TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AddisAbaba

" ፈተናውን ብዙዎቹ ሊያልፉ ይችላል የሚል ግምት ነው የተያዘው " - የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ውስጥ ከሚኖሩ ዳይሬክተሮች እና ቡድን መሪዎች መካከል #ተመሳሳይ የብሔር ማንነት ያላቸው አመራሮች ብዛት ከ40 በመቶ እንዳይበልጥ ሊያደርግ መሆኑ ተሰምቷል።

በቅርቡ ለሚተገብረው #የሠራተኞች_ድልድል ሲባል ከ14 ሺህ በላይ የከተማ አስተደደሩ ሠራተኞች ነገ አርብ ታኅሣሥ 12/2016 ዓ.ም. ለፈተና ይቀመጣሉ።

ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉት ተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ባለፉት ሳምንታት ከሠራተኞቹ ጋር ውይይት ሲያደርግ ቆይቷል ተብሏል።

163 ሺህ ገደማ ሠራተኞች በስሩ ያሉት አስተዳደሩ ፤ በሚተገበረው ለውጥ ውስጥ ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል የከተማዋን የመንግሥት ሠራተኞችን በአዲስ መልኩ መደልደል የሚለው ይገኝበታል።

ለለውጡ ትግበራ ተብሎ የተዘጋጀ #የሥልጠና_ሰነድ ምን ይላል ?

-አሁን በመጀመሪያው ዙር ድልድል እንዲተገበርባቸው የተመረጡት አስራ ስድስት (16) ተቋማት ናቸው። ከእነዚህም መካከል ፦

* የአዲስ አበባ ከተማ መሬት ልማት እና አስተዳደር፣
* ቤቶች ልማት እና አስተዳደር፣ ትራንስፖርት፣
* ፐብሊክ ሰርቨሲ እና ሰው ሀብት ልማት፣
* ፕላን እና ልማት፣
* ሥራ እና ክህሎት፣
* ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮዎች
* ቤቶች ኮርፖሬሽን፣
* ኅብረት ሥራ ኮሚሽን እንዲሁም ሌሎች የከተማይቱ ኤጀንሲዎች እና ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቶች ይገኙበታል።

- የተዘረዘሩት መስሪያ ቤቶች ድልድል የሚደረግባቸው በማዕከል ቢሮዎቻቸው ብቻ ሳይሆን ክፍለ ከተማ እና ወረዳ ላይ ባሉ ጽህፈት ቤቶቻቸው ጭምር ነው።

የአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊው ዶ/ር ጣሰው ገብሬ ምን አሉ ?

° ከላይ የዘረዘሩት መስሪያ ቤቶች ለመጀመሪያው ዙር ትግበራ የተመረጡት ብዙ ተገልጋይ የሚያስተናግዱ እንዲሁም ብልሹ አሰራር እና የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ብዙ መጓደል ያለባቸው በመሆናቸው ነው።

° የሠራተኞች ድልድል ከመከናወኑ በፊት የእነዚህ መ/ቤቶች ሠራተኞች ለፈተና ይቀመጣሉ።

° ፈተና ለመስጠት የታቀደው የሠራተኞቹን የብቃት ደረጃ ለማረጋገጥ ነው።

° ፈተናው የባህሪ እና የቴክኒክ ምዘናዎችን የያዘ ነው። የሚሰጠው የቴክኒክ ምዘና ሠራተኞቹ ከሚሠሩት ሥራ ጋር ግንኙነት ያለው ነው። የባህሪው ፈተና ደግሞ አገልግሎት አሰጣጡን የሚፈታተኑ የባህሪ ችግሮች ስላሉ ያንን ክፍተት ለመሙላት አመላካች እንዲሆን ተስቦ የተዘጋጀ ነው።

° የምዘና ፈተናው የተዘጋጀው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በጋራ ትብብር ነው።

° ፈተናው የሚሰጠው በዩኒቨርስቲ / በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ነው።

° እስካሁን ባለው መረጃም ነገ ፈተናውን የሚወስዱ ሠራተኞች ቁጥር ከ14 ሺህ በላይ ነው።

° ፈተናውን የማያልፉ ሠራተኞች እንዳይኖሩ ዝግጅት እንዲያደርጉ፣ እንዲያጠኑ ተነግሯል። ፈተናው ለማለፍ በሚያስቸግር መንገድ በጣም የተወሳሰበ፣ አብስትራክት እና ንድፈ ሀሳባዊ የሆነ ሳይሆን የሠራተኞችን አቅም ለመለካት አመላካች ሆኖ ነው የተዘጋጀ ነው።

° ብዙዎቹ ሊያልፉ ይችላል የሚል ግምት ነው የተያዘው።

የሪፎርም ሥልጠና ሰነዱ ምን ይላል ?

- የከተማ አስተዳደሩ ባለሙያዎች ፈተናውን ለማለፍ ከ50 በመቶ በላይ ማምጣት ይጠበቅባቸዋል።

- ከዚህ የማለፊያ ውጤት በታች የሆነ ነጥብ ያገኘ ባለሙያ ከደረጃው ዝቅ ብሎ ባሉት የአስተዳደር እርከኖች ላይ ይመደባል።

- ለዳይሬክተሮች እና ለቡድን መሪዎች የተቀመጠው የፈተና ማለፊያ ነጥብ 60 በመቶ ነው። ይህን ነጥብ የማያስመዘግቡ አመራሮች ለዳይሬክተርነት ወይም ለቡድን መሪነት ኃላፊነት #መወዳደር_አልችሉም

ዶ/ር ጣሰው ገብሬ ፦

ሠራተኞች ፈተናውን ማያልፉ ከሆነ ዝቅ ተደርገው ሊመደቡ ይችላሉ። ድልድሉ ሲያልቅ ሌሎች አማራጮች ታይተው ምን ሊደረግ እንደሚችል የተለያዩ ዘዴዎችን ተጠቅሞ መፍትሄ ይፈለግላቸዋል።

በአዲስ መልኩ #ሠራተኞች ሲደለደሉ ከፈተናም በተጨማሪ ሌሎች መስፈርቶችን ይኖራሉ።

- ሰነዱ የሠራተኞች ድልድልን በተመለከተ " ትኩረትን የሚሹ አዳዲስ ጉዳዮች " በሚል ካስቀመጣቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ የብሔር ብሔረሰቦች ስብጥር ጉዳይ ነው።

- ድልድሉ ሲከናወን " ሕብረ ብሔራዊነትና አካታችነት በጥንቃቄ " መተግበር እንዳለበት በሰነዱ ላይ ሰፍሯል።

- " አካታችነትና ፍትሐዊነትን " በሚመለከተው የሰነዱ ክፍል ላይ በዳይሬክተርነት እና ቡድን መሪነት የሥራ መደቦች ላይ አመራሮች ሲመደቡ " የሜሪት ሥርዓት " ይጠበቃል።

- የአመራሮች ድልድል "የብሔር ብሔረሰብ ስብጥርን ባካተተ እና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ መልኩ " ይከናወናል።

- በመ/ቤቱ ካሉ የሥራ መደቦች መካከል በተመሳሳይ ማንነት የተያዙት ከ40 በመቶ መብለጥ የለባቸውም።

- መ/ቤቶቹ ድልድሉን ሲያከናውኑ ይህንን #የብሔር ስብጥሩን ለመጠበቅ እንዲችሉ " ብቃት ያላቸውን ሠራተኞች ከሌሎች መ/ ቤቶች በመለየት በዝውውር እንዲሟሉ " ይደረጋል።

ዶ/ር ጣሰው ገብሬ ፦

ከ40% መብለጥ የለበትም በሚል የተቀመጠው አሠራር፤ የሚተገበረው የቡድን መሪዎች እንዲሁም የዳይሬክተሮች ድልድል ላይ ብቻ ነው።

በዚህ ድልድል ወደ #ሠራተኛው የወረደ እንደዚህ ዓይነት ነገር የለም። የድልድል ደንቡ ውስጥም የለም።

የተመሳሳይ ማንነት ያላቸው ከተወሰነ ፐርሰንት በላይ መሆን የለበትም የሚለው ለዳይሬክተሮች እና ለቡድን መሪዎች ነው።

ከተማዋ የአገሪቱ ዋና ከተማ ናት። ብዙ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ያሉባት ስለሆነች ያንን ሥዕል የሚያሳይ እንዲሆን መደረግ ስላለበት የተቀመጠ ነገር ነው።

ይህ የአገልግሎት አሰጣጥ ሪፎርምና የሠራተኞች ድልድል እስከ ታኅሣሥ 25 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ ለማጠናቀቅ በጊዜያዊነት ዕቅድ ተይዟል።

ይህ መረጃ #ባለቤትነቱ የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።

@tikvahethiopia
#TECNO_Pop8 !

የስልኮን አቅም በእጥፍ ጨምሮ የፈለጉት አገልገሎት በበቂ ሁኔታ ለመከወን የተመረተ ሲሆን አይን ውስጥ ከሚገባ ልዩ ዲዛይን ጋር በማጣመር አዲሱ Pop 8 ከTECNO ሞባይል ቀርብሎታል!

ቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ
#Pop8 #TecnoMobile #TecnoEthiopia
#CBE 

 ገንዘብ ነክ ያልሆኑ አገልግሎቶችን
በሲቢኢ ሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ይጠቀሙ!
*


•  እለታዊ የውጭ ምንዛሬ መረጃ፣
•  የባንካችንን አገልግሎት መስጫ ስፍራዎች መጠቆሚያ፣
•  አስተያየት መስጫ፣
•  ለሌሎችም ገንዘብ ነክ ያልሆኑ አገልግሎቶች

የሲቢኢ ሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ብቻ በቂ ነው!

የሞባይል መተግበሪያውን ከፍተው ውደውስጥ ሳይገቡ አገልግሎቶቹን ያገኛሉ፡፡

የሲቢኢ ሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ለማውረድ፡
•  ለአንድሮይድ ስልኮች፡- https://play.google.com/store/search?q=cbe%20mobile&c=apps
•  ለአይፎን ስልኮች፡- https://apps.apple.com/us/app/cbe-mobile-banking-new/id1534203410

***  
የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!  
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh  
• Telegram፡- https://publielectoral.lat/combankethofficial
#HawassaUniversity

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ሁኔታ በዝርፊያ እየተፈተነ ይገኛል።

አላግባብ ለእስር ታዳረግን ያሉ ሰራተኞችም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ አቅርበዋል።

ለአመታት በሚሰጠዉ ትምህርትና ለማህበረሰቡ በሚያደርገዉ ድጋፍ  የሚታወቀዉ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በዝርፊያ ምክኒያት አየተፈተነ ነዉ።

አሁን ላይ ዩኒቨርሲቲዉ ከኮምፒዉተር እስከ ቀላልና ከባድ ማሽኖች ከመንገድ ላይ መብራት እስከ ግድግዳ ላይ የተገጠሙ ሶኬቶች ሳይቀር አየተዘረፈበት ሲሆን ዳፋዉ የደረሳቸዉ ተማሪዎችም ዘግተዉት የወጡት በር እየተሰበረ ከአልባሳት እስከ ኤሌክትሮኒክስ ከመማሪያ ቁስ እስከ መመረቂያ ሱፍ መዘረፋቸውን ይጠቁማሉ።

ችግሩን ዉስብስብ ያደረገዉ ደግሞ ዝርፊያዉን ለመመርመር የሚመጡት የህግ አካላት በተደጋጋሚ የግቢዉን ሰራተኞች ማሰራቸዉ እንደሆነ ቅሬታች አቅራቢዎች ገልጸዋል።

ከዚህዉ ጋር በተያያዘ በቅርቡ ለእስር መዳረጉን የገለጸልን የዩኒቨርስቲው መምህር በስሙ የነበሩ ኮምፒዉተሮች ተሰርቀዉ ማደራቸዉን ተከትሎ ለዘጠኝ ቀናት ለእስር መዳረጉን ይገልጻል።

መምህሩ እንደሚገልጸዉ " ስንት ጥበቃ ባለበት ግቢ ዉስጥ እቃ ተሸክሜ መዉጣት እንደማልችል እየታወቀ የተያዝኩበት መንገድ አሳፋሪና አግባብነት የጎደለዉ ነበር " ሲል ያስታዉሳል።

ሌላኛዉ ከዝርፊያ ጋር በተያያዘ ለሁለት ቀናት እስር መዳረጉን  የገለጸልን መምህር ደግሞ መምህራኑ የሚታሰሩት ሌሊት ተሰርቆ በሚያድር እቃ መሆኑን ገልፆ ጉዳዩ ተጣርቶ ከእስር ከተለቀቁ በኋላ ፋይላቸዉን ለመዝጋት የሚወስደዉ ጊዜ ከብዙ ጉዳይ እንደሚያስቀራቸዉና  ለእንግልት እየዳረጋቸዉ መሆኑን ያነሳል።

