TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#NEBE

የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልል ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች የተካሄደው የሕዝበ-ውሳኔ ድምፅ ጊዜያዊ ውጤት ለህዝብ ይፋ መደረጉን ገልጿል።

ቦርዱ የድምፅ ቆጠራው ትናንት ማታ ተጠናቆ ጊዜያዊ ውጤቱም የድምጽ አሰጣጥ በተካሄደባቸው በ31 ማዕከላት ሥር በሚገኙ 3 ሺህ 771 ምርጫ ጣቢያዎች ዛሬ ጠዋት ለህዝብ ይፋ ተደርጓል ብሏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NEBE የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች ክልል ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች እና አምስት ልዩ ወረዳዎች የተካሄደው የሕዝበ-ውሳኔ ድምፅ ጊዜያዊ ውጤት ለህዝብ ይፋ መደረጉን ገልጿል። ቦርዱ የድምፅ ቆጠራው ትናንት ማታ ተጠናቆ ጊዜያዊ ውጤቱም የድምጽ አሰጣጥ በተካሄደባቸው በ31 ማዕከላት ሥር በሚገኙ 3 ሺህ 771 ምርጫ ጣቢያዎች ዛሬ ጠዋት ለህዝብ ይፋ ተደርጓል ብሏል። @tikvahethiopia
#NEBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥር 29 ቀን 2015 ዓ.ም. በደ/ብ/ብ/ሕ ክልላዊ መንግሥት ሥር በሚገኙ ስድስት ዞኖች ፦
- በኮንሶ፣
- በደቡብ ኦሞ፣
- በወላይታ፣
- በጋሞ፣
- በጌዴኦ፣
- በጎፋ እና አምስት ልዩ ወረዳዎች ማለትም ፦
• በቡርጂ፣
• በባስኬቶ፣
• በአሌ፣
• በአማሮ፣
• በዲራሼ ላይ ያካሄደውን የሕዝበ ውሣኔ ጊዜያዊ ውጤት የማዳመር ሥራ በሁሉም ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ላይ አጠናቆ በዞንና በልዩ ወረዳ ደረጃ ጊዜያዊ ውጤቶች ይፋ መደረጉን አስታውሷል።

ቦርዱ የመጨረሻውን ውጤት የማጣራትና የማረጋገጥ ሥራ የካቲት 6 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ አርባ ምንጭ ከተማ በሚገኘው የሕዝበ ውሣኔው ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጿል።

ቀደም ሲል ቦርዱ በማህበራዊ ሚዲያ ገጹ የመጨረሻውን በቦርድ የተረጋገጠ ውጤት የካቲት 8 ቀን 2015 ዓ.ም ይፋ እንደሚያደርግ የገለፀ ቢሆንም በርከት ያሉ ግድፈቶችና የምርጫ ህግ ጥሰቶች በቦርዱ የምርጫ ክትትል ቡድን እንዲሁም በምርጫ ታዛቢዎች ሪፖርት በመቅረቡ የማጣራት እና ውጤት የማረጋገጥ ስራን በታቀደበት ግዜ ለማጠናቀቅ አልተቻለም ብሏል።

በዚህም የውጤት ማጣራትና ማረጋገጥ ስራ ፦

የዲራሼ፣
አሌ፣
ደቡብ ኦሞ፣
ባስኬቶ፣
ኮንሶ
ቡርጂ ውጤቶችን የማጣራትና የማረጋገጥ ስራ ተጠናቆ ውጤታቸው በቦርዱ #ፀድቋል

በቀጣይም በቀሪዎቹ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ማለትም ፦
በአማሮ፣ በወላይታ፣ በጋሞ፣ በጌዴኦ እና የጎፋ ግዜያዊ ውጤቶች የማጣራትና የማረጋገጥ ሂደት እንደተጠናቀቀ ቦርዱ ለህዝብ ይፋ የሚያደርግ ይሆናል ሲል አሳውቋል።

በቦርዱ የፀደቀውን ውጤት ከላይ ተያይዟል በተጨማሪ በዚህ ማግኘት ይቻላል : https://nebe.org.et/am/Referendum_Result

#NEBE

@tikvahethiopia
#NEBE

ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ክልል በሚገኙ 6 ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች የተካሄደውን የህዝበ ውሳኔ ውጤት ይፋ አድርጓል።

እነዚህ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች በአንድ ክልል እንዲደራጁ የነጭ እርግብ ምልክት የተወከለ እና በአንድ ክልል መደራጀቱን አልደግፍም ለሚለው የጎጆ ምልክት ተወክሏል፡፡

ውጤቱን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት ወ/ሮ ብርቱካን ሚደቅሳ ተከታዩን መረጃ ሰጥተዋል።

- የወላይታ ዞን ህዝበ ውሳኔ #እንዲደገም በመወሰኑ እና በሌሎች ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ያልተካተቱ 81 የምርጫ ጣቢያዎች ሳይካተቱ፥ ከ1 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ መራጮች በአንድ ክልል እንደራጅ የሚለውን ምልክት መርጠዋል።

- በህዝበ ውሳኔው 78 ሺህ 970 መራጮች በአንድ ክልል መደራጀቱን ያልደገፉ ናቸው።

- በውጤቱ ያልተካተቱ የ81 ጣቢያዎች ውጤት በዞኖቹ አጠቃላይ ውጤት ላይ ሊያመጡ የሚችሉት ተጽዕኖ ባለመኖሩ ሳይካተቱ ቀርተዋል።

- የወላይታ ዞን ሙሉ በውጤቱ ያልተካተተው በአጠቃላይ የህዝበ ውሳኔው ውጤት ላይ ተጽእኖ ሊፈጥር የሚችል በመሆኑ #ድጋሚ ህዝበ ውሳኔ ይደረግበታል።

- የምርጫ ውጤታቸው በውጤቱ ያልተካተቱት የምርጫ ጣቢያዎች የወላይታ ዞን ሙሉ በሙሉ እና ኮንሶ 4 የምርጫ ጣቢያ፣ ደቡብ ኦሞ 4 ምርጫ ጣቢያ፣ ጋሞ 21የምርጫ ጣቢያዎች ፣ ጌዴኦ 23 የምርጫ ጣቢያዎች ፣ ጎፋ 10 የምርጫ ጣቢያዎች ፣ ቡርጂ ልዩ ወረዳ 2 የምርጫ ጣቢያዎች፣ አሌ ልዩ ወረዳ 3 የምርጫ ጣቢያዎች ፣ አማሮ ልዩ ወረዳ 7 እና ደራሼ ልዩ ወረዳ 7 የምርጫ ጣቢያዎች ነው።

Credit : #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#NEBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፥ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤን ያሰናከሉ የህግ አስፈጻሚ አካላት ላይ ፍትሕ ሚኒስቴር ክስ እንዲመሰርት ጠየቀ።

ቦርዱ ይህን የጠየቀው  ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ ጋር በተያያዘ ከሰሞኑ ያጋጠሙ መስተጓጎሎችን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ በሰጠበት ወቅት ነው።

ቦርዱ የፓርቲዎችን ጠቅላላ ጉባኤ ያሰናከሉ የህግ አስፈጻሚ አካላት ላይ ፍትሕ ሚኒስቴር ክስ እንዲመሰርት ከመጠየቅ ባለፈ በመንግስት መስሪያ ቤቶች ስር የሚተዳደሩ ስብሰባ ቦታዎች እና አዳራሾች ለፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ ክፍት እንዲሆኑም ውሳኔ አሳልፏል።

በኢትዮጵያ የምርጫ፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ እና የምርጫ ሥነ-ምግባር አዋጅ መሰረት፤ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤያቸውን ቢያንስ በሶስት ዓመት አንድ ጊዜ ማካሄድ አለባቸው።

የፖለቲካ ፓርቲዎች ይህን ግዴታቸውን ለመፈጸም በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ወቅት መስተጓጎል እየገጠማቸው እንደሚገኝ ምርጫ ቦርድ ገልጿል።

ባለፈው እሁድ የባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ እንዲሁም ከዛ ቀደም ብሎ የእናት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ መስተጓጎሉ ይታወሳል።

ከዚህ ባለፈ ምርጫ ቦርድ የጎጎት ለጉራጌ ሕዝብ አንድነት እና ፍትሕ ፓርቲ አስተባባሪዎች መጋቢት 3 የፓርቲውን ጠቅላላ ጉባኤ ተካፍለው በማግስቱ መጋቢት 4 ቀን የጠቅላላ ጉባኤውን ሰነዶችን እንደያዙ 12ት ሰዎች በፌዴራል ፖሊስ ታስረው ወደ ደቡብ ክልል መወሰዳቸውንና ሁለቱ እስካሁን አለመፈታታቸውን አረጋግጦ እንዲፈቱ ጠይቋል።

የተፈፀመውን " ወንጀል " እንደ ተራ ጉዳይ እንደማይመለከተው ያስታወቀው ምርጫ ቦርድ ድርጊቱ " ፓርቲዎቹ ብቻ ሳይሆን ምርጫ ቦርድም እንዳይኖር የሚያደርግ ነው " ሲል ዛሬ በሰጠው መግለጫ አስታውቋል።

መረጃው የኢትዮጵያ ኢንሳይደር እና ዶቼ ቨለ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#NEBE : የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፓለቲካ ፓርቲዎች ጉባዔ ለማካሄድ እያጋጠሟቸው ያሉትን የሕግ ጥሠቶች አስመልክቶ ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ከላይ የተያያዘውን ደብዳቤ ልኳል።

@tikvahethiopia
#NEBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፤ የትግራይ ክልልን ጨምሮ 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ባልተካሄደባቸው አካባቢዎች እና አካባቢያዊ ምርጫን በ2016 ዓ.ም ለማካሄድ መታቀዱን ዛሬ አሳውቋል።

ቦርዱ ይህን ያሳወቀው የ2015 በጀት ዓመት ያለፉት 9 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ነው።

የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ ፥ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት በተወሰኑ ክልሎች በሚገኙ አካባቢዎች 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ አለመካሄዱን ገልጸዋል።

ይህንኑ ምርጫ ለማካሄድ በ2015 ዝግጅት ለማድረግ ታቅዶ እንደነበር ተናግረዋል።

ነገር ግን የአካባቢ ምርጫ ለማካሄድ ቢታቀድም አለመሳካቱን ገልጸው፣ እነዚህን ምርጫዎች በ2016 ለማካሄድ ቦርዱ ዕቅዱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማቅረቡን ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ፥ ባለፉት ወራት ከፖለቲካ ፓርቲዎች አሠራር ጋር በተያያዘ አንዳንድ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ እንዳያካሂዱ በተለያዩ አካላት መከልከላቸውን ቦርዱ ማረጋገጡን እና አንዳንድ የፓርቲ አመራሮች ለእስር መዳረጋቸውን አቶ ውብሸት ገልጸዋል። ቦርዱ ለዚህ ችግር መፍትሔ ለመስጠት ሥራዎችን እየሠራ መሆኑን አመልክተዋል።

#ኢብኮ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update #NEBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰኔ 12 ቀን 2015 ዓ.ም. በ1,812 ምርጫ ጣቢያዎች ላይ ያስፈጸመውንና 849,896 መራጮች ድምፅ የሰጡበትን የወላይታ ዞን የድጋሚ ሕዝበ ውሣኔ  የውጤት ማዳመሩን ሥራ በዞኑ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ሲያከናወን መቆየቱን ገልጿል።

በዛሬውም ዕለት ቦርዱ የውጤት  የማመሳከሩንና የማዳመሩን ሥራ በማጠናቀቅ በዞን ደረጃ #የጊዜያዊ ውጤቱን ይፋ አድርጓል።

በዚህም መሰረት ፦

እርግብ ፦ የ6ቱ ዞኖች (ኮንሶ፣ ዎላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና የ5ቱ ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ደራሼ) በአንድ የጋራ ክልል መደራጀትን #እንደግፋለሁ ያሉት የድምፅ ብዛት 👉 760,285

