TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ልዩ ሀይል💪ወታደራዊ ትርኢቱን በማቅረብ ላይ ይገኛል። 7ኛው #ሀገር_መከላከያ_ሰራዊት_ቀን

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮጵያን እንፈልጋታለን‼️

ምስኪኑ ዜጋ ሲፈናቀል፣ ሲሰቃይ፣ ሲቸገር፣ ተበደልኩ ሲል፣ ፍትህ ተነፍጊያለሁ ብሎ ሲጮህ፣ መንግስት በድሎኛል ብሎ ሮሮውን ሲያሰማ ለርካሽ #የፖለቲካ_ትርፍ እና #ሀገር_ለማትራመስ የምትሯሯጡ ጨካኝ አረመኔ ሰዎች ኢትዮጵያን ስለምንፈልጋት እጃችሁን ሰብስቡልን።

ሰዎች ሰውነታቸውን ክደው #ሀዘናቸውን እንኳን #ብሄር ለይተው እንዲገልፁ የምትገፋፉ ሰውነታችሁን የከዳችሁ ሁሉ #ኢትዮጵያን ስለምንፈልጋት እጃችሁን ከሀገራችን ላይ አንሱ።

በደንብ ስሙኝ...🔥

ህዝቡን በብሄር ከፋፍላችሁ #ወደጦርነት ለመክተት ፌስቡክ ላይ #ተዘፍዝፋችሁ የምትውሉ ሰዎች--የምትወዱትን ማጣት ስትጀምሩ፣ ምስኪን ህፃናት እንደቅጠል ሲረግፉ ማየት ስትጀምሩ፣ ሚሊዮኖች ሰላም ፍለጋ መሰደድ ሲጀምሩ ስታዩ ደም እምባ እያለቀሳችሁ እያንዳንዷን ፌስቡክ ላይ የዋላችሁበትን ቀን #ትረግሟታላችሁ
.
.
መንግስት በአስቸኳይ #ፍትህ እንፈልጋለን ብለው የሚጮሁ ዜጎች ካሉ ያዳምጥ፤ ምላሽ ይስጥ፤ በምስኪን ዜጎች ህይወት ላይ #ቁማር የሚጫወቱ የፖለቲካ ነጋዴዎችንም አደብ ያስገዛ!

#FACEBOOK ከብዶናል!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#StopHateSpeech #TIKVAH_ETH

√ግንቦት 10 እና 11 - በዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ማዕከልነት /ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፣ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ ፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፣ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፣ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፣ ወሎ ዩኒቨርሲቲ ፣ መቐለ ዩኒቨርሲቲ/

√ግንቦት 17 እና 18 - በጅማ ዩኒቨርሲቲ ማዕከልነት/ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፣ ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፣ ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ፣ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፣ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፣ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፣ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፣ ወሎ ዩኒቨርሲቲ ፣ መቐለ ዩኒቨርሲቲ/

√ግንቦት 24 እና 25 - በሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ማዕከልነት/ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ፣ አ.ሳ.ቴ.ዩ፣ ጅግጅጋ ዩኒቨርሲቲ፣ ጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ ፣ ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ ፣ ዋቻሞ ዩኒቨርሲቲ ፣ ወራቤ ዩኒቨርሲቲ ፣ ወላይታ ሶዶ ዩኒቨርሲቲ፣ ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ፣ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ፣ ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ፣ ወሎ ዩኒቨርሲቲ ፣ መቐለ ዩኒቨርሲቲ/

በቀጣይ፦

√ዲላ ዩኒቨርሲቲ ፣ መቱ ዩኒቨርሲቲ ፣ አምቦ ዩኒቨርሲቲ ፣ አርሲ ዩኒቨርሲቲ ፣ አዲስ አበባ ዩንቨርስቲ ፣ ኮተቤ ዩኒቨርሲቲ ፣ አ.አ.ቴ.ዩ.፣ ሰመራ ዩኒቨርሲቲ

√ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ ፣ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረ ታቦር ዩኒቨርሲቲ ፣ ደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ...በዚህ መልኩ 45 ቱም ዩኒቨርስቲዎች ውስጥ ልዩ ልዩ መድረኮች ይኖሩናል።

የዝግጅቶቹ ይዘቶች፦

√የጥላቻ ንግግሮች ዙሪያ የእርስ በእርስ ውይይት
√የፅዳት ዘመቻ
√ደም ልገሳ
√የችግኝ ተከላ
√የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮች
√በTIKVAH-ETH የሙዚቃ ባንድ እና የኪነጥበብ ቡድኖች ልዩ እና አስተማሪ የኪነጥበብ ዝግጅቶች

ይህን #ሀገር_አድን ዘመቻ የሚመለከታችሁ ሁሉ #እንድታግዙም እንማፀናለን። የታሪክ ተወቃሽ እንዳንሆን አብረን እስራ! የጥላቻ ንግግር ሀገር ያሳጣናል።

ኑ ኢትዮጵያን በፍቅር እንገንባ!!
0919 743630 /ለተጨማሪ መረጃ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሀገር_አቀፍ_ፈተና2011 ብሄራዊ ፈተና ወሳጅ ተማሪዎች በፈተና ወቅት ህብረተሰቡ #የሃሰት መረጃዎችን ባለመቀበልና ባለማሰራጨት እንዲተባበራቸው ጠይቀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ: ጠ/ሚ #አብይ የሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ተማሪዎችን ወመዘክር በመገኘት አበራተዋል። #ሀገር_አቀፍ_ፈተና2011

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ውብ ሀገሬ!

ውብ ሀገሬ፤ ውብ ሀገሬ፣ውብ ሀገሬ
ባንቺ እኮ ነው፤ መከበሬ፤ መከበሬ
.
.
እናት አባት ቢሞት በሀገር #ይለቀሳል
እህት ወንድም ቢሞት በሀገር ይለቀሳል
#ሀገር የሞተ እንደሁ ወዴት ይደረሳል?

▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️▫️

#ኢትዮጵያን መውደድ ማለት፦ ህዝቦቿን፣ የህዝቦቿን ባህል፣ ቋንቋ፣ እምነት እና ስርዓት #መውደድ እና #ማክበር ማለት ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሰበር_ዜና

አትሌት ደምስ ፀጋው አረፈ!

ባለፉት በርካታ አመታት ሀገሩ ኢትዮጵያን ወክሎ በተለያዩ ውድድሮች ሲወዳደር የነበረው አትሌት ደምስ ፀጋው ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል፡፡ አትሌቱ ኢትዮጵያን በመወከል በሀገር አቋራጭ እና የአስፓልት ላይ ውድድሮችን በርካታ ጊዜ ያደረገ ሲሆን በአደረበት ህመም ምክንያት ህይወቱ አልፏል፡፡

አትሌት ደምስ #በግሉ እና #ሀገር በመወከል በርካታ ውድድሮችን አድርጎ ጥሩ ውጤት ያመጣ እንደነበርም ታውቋል፡፡ አትሌቱ ህይወቱ ያለፈው በአሜሪካ ሀገር ሲሆን በቅርብ ቀናት አስከሬኑ ወደ እናት ሀገሩ ኢትዮጵያ ይገባል ተብሏል፡፡

ምንጭ፦ አውሎ ሚዲያ/Bekal Alamirew/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ItsMyDam🇪🇹

www.mygerd.com ላይ ምን ያህል ገንዘብ ተሰባሰበ ?

በታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ በውጭ ሀገር ያሉ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያና የኢትዮጵያ ወዳጆች ታሪካዊ አሻራቸውን የሚያሳርፉበት ድረ ገፅ (www.mygerd.com) ይፋ ሆኖ የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ እየተከናወነ እንደሆነ ይታወቃል።

እስካሁን ድረስ በ1,170 ለጋሾች 149,202 የአሜሪካ ዶላር የተሰበሰበ ሲሆን 53 ሰዎች ደግሞ የገንዘብ ማሰባሰብ ዘመቻ እያደረጉ ይገኛሉ።

