TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#WSU

“ አንድ ዓመት መዘግየት በጣም ከባድ ነው። ግዴታ መማር እንዳለብን አስጠንቅቀውናል ” - የወላይታ ሶዶ ዩኒበርሲቲ ተማሪዎች

“ የተማሩበት ታይም ምን ያህል ነው? ተብሎ መወሰን አለበት” - የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ህብረት

የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲ የ4ኛ ዓመት ተማሪዎች በዚህ ዓመት መመረቅ ሲገባቸው “ አላወቅነውም ” ባሉት ምክንያት ለምረቃ አንድ ‘ዓመት ትጨምራላችሁ’ ተብለው እየተገደዱ መሆኑን አማረው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አሰምተዋል።

ለምን የእናንተ ብቻ ዘገዬ ወይም አንድ ዓመት ጭማሪ ተደረገ ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ አቅርቧል።

* ስኬጁሉ ላይ ነው ችግራቸው። በኮሮና ምክንያት 2013 ዓ/ም ሁሉም ግቢዎች ተማሪዎቻቸውን የጠሩት ሰኔ ወር ላይ ነበር። እኛም ከሁሉም ግቢ እኩል ነበር የገባነው (ሰኔ 26)። ወዲያውኑ (45 ቀናት አቆይቶ) አስወጣን (ከግቢ) ምንም ባላወቅንበት መንገድ። አንድ ሲሚስተር ጨርሰን መወሰጣት ሲገባን ሚድን ፈትኖ አስወጣን። 

* በቀጣዩ ዓመት ደግሞ ሚዲ የወሰድነውን ሁለት ሲሚስተር አድርጎ በአጠቃላይ አስተማረ። ሙሉ 3 ሲሚስተር ነበር ማስተማር የነበረበት ግን አንዱን ዓመት በሁለት ሲሚስተር ብቻ አደረገ። ስህተቱን የሰሩት እዚሁ ላይ ነው።

* ሬጅስተራር ላይ የሰፈረው “4ኛ ዓመት ናችሁ” ነው የሚለው። እኛ የምንማረው ግን ገና ሦስተኛ ዓመት ሁለተኛ ሲሚስተርን እየጀመርን ነው። ሌሎች ግቢዎች ግን አሁን 4ኛ ዓመት ሁለተኛ ሲሚስተርን እያስተማሩ ነው። የእኛ ሙሉ 3 ሲሚስተሮች ወደ ኋላ ቀርቷል ማለት ነው።

* ‘ወደ ኋላ ቀረን’ ብለን ስናመለክት ‘#አስተካክላለሁ’ ብሎ ‘3 ሲሚስተር አስተምራለሁ’ ካለ በኋላ ሁለት ሲሚስተር አስተማረና ካፌ ዘጋ። እንደዛ እየተደረገ አንድ ዓመት ባከነ። የእኛን የአንድ ዓመት በጀት ለምን እንደፈለጉት አናውቅም። ከሌሎች ግቢዎች በሚለይ ሁኔታ በሚያስጠላ ሁኔታ ላይ ነው ያለነው።

የሚል ማብራሪያ በአንድ ተወካያቸው በኩል ሰጥተዋል።

“ ሌሎች ግቢዎች የእኛን ባቾች በዚህ ዓመት ያስመርቃሉ። የእኛ ግን በዚህ ዓመት አይደለም” ያሉት ተማሪዎቹ፣ “ በዚህ ሳምንት ክላስ አልገባንም። ነገር ግን ግዴታ በቀጣይ ሰኞ መግባት እንዳለብን ተነግሮናል። ግዴታ መማር እንዳለብን አስጠንቅቀውናል። ” ሲሉ አስረድተዋል።

አክለውም፣ “ አንድ ዓመት መዘግየት በጣም ከባድ ነው። ሙሉ 3 ሲሚስተር አስተምሮ ሰኔ ላይ ይፈትነን (እንመረቅ) አንልም። ቢያንስ ስለ Exit exam የሚሆኑ ኮርሶችን ወደዚህ አሸጋሽገውልን Exist ተፈትነን ቀጣዩን አንድ ሲሚስተር እንድንወስድ ያድርጉን። አንድ ዓመት ከመዘግየት ግማሽ ዓመት መዘግየት ይሻላል ብለዋል ” ሲሉ አሳስበዋል።

ቅሬታውን በተመለከተ ምን ምላሽ እንዳለው ለመጠየቅ ወደ ዩኒቨርስቲው ከፍተኛ አመራሮሽ የተደረገው ሙከራ ባይሳካም፣ የወላይታ ሶዶ ዩኒቨርስቲው የተማሪዎች ኀብረት ፕሬዝዳንት ተማሪ ፍሬው ተክሌ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ “ ስኬጁል ላይ የተቀየረ ነገር የለም። ያልተጣራ መረጃ እንጂ በእኛ ፔጅ ላይ የተለጠፈ አይደለም ” ሲሉ አስተባብለዋል።

ተማሪ ፍሬው፣ “ የሚመረቁት መቼ ነው? ለሚለው የተማሩበት ታይም ምን ያህል ነው? የሚለው መወሰን አለበት” ያሉ ሲሆን፣ የዘንድሮ ተማሪዎቹ በቀጣይ ዓመት ነው የምትመረቁት ተብለዋል ወይስ አልተባሉም? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄም ቀጥኛ መልስ በመስጠት ፋንታ፤ “በእስኬጁል መሠረት ነው እኮ ይሄ ውሳኔ” ብለዋል።

መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia