሌላ ወቅት ደግሞ በታጣቂው ቡድን (በተለምዶ ፋኖ በመባል የሚታወቀው) በቁጥጥር ስር ውለዋል።

የትጥቅ ግጭቱ በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ በከባድ መሣሪያ እና አልፎ አልፎ በአየር / ድሮን ድብደባ ጭምር የታገዘ ነው።

በግጭቱ ዐውድ ውስጥ #የአየር /#ድሮን መሣሪያን ጨምሮ በከባድ መሣሪያዎች ጥቃት የተነሳ በሲቪል ሰዎች ላይ ሞት እና የአካል ጉዳት የደረሰ ሲሆን ፣ ሰዎች መኖሪያ አካባቢያቸውን ጥለው ለመሸሽ ተገደዋል።

ለምሳሌ ፦

- በሰሜን ሸዋ ዞን፣ በረኸት ወረዳ፣ ' መጥተህ ብላ ' ከተማ ጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም. በተፈጸመ የድሮን ጥቃት የአንድ ዓመት ከሰባት ወር ሕፃንን ጨምሮ በርካታ ሲቪል ሰዎች #ተገድለዋል፤ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል።

- በደብረ ማርቆስ ከተማ ጥቅምት 8 ቀን 2016 ዓ.ም. በተፈጸመ የድሮን ጥቃት  ቢያንስ 8 ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል።

- በደንበጫ ከተማ ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም. በከባድ መሣሪያ ድብደባ ምክንያት ሲቪል ሰዎች ላይ የሞትና የአካል ጉዳት ደርሷል።

ኮሚሽኑ እነዚህን መረጃዎች ያገኘው የአካባቢውን ነዋሪዎች እና የዓይን ምስክሮችን በማነጋገር ነው።

በአንዳንድ አካባቢዎች ጥቃትን አልያም ግጭትን በመሸሽ ነዋሪዎች ሙሉ በሙሉ ከቀያቸው ተፈናቅለው በአሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለማረጋገጥ ተችሏል።

በምንጃር ወረዳ ውስጥ የአውራ ጎዳና ጎጥ ነዋሪዎች ከመስከረም 6 ቀን 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ከቀያቸው ተፈናቀለው ቢያንስ 3ዐዐዐ የሚሆኑት አሞራ ቤቴ ቀበሌ በሚገኝ አንድ ትምህርት ቤትና ክፍት ሜዳ ላይ (በዛፍ ሥር) ተጠልለው የሚገኙ ሲሆን፣ ሌሎች ቁጥራቸው ያልታወቀ መተሃራና አዋሽን ጨምሮ ወደ የተለያዩ አካባቢዎች ተፈናቅለዋል።

ለተፈናቃዮች የተወሰነ ድጋፍ በማኅበረሰቡና እና በአንድ ተራድዖ ድርጅት የተደረገ ቢሆንም፣ በቂ ባለመሆኑ በአሳሳቢ ሁኔታ እንደሚገኙ ለመረዳት ተችሏል።

የነዋሪዎችን መፈናቀል ተከትሎ ሰብላቸው እንደወደመ፣ ንብረታቸው እንደተዘረፈ፣ የቤቶቻቸው ጣራያ እና በር እየተነቀለ እንደተወሰደ፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ ቤቶቻቸውን ከአጎራባች ክልል በመጡ ኃይሎች በኮንስትራክሽን መሣሪያዎች ጭምር ማፍረስ እንደተጀመረ ኢሰመኮ ያነጋገራቸው የአካባቢው ነዋሪዎችና የመንግሥት ኃላፊዎች አስረድተዋል።

በመንግሥት የጸጥታ ኃይል አባላት የሚፈጸሙ ከሕግ ውጪ የሆኑ ግድያዎች አሁንም መቀጠላቸውን ኢሰመኮ ተዓማኒ መረጃዎችን እየተቀበለ እንደሚገኝ ገልጿል።

ግጭቱ በተካሄደባቸው አካባቢዎች የመንግሥት የጸጥታ አካላት በመንገድ ላይ ወይም ቤት ለቤት ፍተሻ በማድረግ ከያዟቸው በርካታ ሲቪል ሰዎች ውስጥ ፦

- " ፋኖን ትደግፋላችሁ "

- " ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ "

- " መሣሪያ አምጡ "


- " የተኩስ ድምጽ ስለተሰማበት አቅጣጫ መረጃ ስጡ " በሚልና ይህንን በመሰሉ ምክንያቶች ከሕግ ውጭ የሆኑ ግድያዎች መፈጸማቸውን የሚያሳዩ ተዓማኒ መረጃዎች ተገኝተዋል።

እንደማሳያ ፦

▪️በባሕር ዳር ሰባታሚት አካባቢ መስከረም 29 እና 30 ቀን 2016 ዓ.ም. #ሦስት_ወንድማማቾችን ጨምሮ በርካታ ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል።