ጎጆ ቤት ፦ የ6ቱ ዞኖች (ኮንሶ፣ ዎላይታ፣ ደቡብ ኦሞ፣ ጋሞ፣ ጌዴኦ፣ ጎፋ) እና የ5ቱ ልዩ ወረዳዎች (ቡርጂ፣ ባስኬቶ፣ አሌ፣ አማሮ፣ ደራሼ) በአንድ የጋራ ክልል መደራጀትን #አልደግፍም ያሉት የድምፅ ብዛት 👉 42,413

ከፍተኛ ቁጥር ያለው ድምፅ ያገኘ የሕዝበ ውሳኔ አማራጭ - #እርግብ መሆኑ ተገልጿል።

@tikvahethiopia
#NEBE

በገዛ ፍቃዳቸው ከኃላፊነታቸው በለቀቁት ወ/ሪት ብርቱካን ሚደቅሳ ምትክ አዲስ የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ለመተካት 8 አባላት ያሉት የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ ዕጩ መልማይ ኮሚቴ ዛሬ ተሰይሟል።

ይኸው ኮሚቴ የተሰየመው በኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ነው።

የኢፌዴሪ ህገ መንግሥት አንቀጽ 102 እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቋቋሚያ አዋጅ 1133/2011 አንቀፅ 5/1 ላይ በሰፈረው መሰረት #ጠቅላይ_ሚኒስትሩ ዕጩ የስራ አመራር ቦርድ አባላት የሚመለምል ገለልተኛ ኮሚቴ እንደሚሰይሙ ይደነግጋል።

የተቋቋመው መልማይ ኮሚቴ ወደ ስራ መግባቱ የተነገረ ሲሆን በቅርቡ #ጥቆማ መቀበል እንደሚጀምር ተገልጿል።

የምርጫ ቦርድ ሰብሰቢ መልማይ ኮሚቴው ፦
- ቀሲስ ታጋይ ታደለ (ሰብሳቢ)
- ፕ/ር ተከተል ዮሐንስ (አባል)
- አቶ ባዩህ በዛብህ (አባል)
- ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ (አባል)
- አቶ ካሳሁን ፎሎ (አባል)
- ወይዘሮ ርግበ ገብረሃዋርያ (አባል)
- ወይዘሮ እንግዳዬ እሸቴ (አባል)
- ኢ/ር መላኩ እዘዘው (አባል)

መረጃው ከጠቅላይ ሚኒስቴር ፅ/ቤት የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
#NEBE

ወ/ሮ ሜላተወርቅ እና አቶ ታደሰ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢነት የመጨረሻ እጩዎች ሆነው መለየታቸው ተነገረ።

በብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ እጩ መልማይ ኮሚቴ ከህዳር 3 እስከ 13 ድረስ 56 ጥቆማዎችን በተለያዩ የጥቆማ መንገዶች መቀበሉን ገልጿል። ከእነዚህ መካከል 52ቱ ወንዶች ሲሆኑ ቀሪ 4 ደግሞ ሴቶች እንደነበሩ አመልክቷል።

በዚህም በተለያዩ ሶስት ዙሮች በተለያዩ መስፈርቶች 5 ግለሰቦች የተለዩ ሲሆን በመጨረሻም መስፈርቱን ያሟሉ ሁለት እጩዎች መለየታቸው ገልጿል።

በዚህም መሰረት ፦

- ወይዘሮ ሜላተወርቅ ሃይሉ

- አቶ ታደሰ ለማ ለብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢነት የመጨረሻ እጩዎች ሆነው መመረጣቸውን ይፋ አድርጓል።

ሁለቱ እጩዎች የተመረጡት ባላቸው ልምድና ተሞክሮ የፖለቲካ ገለልተኝነት እና ሌሎች መስፈርቶችን አሟልተው በመገኘታቸው ነው ብሏል።

ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አንድ ሰብሳቢ የሚያስፈልገው በመሆኑ ሁለቱ እጩዎች ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ይቀርባሉ።

በመጨረሻ ፤ ከሁለቱ አንዱ የቦርዱ ሰብሳቢ እንደሚሆኑና ሹመቱም በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንደሚፀድቅ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ዘግቧል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NEBE ወ/ሮ ሜላተወርቅ እና አቶ ታደሰ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢነት የመጨረሻ እጩዎች ሆነው መለየታቸው ተነገረ። በብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የስራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ እጩ መልማይ ኮሚቴ ከህዳር 3 እስከ 13 ድረስ 56 ጥቆማዎችን በተለያዩ የጥቆማ መንገዶች መቀበሉን ገልጿል። ከእነዚህ መካከል 52ቱ ወንዶች ሲሆኑ ቀሪ 4 ደግሞ ሴቶች እንደነበሩ አመልክቷል። በዚህም በተለያዩ ሶስት ዙሮች በተለያዩ…
#NEBE

ዛሬ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው መደበኛ ስብሰባው ወ/ሮ ምዕላተወርቅ ሀይሉን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ አድርጎ ሾሟል ።

ምክር ቤቱ ወ/ሮ ሜላተወርቅ ኃይሉን የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ አድርጎ የሾመው በ1 ድምፀ ተዓቅቦ በአበላጫ ድምፅ ነው።

ወ/ሮ ሜላተወርቅ ማናቸው ?

- ወ/ሮ ሜላትወርቅ ለብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ኃላፊነት አዲስ አይደሉም። ቦርዱን በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች አገልግለዋል።

- ለሁለት ዓመታት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ሰርተዋል።

- የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሕግ ትምህርት ቤት ምርቋ ሜላትወርቅ የሥራ ሕይወታቸው የሚጀምረው በኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን ነው። በኮሚሽኑ ከጀማሪ የሕግ ኦፊሰርነት እስከ ኦፕሬሽን ኃላፊነት ድረስ ሰርተዋል።

- የኒው ጀኔሬሽን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ተባባሪ መሥራችም ናቸው።

- የሕግ ማማከር አገልግሎት የሚሰጥ የሕግ ድርጅት አቋቁመው ነበር።

- ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በሕግ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን ካገኙ በኋላ ከሰላም እና ደኅንነት ጥናቶች ተቋም (አይፒኤስኤስ) የማስተርስ ዲግሪያቸው ተቀብለዋል።

- ከአሜሪካ ሀርቫርድ ዩኒቨርሲቲ ኬኔዲ ትምህርት ቤት በሕዝብ አስተዳደር ሌላ የማስተርስ ዲግሪ አላቸው።

- በአካዳሚክ፣ በፖሊሲ እና በፐብሊክ ሴክትር ባለሙያነት፣ በሁለትዮሽ እና በዘርፈ ባለብዙወገን ስምምነቶች ተደራዳሪነት፣ በግልግል ዳኝነት አማካሪ በመሆን ሰፊ ልምድ እንዳላቸው በቅርብ የሚያውቋቸው ሰዎች ይናገራሉ።

ቀጣይ ምን ይጠብቃቸዋል ?

* የቀድሞዋ ሰብሳቢ ወ/ሪ ብርቱካን ሚደቅሳ ያላጠናቀቋቸው የቤት ሥራዎች ከፊታቸው ይጠብቃቸዋል።

* ቀዳሚው እና ትልቁ ያለፈው ምርጫ ባልተካሄደባቸው የአገሪቱ አካባቢዎች ምርጫ ማካሄድ ነው።

* ለሁለት ዓመት ጦርነት ሲካሄድበት በቆየው የትግራይ ክልል የፓርላማም የክልል ም/ ቤት ምርጫ አልተካሄደም። ክልሉ ላለፉት 3 ዓመታት በሕዝብ ተ/ም/ቤት ተወካይ የለውም። ቦርዱ በተያዘው 2016 ዓ.ም. በክልሉ ምርጫ ለማካሄድ ዕቅድ መያዙን ለፓርላማ አስታውቆ ነበር። መጪው የቦርዱ ሰብሳቢ ይህን ዕቅድ ያሳኩታል ወይ የሚለው በሂደት የሚታይ ጉዳይ ነው።

- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልልም በተወሰኑ አካባቢዎች ምርጫ ያልተደረገባቸው ቦታዎች አሉ።

- በአማራ ክልል እና በኦሮሚያ ክልል ወለጋ ዞኖች በፀጥታ ችግር ምርጫ ያልተካሄደባቸው አካባቢዎችም አሉ።

-  የአካባቢ ምርጫም ዋነኛ የቤት ሥራ ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከህ/ተ/ም/ቤት እና ከቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው ያሰባሰበው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#TPLF

" ጠቅላላ ጉባኤው ከቦርዱ ፍቃድ ውጭ ከተካሄደ  ቦርዱ ለዚህ ጉባኤም ሆነ በጉባኤዎቹ ላይ ለሚወሰኑ ውሳኔዎች በሙሉ ዕውቅና አይሰጥም "- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከህወሓት ጉባኤ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ለድርጅቱ ደብዳቤ ጽፏል።

ቦርዱ ፥ ነሐሴ 3/2016 ዓ/ም ለፓርቲው በጻፈው ደብዳቤ ፖርቲው በልዩ ሁኔታ መመዝገቡን እና የህጋዊ ሰውነት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀትም እንደሰጠው አስታውሷል።

ፓርቲው የቦርዱ ደብዳቤ እና የምስክር ወረቀት ከደረሰው ቀን ጀምሮ የሚተዳደረው የኢትዮጵያ የምርጫ የፖለቲካ ፖርቲዎች ምዝገባና የምርጫ ስነ ምግባር አዋጅ ቁጥር 1162/2011ና ይህን አዋጅ ባሻሻለው አዋጅ ቁጥር 1332/2016 እንዲሁም እነዚህን አዋጆች መሰረት ተደርገው በወጡ መመሪያዎችና የቦርዱ ውሳኔዎች መሰረት እንደሆነ አስገንዝቧል።

ቦርዱ ውሳኔ የሰጠባቸውና በደብዳቤ ከገለፃቸው በፓርቲው መተግበር ካለባቸው ተግባራት መካከል ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ከማድረጉ ከ21 ቀን በፊት ለቦርዱ ማሳወቅና ፖርቲው በሚያደርገው ጠቅላላ ጉባኤ የቦርዱ ታዛቢዎች መገኘት በዋናነት የተገለፁ ግዴታዎች እንደሆኑ አመልክቷል።

ሆኖም ግን በአሁኑ ወቅት ፖርቲው ጠቅላላ ጉባኤ ሊያደርግ መሆኑን ቦርዱ በተለያዩ መገናኛ ብዙሀን እየተዘገበ መሆኑ መመልከቱን ገልጿል።

በዚህም ቦርዱ " ለአንድ ጠቅላላ ጉባኤ መደረግ አስፈላጊ የሆኑ የቅድመ ዝግጅት ስራዎችን እንዲያውቅ ባልተደረገበት፣ ባልተከታተለበትና ባላረጋገጠበት እንዲሁም የቦርዱ ታዛቢዎች ባልተገኙበት ተጠራ የተባለው ጠቅላላ ጉባኤ ሊካሄድ አይችልም " ሲል አሳውቋል።

ጠቅላላ ጉባኤው ከቦርዱ ፍቃድ ውጭ ከተካሄደ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለዚህ ጉባኤም ሆነ በጉባኤዎቹ ላይ ለሚወሰኑ ውሳኔዎች በሙሉ ዕውቅና የማይሰጥ መሆኑን ለህወሓት በጻፈው ደብዳቤ ላይ ገልጿል።

#TPLF #NEBE

@tikvahethiopia