TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
የቤት ኪራይ ? የአከራይ ተከራይ አዋጅ ተግባራዊ መሆን ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የቤት ተከራዮች " ኪራይ ጨምሩ ካለዚያ ለቃችሁ ውጡ " እየተባሉ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል። በተለይ በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች የሚኖሩና ቃላቸውን የሰጡን ተከራዮች ፥ አከራዮቻቸው በአንድ ጊዜ ከፍተኛ የኪራይ ብር እንዲጨምሩ ያን የማያደርጉ ከሆነ አስወጥተዋቸው ለሌላ ሰው እንደሚያከራዩ እንደነገሯቸው ገልጸዋል።…
#AddisAbaba

" ... የቤት አከራይ የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው በዓመት አንዴ መንግስት በሚያወጣው ተመን ብቻ ነው " - ቤቶች ልማትና አስተዳደር

የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።

ቢሮው ከሰኔ 1/2016 ዓ/ም ጀምሮ በ120 ወረዳዎች ምዝገባ እየተከናወነ እንደሆነ ገልጿል።

በቀሪ የ15 ቀናት ጊዜ ዜጎች በአቅራቢያቸው በሚገኙ ወረዳዎች በማቅናት ምዝገባ እንዲያካሂዱ አሳስቧል።

አከራዮች የውል ስምምነቱን ሳይፈጽሙ እስከ 3 ወር ድረስ ከቆዩ የ2 ወር የቤት ኪራይ እንዲከፍሉ ይደረጋል ተብሏል።

ይህንን ስራ ብቻ የሚያከናውን ቡድን መቋቋሙንም ቢሮው ገልጿል።

የውል ምዝገባው ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ በምሽት ጭምር እየተሰጠ እንደሆነ ያመለከተው ቢሮው ፥ " የተሰጠው የምዝገባ ጊዜ በቂ በመሆኑ የቀን ጭማሪ ላይኖር ይችላል " ሲል አሳውቋል።

ቢሮው በመግለጫው ከመጋቢት 24 ጀምሮ የሚደረግ የቤት ኪራይ ጭማሪ እና ውል ማቋረጥ ክልክል እንደሆነ እና ተቀባይነትም እንደሌለው አመልክቷል።

መንግስት ጥናት በማድረግ በሚቀጥለው ዓመት ሰኔ ወር ላይ የዋጋ ጭማሪ እንደሚያደርግ አሳውቋል።

አከራይ የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው በዓመት አንዴ መንግስት በሚያወጣው ተመን ብቻ እንደሚሆን አስገንዝቧል።

#FBC
#AddisAbaba #HousingDevelopmentandAdministration
#AddisAbaba

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " ... የቤት አከራይ የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው በዓመት አንዴ መንግስት በሚያወጣው ተመን ብቻ ነው " - ቤቶች ልማትና አስተዳደር የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል። ቢሮው ከሰኔ 1/2016 ዓ/ም ጀምሮ በ120 ወረዳዎች ምዝገባ እየተከናወነ እንደሆነ ገልጿል። በቀሪ የ15 ቀናት ጊዜ ዜጎች…
" ' የቤት ኪራይ ጨምሩ ' ወይም ' ቤቱን ልቀቁ ' የሚል ግፊት ከደረሰባችሁ ደውላችሁ ጠቁሙኝ " - የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ

በአዲስ አበባ ፤  ' ከአከራይ ተከራይ  የውል ስምምነት ' ጋር በተያያዘ ተከራዮች የሚገጥማቸውን ማንኛውም ችግር ጥቆማ ሊሰጡ እንደሚችሉ የከተማው የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።

ቢሮው ማንኛውም አከራይ ከመጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ የቤት ኪራይ መጨመርም ሆነ ተከራይን ማስወጣት ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑን አስገንዝቧል።

ከዚህም ጋር በተያያዘ ተከራዮች የቤት ኪራይ ጭማሪ አልያም ' ቤቱን ይልቀቁልኝ ' የሚል ግፊት ከአከራዮች ከደረሰባቸው በስልክ ቁጥር +251118722917 / +251118553820 ላይ በመደወልና ጥቆማቸውን በመስጠት መብታቸውን ማስከበር እንደሚችሉ ገልጿል።

በሌላ በኩል ፤ ሰኔ 1 ላይ የጀመረው የአከራይ ተከራይ የውል ስምምነት ሊጠናቀቅ  14 ቀናት የቀሩት ሲሆን ዜጎች በአቅራቢያቸው በሚገኙት ወረዳዎች በማቅናት ምዝገባ እንዲያካሂዱ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

አከራዮች የውል ስምምነቱን ሳይፈጽሙ እስከ ሶስት ወር ድረስ ከቆዩ የሁለት ወር የቤት ኪራይ እንዲከፍሉ እንደሚደረግ ተገልጿል።

መንግስት ጥናት በማድረግ በሚቀጥለው ዓመት ሰኔ ወር ላይ የዋጋ ጭማሪ እንደሚያደርግ አሳውቋል።

አከራይ የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው በዓመት አንዴ መንግስት በሚያወጣው ተመን ብቻ እንደሚሆን ተነግሯል።

#TikvahEthiopia
#HousingDevelopmentandAdministration

@tikvahethiopia