▪️በሰሜን ጎጃም ዞን፣ አዴት ከተማ መስከረም 29 ቀን 2016 ዓ.ም. ፍልሰታ ደብረ ማሪያም የሚኖሩ 12 የአብነት ተማሪዎችን ጨምሮ ሌሎች ሲቪል ሰዎች ተገድለዋል።

▪️ በምሥራቅ ጎጃም ዞን፣ አማኑኤል ከተማ ጥቅምት 3 ቀን 2016 ዓ.ም. ቢያንስ 8 ሲቪል ሰዎች በቤት ለቤት ፍተሻ እንደተገደሉ ለማወቅ ተችሏል።

▪️በምሥራቅ ጎጃም ዞን፣ ጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ፣ ግንደወይን ከተማ ሞጣ በር ተብሎ በሚጠራ አካባቢ መስከረም 18 ቀን 2016 ዓ.ም. አንድ በጥይት የቆሰለን ግለሰብ እናቱና እህቱ በባጃጅ አሳፍረው ወደ ሕክምና ተቋም በመውሰድ ላይ እያሉ፣ የመንግሥት የጸጥታ አካላት ባጃጁን አስቁመው ሁሉንም ተሳፋሪዎች ካስወረዱ በኋላ " የቆሰለው እኛን ሲዋጋ ነው " በሚል ምክንያት የባጃጅ አሽከርካሪውን ጨምሮ አራቱን ሰዎች በጥይት እንደገደሏቸው ኮሚሽኑ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች አስረድተዋል።

በባሕር ዳር፣ በፍኖተሰላም፣ በጎንደር እና በወልድያ ከተሞች በትጥቅ ግጭቱ ቆስለው ሕክምና ሲከታተሉ የነበሩ የተወሰኑ ሲቪል ሰዎች እና የታጣቂ ቡድኑ አባላት በመሆን በመንግሥት የጸጥታ አካላት የተጠረጠሩ ሰዎች ሕክምናቸው እዲቋረጥ ተደርጎ #ወዳልታወቀ_ስፍራ ከተወሰዱ በኋላ ፣ ከፊሎቹ ከተወሰኑ ቀናት በኋላ ወደ ሕክምና ተቋማቱ ሲመለሱ ቀሪዎቹ ያሉበት ሁኔታ ይህ መግለጫ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ ማረጋገጥ አልተቻለም።
 
በሌላ በኩል በየደረጃው የሚገኙ ሲቪል የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች፣ ግድያዎችና እገታዎች በታጠቁ ኃይሎች ተፈጽመዋል።

ለምሳሌ ፦

መስከረም 28 ቀን 2016 ዓ/ም የአማራ ክልል ምክር ቤት የሕግ፣ ፍትሕና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢን ጨምሮ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ከባሕር ዳር ወደ ደብረ ታቦር ሲሄዱ ' አለምበር ከተማ ' አካባቢ በታጣቂዎች ተገድለዋል።

በተለያዩ የክልሉ አካባቢዎች ማረሚያ ቤቶችና ፖሊስ ጣቢያዎች ላይ ጥቃት በመሰንዘር ታራሚዎችና ተጠርጣሪዎች እንዲያመልጡ ተደርጓል። 
 
ኮሚሽኑ ባደረገው ክትትል ፤ በተለይም ከመንግሥት ተቋማት ጭምር በሚደርሱት መረጃዎች መሠረት በግጭቱ ዐውድ የሚፈጸሙ የአስገድዶ መድፈር ድርጊቶች በጣም አሳሳቢ እና በአፋጣኝ ተገቢው ምርመራ ተደረጎ አርምጃ ሊወሰድበት የሚገባው ነው፡፡

የሕክምና አገልግሎት ለማግኘት በተለያዩ የጤና ተቋማት መድረስ የቻሉትን ተጎጂዎች ቁጥር ብቻ መሠረት በማድረግ ከሐምሌ ወር 2016 ዓ.ም. ጀምሮ ይህ መግለጫ እስከ ወጣበት ጊዜ ድረስ ቢያንስ #2ዐዐ_የአስገድዶ_መድፈር ተጎጂዎች በጤና ተቋማት ተመዝግበዋል፤ ከተጎጂዎች መካከልም የሀገር ውስጥ ተፈናቃይ ሴቶች እና የጤና ባለሞያ ሴቶች ጭምር ይገኙበታል።

ከትጥቅ ግጭቱ መስፋፋት ጋር ተያይዞ ፦
🔹ሲቪል ሰዎች እና የሲቪል የንግድ እና የመሠረተ ልማት ተቋማት ላይ ዝርፊያ ተፈፅሟል።
🔹የማሳ ላይ ሰብል ውድመት ጨምሮ በሲቪል ሰዎች፣ በሕዝብ እና በመሠረተ ልማት ላይ ጉዳት ደርሷል።
🔹ሕፃናት ከትምህርት ውጪ ሆነዋል በአንዳንድ አካባቢዎች የትምህርት ተቋማት ለወታደራዊ አገልግሎት ውለዋል። ይህ ደግሞ አፋጣኝ ትኩረት የሚሻ ነው።

በክልሉ ውስጥ በተለየ ሁኔታ ከተፈቀደላቸው ተቋማት በስተቀር ይህ መግለጫ እስከ ወጣበት ጊዜ ድረስ የኢንተርኔት አገልግሎት የተቋረጠ ሲሆን፣ በተለይም በግጭት ላይ ባሉ አካባቢዎች የስልክ አገልግሎትም ጨምሮ ተቋርጧል።

(ዛሬ ከ #ኢሰመኮ የተላከል ሙሉ መግለጫ በዚህ ታገኛላችሁ ፦ https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/82609?single)

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#አማራ

" ጥናቱ ባካለላቸው ወረዳዎች 36 ሰዎች በድርቅ ምክንያት ህይወታቸው አልፏል " - ረዳት ፕሮፌሰር አምሳሉ ደረጀ

የደባርቅ ዩኒቨርስቲ 8 አባላት ባሉት የጥናት ቡድን በመመደብ በሰሜን ጎንደር ዞን የተከሰተውን ድርቅ መጠንና ስፋት ያጠና ሲሆን ውጤቱንም ይፋ ማድረጉን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ሰምቷል።

ይህንን በተመለከተ የጥናት ብድኑ ስብሳቢ ረዳት ፕሮፌሰር አምሳሉ ደረጀ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጻ ሰጥተው ነበር።

ምን አሉ ?

- ጥናቱ ከመስከረም 28 እስከ ህዳር 20 2016 ዓ.ም የተካሄደ ነው። ጥናቱ ድርቅ በጃናሞራ፣ በበየዳና በጠለምት ወረዳዎች በሚገኙ ቀበሌዎችን ላይ የተካሄደ ነው።

- ጥናቱ ድርቁ በእነዚህ አከባቢዎች (በሦስቱ ወረዳዎች) በሚኖሩ ነዋሪዎች ላይ ጉዳት አድርሷል። 73 ሺህ 387 የቤት እንስሳትም በዚሁ ምክንያት #መሞታቸውን አረጋግጧል።

- በበየዳና ጃናሞራ ወረዳ ከቤተሰቦቻቸው ርቀው የሚኖሩ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ትምህርት ለማቋረጥ ተገደዋል። 16ሺ 650 ተማሪዎች ትምህርታቸውን ለመከታተል ተቸግረዋል። 292 ተማሪዎች አካባቢውን ለቀው ጠፍተዋል።

- ጥንቱ ባካለላቸው ወረዳዎች 36 ሰዎች በድርቅ ምክንያት ህይወታቸው አልፏል። የድርቁ ተጎጅዎች ድርቅን እንዲቋቋሙት ለማስቻል አስቸኳይ የምግብ የውኃ አቅርቦት ማቅረብ ይገባል።

ጥናቱ እንደመፍትሄ ምን አቀረበ ?

* የትክልትና ፍራፍሬ ዘር ማቅረብ፤
* የእንሰሳት መኖ ማቅረብ፤
* የእንሰሳት ክትባት  ማካሄድ፤
* የመድሂኒት ግዥና አቅርቦት፤
* የትምህርት ቤት ምግብ ፕሮግራም መጀመር፤
* የቤት ለቤት ልየታና ህክምና ማካሄድ
* የ12ኛ ክፍል ተማሪዎችን በአንድ አካባቢ እንዲማሩ መርዳት ይገኙበታል።

የዞኑ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሰላምይሁን ሙላት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል  ፦

° በዞኑ በ6 ወረዳዎች በሚገኙ 83 ቀበሌዎች በተከሰተ የድርቅ አደጋ ከ 452 ሺህ በላይ ነዋሪዎች ለድርቅ አደጋ ተጋልጠዋል።

° በሰብል የተሸፈነ 34 ሺህ ሄክታር መሬት በድርቅ ተጎድቷል።

° ለህብረተሰቡና ለእንሰሳት አግልግሎት የሚሰጡ የውኃ ተቋማት ደርቀዋል።

° ድርቁ በ100 የትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ ላሉ 54 ሺ 406 ተማሪዎች እንቅፋት ሆኗል።

° የፌደራል መንግስት አስቸኳይ ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው 239 ሺህ 400 የድርቁ ተጎጅዎች የምግብ እህል ለማዳረስ እየሰራ ነው። እስካሁን ለ177ሺ 100 ሰዎች አስቸኳይ የምግብ እህል ማድረስ ተችሏል።

° በክልል መንግስት 5 ሺህ 100 ኩንታል፤ በሌሎች ረጅ ድርጅቶች ደግሞ 7 ሺህ 73 ኩንታል እህል ድጋፍ ተደርጎል።

° ከተረጅው ብዛት አኳያና የድርቁ ተጎጅዎች መጠን እያደገ በመምጣቱ አሁንም ሰፊ ድጋፍ ያስፈልጋል።

° በድርቅ የተጎዱ ወገኖችን ለመታደግ ርብርብ ላደረጉ አካላት ሁሉ ምስጋና ይገባቸዋል። አሁንም መቀጠል ይገባል።

መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የጎንደር የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተስብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አማራ • " ከ13,000 በላይ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ባለመመለሳቸው የከፋ ችግር ውስጥ ናቸው " - የዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ፅ/ቤት • " በሰሃላ ወረዳ 94 በመቶ ነፍሰጡሮችና የሚያጠቡ እናቶች፣ 45 በመቶ ከአምስት ዓመት በታች ሕጻናት በምግብ እጥረት ተጎድተዋል " - የዞኑ ጤና መምሪያ ቢሮ በአማራ ክልል ዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን በአበርገሌና…
#አማራ #ዋግኽምራ

" ዞኑ ከነበሩት 33 አምቡላንሶች አሁን ላይ 9 አምቡላንሶች ብቻ ነው ያሉት። … የህፃናትና የእናቶች የህክምና አገልግሎት አደጋ ውስጥ ነው " - የዋግኽምራ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ

ከጸጥታ ጋር በተያያዘ ፦
* የመድኃኒት፣
* የትራንስፖርት፣
* የሕክምና መሣሪያዎች እጥረት በማጋጠሙ በዞኑ የሚገኙ የሕክምና ተቋማት አገልግሎት ለመስጠት ፈተና እንደሆነባቸው በአማራ ክልል የዋግኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።

የዞኑ ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ ምን አሉ ?

- ዞኑ ከነበሩት 33 አምቡላንሶች አሁን ላይ ዘጠኝ አምቡላንሶች ብቻ ነው ያሉት። በሰርቪስ፣ በሥራ ጫና ከጥቅም ውጪ ሆነዋል። 

- በተፈለገና ባለቀ ሰዓት ወቅቱን ጠብቆ መድኃኒት ለመግዛት እንቅስቃሴዎች ገድበውናል። የሴኩሪቲ ችግር በጣም አሳሳቢ ነው። ሪፈራሎች በሚፈለገው መልኩ እየተንቀሳቀሱ አይደለም። ስለዚህ በእናቶችና በህፃናት የጤና አገልግሎት ጠቅላላ አደጋ ውስጥ ነው። 

- ሰውከፍሎ መታከም አልቻለም። የጤና መድህን ሽፋናችን ዝቅተኛ ነው። ራሳቸውን ሰርቫይብ ማድረግ ያልቻሉ፣ ለመከላከያ፣ ለልዩ ኃይል ለሌሎች ቁስለኞች ሁሉ ጠቅላላ አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ የጤና ተቋማት ናቸው ያሉት። እየጠፉ ያሉበት ሁኔታ ነው ያለው። ግን ደግሞ በትግል እንደምንም እየተቋቋምን ማኅበረሰቡን ለማዳረስ እየሞከርን ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የጸጥታው ችግር በድርቅ ለተጎዱት ምን ጉዳት አስከተለ ? ሲል ጠይቋል።

° ይህ ሁኔታ በተለይ በዞኑ በድርቅ ምክንያት ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው የማኅበረሰብ ክፍሎች እያሳደረው ያለው ተፅዕኖ ከፍተኛ ነው።

* ኮሌራ ተከስቶብናል። እንደ ጤና ተቋማት ትልቅ ሥጋት፣ ከባድ ወረርሽኝ ላይ ነው ያለነው። ቁጥር አንድ ተጋላጭ የሚባሉት ህፃናት፣ ነፍሰጡርና አጥቢ እናቶች፣ አረጋዊያን፣ አካል ጉዳተኞች ናቸው። 

° ከኅዳር 6 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ የልየታ ሥራ በሁሉም ወረዳዎች አሰርተን ነበር። በዚያ መሠረት አስደንጋጭ ቁጥር ነው ያገኘነው። ከለየናቸው ነፍሰጡር፣ አጥቢ እናቶች 81 በመቶ የሚሆኑት አጣዳፊ መካከለኛ የምግብ እጥረት ያለባቸው ናቸው።

° እንደ ዞን ከለየናቸው ህፃናት 45 በመቶዎቹ አጣዳፊ ከፍተኛ የምግብ እጥረት ችግር ያለባቸው ናቸው። ይህ ቁጥር ከተቀመጠው ስታንዳርድ በላይና አስደንጋጭ ነው። አስደንጋጭ ከመሆኑም በላይ አሁን እየተሰሩ ያሉ ሥራዎች በጣም ዘገምተኛ ናቸው ብለዋል።

የዋግኽምራ ብሄረሰብ ዞን አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት ከዚሁ ጋር በተያያዘ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል ፦
☑️ 95 በመቶ እናቶች በምግብ እንደተጎዱ፣
☑️ የህፃናት የረሃብ መጠን 15 በመቶ ከደረሰ እንኳ ከስታንዳርድ በላይ እንደሆነ ነገር ግን ከ30 በመቶ በላይ ህፃናት በምግብ እጥረት እንደተጎዱ ገልጾ ነበር።

አሁን የጤና መምሪያ ኃላፊው በገለጹት መሠረት ደግሞ የህፃናቱ የምግብ እጥረት ጉዳት ወደ 45 በመቶ ከፍ ብሏል።

የዞኑ ጤና መምሪያ ፤ በተለይ የጸጥታው ችግር ከድርቁ ጋር ተያይዞ በጤና አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ፈተና መሆኑን፣ ድርቅ፣ ጦርነት፣ ወረርሽኝ በዞኑ መደራረባቸውን ገልጾ እስካሁን ድጋፍ ያደረጉትን ሁሉ አመስግነው፣ አሁንም መንግሥት፣ በጎ አድራጊ ድርጅቶች ከችግሩ ውስብስብነት አንፃር ከፍተኛ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተረድተው #እርዳታቸውን እንዲቀጥሉ ጥሪ አቅርቧል።

መረጃው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ተጠናክሮ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia
#አማራ

" ከ2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ውጭ ናቸው "

በጸጥታ ችግር ከ2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን አማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ገለጸ።

በመከላከያ ሠራዊትና በፋኖ በታጣቂዎች መካከል በክልልሉ በሚስተዋለው የተኩስ ልውውጥ ሳቢያ ምን ያህል ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ እንደሆኑ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጌታቸው ቢያዝን፣ ከ2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታ ውጪ መሆናቸውን ገልጸውልናል።

አቶ ጌታቸው ቢያዝን ምን አሉ ?

- በክልሉ የሚስተዋለው ወቅታዊ የጸጥታ ችግር የተማሪዎች የምዝገባ ሥራ ላይ ከፍተኛ ጫና እንዳሳደረ ነው።

- እንደ ክልል 6.2 ሚሊዮን ተማሪዎችን መዝግበን ማስተማር ነበረብን ፤ አሁን ላይ ግን እነዚያን ተማሪዎች መዝግበን በሙሉ ወደ ትምህርት ቤት ማምጣት አልቻልንም።

- አሁን ከ2 ሚሊዮን በላይ ተማሪዎች ያልተመዘገቡ አሉ። ይሄ ተሳትፎን በከፍተኛ ደረጃ ይጎዳል። ተሳትፎን ይጎዳል ማለት መማር የሚገባቸውን ተማሪዎች የትምህርት ዕድል እንዳያገኙ እያደረግን ነው ማለት ነው። በሕይወታቸው ጭምር እየፈረድን ነው ማለት ነው።

- ከተሳትፎው ባሻገር የትምህርት ጥራቱ ላይም ከፍተኛ ጫና እያሳደረ ነው፤ ጉዳቱ በአጠቃላይ አስከፊ ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጸጥታው ችግር ሳቢያ ምን ያህል መምህራን ከመማር ማስተማር ሥራቸው ውጪ ሆኑ ? ሲልም ጠይቋል።

አቶ ጌታቸው ፦ " በ2,000 አካባቢ ትምህርት ቤቶች የሚገኙ መምህራን ከሥራ ውጪ እንደሆኑ ተናግረዋል። ነገር ግን መምህራኑ ወደ ሥራቸው እንዲመለሱ የማድረግ ሥራ እየተሰራ ነው " ብለዋል።

የጸጥታ ችግር በትምህርት ተቋማት ላይ ያደረሰውን ጉዳት በተመለከተም ማብራሪያ ጠይቀናቸዋል።

አቶ ጌታቸው ፦ " በግጭት ወደ 42 ትምህርት ቤቶች የወደሙ አሉ። ጉዳቱ ከፍተኛ ነው። አሁን ከዚህ ለመውጣት ርብርብ እያደረግን ነው። " ሲሉ መልሰዋል።

በክልሉ የመማር ማስተማር አገልግሎት ሳይሸራረፍ እየተሰጠባቸው ያሉና በጸጥታው ምክንያት አገልግሎቱን የማይስጡ ምን ያህል የትምህርት ናቸው ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄም ፦

" በእኛ ክልል ወደ 10,000 አካባቢ ትምህርት ቤቶች አሉ። ከ10,000 አካባቢ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ወደ 2,000 አካባቢ የሚሆኑት ትምህርት ቤቶች በአንድም ይሁን በሌላ በጸጥታው ችግር አፌክት ሆነዋል። ወደ መደበኛ ሥራ ለመመለስ ነው እየሰራን ያለነው። " ሲሉ መልሰዋል።

በክልሉ የሚስተዋለው የጸጥታ ችግር ከላይ የተጠቀሱትን ጉዳቶች በዘርፉ ከማስከተሉ ባሻገር በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ውድመት ከደረሰባቸው 400 በላይ ትምህርት መካከል ሙሉ ለሙሉ ወደሙ የተባሉ የ1,000 ትምህርት ቤቶችን ግንባታ ለማከናወን እየተንቀሳቀሱ ባሉበት ወቅት አሁናዊው ጦርነት መከሰቱ ሌላ ችግር እንደሆነባቸው፣ ሆኖም ግን ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመለሱ በየ ወረዳዎችና ዞኖች ውይይት እየተደረገ መሆኑ ተመላክቷል።

በአማራ ክልል በመከላከያ ሠራዊትና በፋኖ ታጣቂዎች መካከል በሚደረጉ የተኩስ ልውውጦች በንጹሐን ላይ ሞትና ጾታዊ ጥቃቶች መድረሳቸውን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ከዚህ በፊት መግለጹና የተኩስ ልውውጡ እንዲቆም ማሳሰቡ አይዘነጋም።

ዘገባውን ያዘጋጀው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ዋግኽምራ " ድርቁ በጣም እየባሰ ነው። መታከም ያለባቸው ህፃናት ለተከታታይ 2 ወራት ምንም አልተደረገላቸውም" - ዋግኽምራ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ በአማራ ክልል የዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ጤና መምሪያ ቢሮ ኃላፊ አቶ አሰፋ ነጋሽ በዞኑ ስላሉ አሳሳቢ ጉዳዮች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ? - ድርቁ በጣም #እየባሰ ነው። ባለፈው ጥናት ካጠናን በኋላ ሊደረግ የሚገባው ግን ያልተደረገ በጣም በስፋት…
#አማራ #ዋግኽምራ

በአማራ ክልል በዋግኽምራ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ሰሃላ ሰየምትን ጨምሮ ድርቅ በተከሰተባቸው ሌሎችም ወረዳዎች ላይ እንስሳት በመኖ እጥረት #እየሞቱ ፣ አካባቢያቸውን ለቀው #እየተፈናቀሉ መሆኑን አስተዳደሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።

የአስተዳደሩ አደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ምህረት መላኩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ፣ ከ10,000 በላይ የተለያዬ እንስሳት በውሃና በመኖ እጥረት ሞተዋል።

በአበርገሌ፣ በሮቢና፣ በበለቃ በላይኛው ተከዜ ተፋሰስ በተለይ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ነጻ ያልወጡ፣ መንግሥት የማይቆጣጠራቸው ቀበሌዎች ላይ ሰፋ ያለ ችግር እንዳለ ገልጸዋል።

በአሁኑ ወቅት በአጠቃላይ በድርቁ ቀጥተኛ ጉዳት እየደረሰባቸው ያሉ እንስሳትን በሚመለከት ኃላፊው ፤ በሦስቱም ወረዳዎች ፦
* ሰሃላ ሰየምት፣
* ዝቋላ፣
* አበርገሌ በጣም የቅድሚያ ቅድሚያ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ተብለው የለተለዩ ወደ 791,000 አካባቢ እንደሆኑ አስረድተዋል።

ከ791,000ዎቹ ውስጥ በተለይ ሰሃላ ሰየምት ወረዳ ላይ ያሉት ክርቲካሊ የዕለትም አቅርቦት ስላጡ 171,000 ወደ ደሃና ወረዳ ተፈናቅለው እንዲሄዱና ተጠግተው ለጊዜው እንዲቆዩ መደረጉን ተናግረዋል።

" ይህን ይህል ተፈናቅሎ ከሄደ ቀሪው 620,000 ደግሞ ከዚያው #እየተላወሰ ነው ያለው " ሲሉ አክለዋል።

ያንብቡ👇
https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-01-24

@tikvahethiopia
#Ethiopia #US

አሜሪካ ከ #አማራ_ፋኖ ታጣቂዎች ጋር የሰላም ንግግር እንዲጀመር የኢትዮጵያ መንግሥትን እንደጠየቀች አሳውቃለች።

የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ሞሊ ፊ እንዲሁም የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ አምባሳደር ማይክ ሃመር በኦንላይን መግለጫ ሰጥተው ነበር።

መግለጫቸው ባለፉት ቀናት በኢትዮጵያ የነበራቸውን የስራ ቆይታ የተመለከተ ነበር። 

በዚህ ወቅት በኢትዮጵያ ቆይታቸው ከጠ/ ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ጨምሮ ከተለያዩ ባለስልጣናትና የተቋማት መሪዎች ጋር በኢትዮጵያ ያሉ ግጭቶች #በውይይት እንዲፈቱ መነጋገራቸውን አሳውቀዋል።

አሜሪካ በኦሮሚያ እየተካሄደ ያለው ግጭት እልባት እንዲያገኝ የበኩሏን ሚና እየተጫወተች መሆኑን ገልጸው በአማራ ክልልም ግጭቶች በሰላም እንዲቋጩ ከፋኖ ጋር ንግግር እንዲጀመር ጥሪ መቅርቡን ተናግረዋል።

አምባሳደር ማይክ ሃመር ምን አሉ ?

