#NEBE

ዛሬ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደቡብ ክልል በሚገኙ 6 ዞኖችና 5 ልዩ ወረዳዎች የተካሄደውን የህዝበ ውሳኔ ውጤት ይፋ አድርጓል።

እነዚህ ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች በአንድ ክልል እንዲደራጁ የነጭ እርግብ ምልክት የተወከለ እና በአንድ ክልል መደራጀቱን አልደግፍም ለሚለው የጎጆ ምልክት ተወክሏል፡፡

ውጤቱን አስመልክቶ መግለጫ የሰጡት ወ/ሮ ብርቱካን ሚደቅሳ ተከታዩን መረጃ ሰጥተዋል።

- የወላይታ ዞን ህዝበ ውሳኔ #እንዲደገም በመወሰኑ እና በሌሎች ዞኖችና ልዩ ወረዳዎች ያልተካተቱ 81 የምርጫ ጣቢያዎች ሳይካተቱ፥ ከ1 ነጥብ 6 ሚሊየን በላይ መራጮች በአንድ ክልል እንደራጅ የሚለውን ምልክት መርጠዋል።

- በህዝበ ውሳኔው 78 ሺህ 970 መራጮች በአንድ ክልል መደራጀቱን ያልደገፉ ናቸው።

- በውጤቱ ያልተካተቱ የ81 ጣቢያዎች ውጤት በዞኖቹ አጠቃላይ ውጤት ላይ ሊያመጡ የሚችሉት ተጽዕኖ ባለመኖሩ ሳይካተቱ ቀርተዋል።

- የወላይታ ዞን ሙሉ በውጤቱ ያልተካተተው በአጠቃላይ የህዝበ ውሳኔው ውጤት ላይ ተጽእኖ ሊፈጥር የሚችል በመሆኑ #ድጋሚ ህዝበ ውሳኔ ይደረግበታል።

- የምርጫ ውጤታቸው በውጤቱ ያልተካተቱት የምርጫ ጣቢያዎች የወላይታ ዞን ሙሉ በሙሉ እና ኮንሶ 4 የምርጫ ጣቢያ፣ ደቡብ ኦሞ 4 ምርጫ ጣቢያ፣ ጋሞ 21የምርጫ ጣቢያዎች ፣ ጌዴኦ 23 የምርጫ ጣቢያዎች ፣ ጎፋ 10 የምርጫ ጣቢያዎች ፣ ቡርጂ ልዩ ወረዳ 2 የምርጫ ጣቢያዎች፣ አሌ ልዩ ወረዳ 3 የምርጫ ጣቢያዎች ፣ አማሮ ልዩ ወረዳ 7 እና ደራሼ ልዩ ወረዳ 7 የምርጫ ጣቢያዎች ነው።

Credit : #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia