TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ItsMyDam🇪🇹

www.mygerd.com ላይ ምን ያህል ገንዘብ ተሰባሰበ ?

በታላቁ ኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ላይ በውጭ ሀገር ያሉ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልደ ኢትዮጵያውያና የኢትዮጵያ ወዳጆች ታሪካዊ አሻራቸውን የሚያሳርፉበት ድረ ገፅ (www.mygerd.com) ይፋ ሆኖ የገንዘብ ማሰባሰብ ስራ እየተከናወነ እንደሆነ ይታወቃል።

እስካሁን ድረስ በ1,170 ለጋሾች 149,202 የአሜሪካ ዶላር የተሰበሰበ ሲሆን 53 ሰዎች ደግሞ የገንዘብ ማሰባሰብ ዘመቻ እያደረጉ ይገኛሉ።

ይህ የድጋፍ ማሰባሰብ ስራ የአንድ ወቅት ብቻ ጉዳይ እንዳይሆን እና ዘላቂነት እንዲኖረው ድረገፁን በማስተዋወቅ ገንዘብም እንዲሰባሰብ በማድረግ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ ይገባዋል።

እውነተኛ ሀገርን መውደድ እና ለሀገር ማሰብ በተግባር የሚገለፀው እንደታላቁ ግድብ አይነት ስራዎችን ከዳር በማድረስ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገር አሻራን ጥሎ በማለፍ ነውና በተለይ በውጭ ሀገር ብዙ ተከታዮች ያላቸው አካላት ፣ማህበራዊ ሚዲያዎች እንዲሁም አክቲቪስቶች ስራቸውን ማጠናከር አለባቸው።

#ሀገር_ማለት_ሰው_ነውና ከትውልድ እስከ ትውልድ ዘመናትን የሚሻገረውን ሚሊዮኖች ኢትዮጵያውያን ከጨለማ ውስጥ የሚያወጣውን፣ ድህነታችንንም አሽቀጥሮ የሚጥለውን ከጫፍ የደረሰውን ሀገራዊ ግዙፍ ፕሮጀክት ማጠናቀቅ የሁላችንም ግዴታ ነው።

@tikvahethiopia