" ባለፈው ሕዳር ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር በዳሬሰላም በተደረገው ውይይት ላይ በቀጥታ ተሳትፈናል። አሁን ይህን ለመቀጠል ዝግጁ ነን። ግጭቱ በሰላም እንዲፈታ እንዴት መመቻቸት እንደሚቻል ለሁለቱም አካላት ሃሳብ አቅርበናል።

ከፋኖ ጋር ንግግር እንዲደረግ አምባሳደር ማሲንጋ ለመንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን እናውቃለን።

ሰላምን ለማረጋገጥ ያሉትን እድሎች በመጠቀም ጥረታችንን ለመቀጠል ዝግጁ ነን። በተደጋጋሚ እንዳልነው ለነዚህ ግጭቶች ወታደራዊ መፍትሄ አማራጭ አይሆንም አሁንም ትኩረት መደረግ ያለበት ውይይት ላይ ነው። " ብለዋል።

ሞሊ ፊ ምን አሉ ?

" ኢትዮጵያ በአሁን ወቅት በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች ያጋጠሟትን ፈተናዎች በሰላም ለመፍታት ቁርጠኛ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ቁርጠንኝነታቸው እንዲቀጥሉ እናበረታታለን።

በታጣቂዎች ለሚፈፀሙት ጥቃቶች የመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ስለሚወስዱት እርምጃ አሳሳቢነት ገልጸናል። የጸጥታው ሁኔታን አሳሳቢነት ብንረዳም የሲቪሎችን መብት ለመጠበቅ ተጨማሪ ጥሪ ያስፈልጋል " ብለዋል።

አምባሳደር ማይክ ሃመር ፤ " ከተለያዩ ባለስልጣናት ጋር በተደረገው ስብሰባ ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር ውይይት ለማመቻቸት እንዲሁም የቀጠሉትን ግጭቶች በሰላም ለመፍታት ከአማራ ፋኖ ጋር ሊደረግ የሚችል ንግግር ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት እንዳለን ገልጸናል " ብለዋል።

ሃመር በኢትዮጵያ ላለው ግጭት ወታደራዊ መፍትሄ እንደሌለ ገልጸው የኢትዮጵያ መንግሥትም ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁነት እንዳለው መግለፁን እናደንቃለን ሲሉ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ መንግሥት ከዚህ ቀደም ግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ ፅኑ አቋም እንዳለው መግለፁ ይታወቃል። ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋርም በይፋ ሁለት ጊዜ ድርድር ቢቀመጥም መጨረሻ ላይ መሳካት አልቻለም። በአማራ በኩል ከፋኖ ጋር ለድርድር ስለመቀመጥ እስካሁን በይፋ የተባለ ነገር የለም።

አሜሪካውያኑ ባለስልጣናት በሰጡት መግለጫ ከኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት ጋር ሳይሳካ ቀርቶ የተቋረጠው ድርድር መቼ እንደሚቀጥል እንዲሁም መንግሥት ከፋኖ ጋር ለድርድር ይቀመጥ እንደሆነ በግልፅ ባይናገሩም የኢትዮጵያ መንግሥት ለሰላማዊ መፍትሄ ዝግጁ እንደሆነ እንዳሳወቃቸው ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው የቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ / ጋዜጠና ኬኔዲ አባተ መሆኑን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Tigray የትግራይ ክልል የማህበረሰብ ተወካዮች ጥያቄ እና የጠቅላይ ሚኒስትሩ ምላሽ ምን ነበር ? ከትግራይ ወደ አ/አ የመጡ የማህበረሰቡ ተወካዮችና እዚህም ያሉ ተወላጆች ከጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ጋር በነበራቸው ቆይታ ፤ የትግራይ ህዝብ ከማንም ህዝብ ጋር  መጋጨት እንደማይፈልግ ገልጸው ፓለቲከኞችም ልጓም ማበጀት እንዳለባቸው አስገንዝበዋል። በአፅንኦት በጦርነቱ ከቄያቸው የተፈናቀሉ ወደ ቦታቸው…
#ትግራይ #አማራ

" እኔ #ከሪፈረንደም ውጭ መፍትሄ ያለ አይመስለኝም " - ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በትግራይ እና አማራ በኩል ላለው ችግር " ዘላቂው መፍትሄ ህዝባዊ ሪፈረንደም " ነው ሲሉ ተናግረዋል።

ጠቅለይ ሚኒስትሩ ፥ ከዚህ ቀደምም በትግራይ እና አማራ ላለው ችግር ዘላቂ መፍትሄ " ህዝቡ ህዝበ ውሳኔ ሲያደርግ " እንደሆነ በተደጋጋሚ እንደተናገሩት ጠቁመዋል።

" የሆነን ሰዎች እዛ ተቀምጠው ፣ እዛ ተቀምጠው ሲናገሩ አይደለም። ህዝቡን መልሰን ህጋዊ በሆነ መንገድ ዓለም እያየው ሪፈረንደም አድርገው ወደሚፈልጉት ቢጠቃለሉ ከዚያ በኃላ ለጥያቄ አይመችም " ብለዋል።

" አሁን ላይ ግን ሪፈረንደም የሚባል ነገር አይፈልገም " ያሉት ዶ/ር ዐቢይ " እራሱ ነዋሪው ሳይሆን ሌላ ሰው ነው መወሰን የሚፈልገው እዚህ እየመጣ ጥያቄ ያቀርባል ' አልተፈታም ' እያለ እኔ ደግሞ አቅጣጫ አስቀምጫለሁ እንዲፈታ " ሲሉ ተናግረዋል።

እሳቸው ያስቀመጡት አቅጣጫ በመጀመሪያ የተፈናቀውለው ህዝብ እንዲመለስ ከዛ ህዝቡ እንዲወስን (ሪፈረንደም እንዲያደርግ) መሆኑን ተናግረዋል።

" ሪፈረንደም ከተደረገ በኃላ ህዝቡ የወሰነውን እናክብርለት ፤ እኔ እዚህ ሆኜ መወሰን አልችልም " ብለዋል።

ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ " በትግራይ በኩል ስናነጋግር ያለው ናሬሽን እና በአማራ በኩል ስናነጋግር ያለው ናሬሽን በጣም የተራራቀ ነው ምንም የተቀራረበ አይደለም ለማቀራረብ የሚቻለው ህዝቡ እራሱ ሲወስን ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ከዚህ (ሪፈረንደም) ውጭ ለጊዜው ሌላ #መፍትሄ ያለ እንደማይመስላቸውም ገልጸዋል።

" ህዝቡ እንዲወስን ከተደረገ የተረጋጋ አካባቢ ይፈጠራል " ብለዋል።

" እያባላን ያለው የቦታ ችግር አይደለም እኛን የሚያባላን እንደ ንብ ቀፎ ውስጣችን የሚጮኸው ጩኸት ነው እንጂ ሀገሩማ በቂ ነው ቢሰራበት ቦታዎቹ ክፍት ናቸው መንገድ የላቸው ፣ ቤት የላቸው ክፍት ናቸው ' አልገባሁም ገባሁ ' እንጨቃጨካለን እንጂ የቦታ ችግር የለም ቦታው ላይ የሚስራት ችግር ነው የሚያጨቃጭቀን " ብለዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#አብና🕯 " የ4ሰዎች አስክሬን ተገኝቷል ፤ የ6 ሰዎች አስከሬን ሊገኝ አልቻለም ! " በአማራ ክልል፣ ሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ አብና ቀበሌ ልዩ ስሙ ኖላ በተባለ ቦታ ነሐሴ 18/2016 ዓ.ም በደረሰ የመሬት መንሸራተት አደጋ 10 ሰዎች ሞተዋል። የጠለምት ወረዳ የመንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጽሕፈት ቤት ኀላፊ ተስፋየ ወርቅነህ ምን አሉ ? " የ4 ሰዎች አስከሬን በፍለጋ ተገኝቷል ፤ የቀሪ 6…
#አማራ #ጎንደር🕯

በአማራ፣ ሰሜን ጎንደር ዞን 3 ወረዳዎች በመሬት መንሸራተት አደጋ የሞቱ እና የተጎዱ ሰዎች ቁጥር በዛሬው ዕለት ጨምሯል።

ሟች ወገኖቻችን 23 ደርሰዋል።

የአካል ጉዳት የደረሰባቸው ወገኖቻችን ደግሞ  8 መድረሳቸው ተነግሯል።

ከቄያቸው የተፈናቀሉ ወገኖቻችን አጠቃላይ ከ2 ሺህ 700 በላይ ናቸው።

አደጋው የደረሰው በዞኑ በጠለምት፣ በጃናሞራ፣ በአዲአርቃይና በየዳ ወረዳዎች በሚገኙ 11 የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ ነው፡፡

ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሰሜን ጎንደር ኮሚኒኬሽን ነው።

#አማራ #ሰሜንጎንደር

@tikvahethiopia