ይህ የድጋፍ ማሰባሰብ ስራ የአንድ ወቅት ብቻ ጉዳይ እንዳይሆን እና ዘላቂነት እንዲኖረው ድረገፁን በማስተዋወቅ ገንዘብም እንዲሰባሰብ በማድረግ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባዋል።

እውነተኛ ሀገርን መውደድ እና ለሀገር ማሰብ በተግባር የሚገለፀው እንደታላቁ ግድብ አይነት ስራዎችን ከዳር በማድረስ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገር አሻራን ጥሎ በማለፍ ነውና በተለይ በውጭ ሀገር ብዙ ተከታዮች ያላቸው አካላት ፣ማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲሁም አክቲቪስቶች ስራቸውን ማጠናከር አለባቸው።

#ሀገር_ማለት_ሰው_ነውና ከትውልድ እስከ ትውልድ ዘመናትን የሚሻገረውን ሚሊዮኖች ኢትዮጵያውያን ከጨለማ ውስጥ የሚያወጣውን፣ ድህነታችንንም አሽቀጥሮ የሚጥለውን ከጫፍ የደረሰውን ሀገራዊ ግዙፍ ፕሮጀክት ማጠናቀቅ የሁላችንም ግዴታ ነው።

@tikvahethiopia
#ይገምቱ

የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ማን ይሆናል ?

#ፈረንሳይ እና #አርጀንቲና ከ12:00 ጀምሮ የዓለም ዋንጫው ባለድል ለመሆን ከፍተኛ ፍልሚያ ያደርጋሉ።

የኳታሩን የዓለም ዋንጫ ማን ያሸንፋል ? የዋንጫው ባለቤት የሚሆነውን #ሀገር በትክክል ለመገመቱ 20 የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የ250 የሞባይል ብር ካርድ በሥጦታ የምናበረክት ይሆናል።

20 ትክክለኛ ገማቾች የሚለየቱ መልዕክቱን በላኩበት ቅደም ተከተል ነው።

ግምቱን መላክ ሚቻለው ጨዋታው እስከሚጀምርበት ደቂቃ ድረስ ብቻ ሲሆን #Edit የተደረገ ምላሽ ተቀባይነት አይኖረም።

(ግምትዎን #ከታች_ባለው የአስተያየት ማስቀመጫ ላይ ያኑሩ ፤ ፈረንሳይ ወይስ አርጀንቲና ? ከሁለቱ ሀገራት አንዱን ብቻ ይምረጡ ፤ ውጤት / በቁጥር መገመት #አያስፈልግም )

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ትምህርት የሚጀምረው መስከረም 7 ነው " - የአ/አ ትምህርት ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት የፊታችን ሰኞ መስከረም 7 /01/2016 ዓ.ም በሁሉም ትምህርት ተቋማት እንደሚጀምር አስታወቀ።

ቢሮው ይህን ያሳወቀው የትምህርት ሚኒስቴር የ2016 ዓ/ም የትምህርት ካላንደርን ለህዝብ ካሰራጨ በኃላ በማህበራዊ ትስስር ገፁ ባወጣው አጭር መልዕክት ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ ፤ " የ2016 የትምህርት ዘመን ትምህርት መስከረም 14 /1/2016 ዓ.ም እንደሚጀመር በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ #የተሳሳተ ነው " ብሏል።

ቢሮው በየትኞቹ የማህበራዊ ሚዲያዎች የተሳሳተ መረጃ እንደተሰራጨ በግልፅ አላሰፈረም።

የትምህርት ሚኒስቴር ዛሬ ቅዳሜ በተረጋገጠው የማህበራዊ ትስስር ገፁ ላይ ይፋ ባደረገው የ2016 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱ የሚመራበት #ሀገር_አቀፍ የትምህርት ካላንደር መሰረት ከመስረም 7 እስከ 11/2016 ዓ/ም ድረስ የትምህርት ሳምንት ሆኖ ይከበራል ብሏል።

መስከረም 14 ደግሞ የአንደኛ ሴሚስተር መደበኛ የክፍል ውስጥ ትምህርት እንደሚጀምር አሳውቋል።

ትምህርት ሚኒስቴር በዚህ ካላንደሩ ላይ ክልሎች በብሔራዊ ፈተናና በተለያዩ ክልላዊ ነባራዊ ሁኔታዎች መነሻ #የተወሰኑ የቀናት ለውጦች ሊያደርጉ እንደሚችሉ ታሳቢ ይደረግ ብሏል።

የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ ከዚህ ቀደም ይፋ ባደረገው መሰረት የ2016 ዓ/ም ትምህርት ሰኞ መስከረም 7 ቀን 2016 ዓ/ም በሁሉም ተቋም እንደሚጀምር #አስረግጦ ተናግሯል ፤ መላው የትምህርት ማህበረሰብ ይህን እንዲያውቀው ብሏል።

ከቀናት በፊት የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ የ2016 ዓ/ም የትምህርት መስከረም 7/2016 ዓ/ም እንደሚጀምር ማሳወቁን መዘገባችን ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ℹ️ ግብፅ በፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አል ሲሲ ቃል አቀባይ በኩል ከሶማሊያ ጎን እንደምትቆምና ደህንነቷንና መረጋጋቷን ለመደገፍ ፅኑ አቋም እንዳላት ገልጻለች። የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሼክ ሀሰን ሞሀሙድ ፤ ትላንት ምሽት ወደ አል ሲሲ ስልክ ደውለው #ከሁለት_ሳምንት በፊት ላሸነፉት ምርጫ " እንኳን ደስ አልዎት " ብለዋል። የስልክ ውይይቱን ተከትሎ የግብፅ ፕሬዜዳንት ቃል አቀባይ ሁለቱ መሪዎች ፦ -…
ዛሬ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሐሰን ሼይክ ሞሐሙድ " ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት " በሚል ወደ ኤርትራ፣ አስመራ መጓዛቸው ተሰምቷል።

የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት ፅ/ቤት ሐሰን ሼይክ ሞሐሙድ " በሁለቱ ወንድማማች አገራት " የሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ለመምክር ወደ ኤርትራ ተጉዘዋል ብሏል።

በቆይታቸውም ከኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር ይመክራሉ ተብሏል።

ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ ሶማሌላንድ ጋር የባሕር በር ማግኘት መንገድ ይጠርጋል  የተባለውን የመግባቢያ ስምምነት ከተፈራረመች ወዲይ ፕሬዝዳንቱ ወደ ተተለያዩ ሀገራት መሪዎች የስልክ በመደወል ውይይት ሲያደርጉ መሰንበታቸው ተሰምቷል።

ከማንም በፊት በቅድሚያ የደወሉላቸው ለግብፁ መሪ አብዱል ፈታህ አልሲሲ ሲሆን ከዛ በኃላ ከኳታር ኤሚር፣ ከኡጋንዳው መሪ ፣ ከቱርክ እንዱሁም ከአውሮፓ ኅብረት የውጭ ጉዳይ እና የደኅንነት ፖሊሲ ከፍተኛ ተወካይ ጋር መክረዋል።

ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር ባደረገችው የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ማንም የሚጎዳ አካልና #ሀገር ፤ የተጣሰ ህግና የተሰበረም እምነት እንደሌለ አሳውቃለች።

እጅግ ከፍተኛ የህዝብ ቁጥር፣ የቆዳ ስፋት እና እድገት ኖሯት የባህር በር አልባ የሆነችው ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ ፣ ያለ አንዳች ግጭት እና ጦርነት በሰጥቶ መቀበል መርህ ጥቅሟን ለማስከበር እንደምትሰራ በተደጋጋሚ ገልጻለች።

ሀገራት ከበርካታ ሺህ ኪሎሜትሮች መጥተው በዚሁ ቀጠና ቤዝ ሲመሰርቱ ጥቅማቸው ለማስከበር መሆኑን የገለፀችው ኢትዮጵያ የቀጠናው ባለቤት የሆና እጆቿን አጣጥፋ የምትቀመጥበት ምክንያት እንደሌለ ገልጻለች።

@tikvahethiopia