ከዚህዉ ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ  ምክትል ፕሬዚዳንት ዶር ሳሙኤል ጅሎ እንደሚገልጹት መምህራን ለእስር የሚዳረጉበት ምክኒያት ቢሯቸዉ በቁልፍ ተከፍቶ እቃዉ ጠፍቶ መገኘቱን ተከትሎ የምርመራ ትኩረት እነሱ ላይ የሚያነጣጥር በመሆኑ ነው በማለት ገልጸዋል ።

ዶ/ር ሳሙኤል አክለዉም መምህራን በሚያዙበት ወቅት በአግባቡና በክብር እንዲሆን የጸጥታ አካላትን እያነጋገሩ መሆናቸዉን ገልጸዉ ምርመራዎች በአጭር ጊዜ ዉስጥ እንዲያልቅና ፋይላቸዉ አንዲዘጋም ጥረት እንደሚያደርጉ አመላክተዋል።

በግቢዉ ዉስጥ የሚስተዋለዉን ዝርፊያ ለመቆጣጠር አሁን ላይ የጥበቃ አሰራሩን አዉትሶርስ ለማድረግ ጨረታ ላይ መሆናቸዉን የሚገልጹት ዶክተር ሳሙኤል አዉትሶርስ በማይደረጉ ክፍሎችም የጥበቃ ቁጥር ለመጨመር መታሰቡን ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪ አሁን ላይ ዩኒቨርስቲው ችግሩን ለመቅረፍ አንዳንድ ህንጻዎችን የስማርት ሴኪዉሪቲ ሲስተም መጠቀም መጀመሩን ተከትሎ ለዉጦች ቢኖሩም የስማርት ሲስተሞች የራሳቸዉ ክፍተት መኖርና የችግሩ ስር መስደድ ግን ሁኔታዉን ከባድ ሆኖ ይቀጥል ዘንድ ምክንያት ሆኗል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" በረሃብ የሰዎች ህይወት ስለማለፉ ማረጋገጫ የለንም " - አምባሳደር ሽፈራው ተ/ማርያም (ዶ/ር)

የፌዴራል አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) " በኢትዮጵያ በረሃብ ምክንያት የሰው ህይወት አልፏል የሚል ማረጋገጫ የለንም " አሉ።

ኮሚሽነሩ ይህንን ያሉት ከፋና ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ነው።

አምባሳደር ሽፈራው ተ/ማርያም (ዶ/ር) ምን አሉ ?

- መንግስት 11 ቢሊዮን ብር መድቦ እየሰራ ነው።

- በፌዴራል የሚደረገው ድጋፍ ክልሎችና ከታች ያሉ መዋቅሮቻቸው እንዲሁም ማህበረሰቡ በሚያደርገው ድጋፍ ላይ ተጨማሪ ነው።

- አንዳንድ አካባቢዎች ላይ የአህል ክምችት ቢኖረንም ትራንስፖርት ሰጪዎች በፀጥታው ምክንያት በፈለግነው ልክ ለማቅረብ አልቻልንም የሚሉት ነገር አለ። ይሄን ከሚመለከታቸው ጋር ተነጋግሮ ይስተካከላል።

- የድርቅ አደጋ ወደ ረሃብ ተቀይሮ የሰውን ህይወት የሚያጠፋበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ መዋቅራዊ አደረጃጀታችን የሚፈቅል አይደለም። የቀበሌ፣ የወረዳ ፣ የዞን፣ የክልል መዋቅር አለን የሚችለውን የመደጋገፍ ስራ ይሰራል። ህይወትን የመታደግ ስራ ይሰራል። እዚህ ላይ የፌዴራልም ድጋፍ አለ።

- የድርቅ አደጋ በሚኖርበት ጊዜ የስነምግብ ሁኔታዎችን በመውሰድ ምናልባት በአካባቢው የሚፈጠሩ ወረርሽኝ እና የመሳሰሉት ነገሮች የተለያዩ ነገሮችን ፈጥረው የዜጎቻችንን በሽታን የመቋቋም አቅም አዳክመው በቀላሉ የመሸነፍ እና የመሳሳሉት ጉዳዮች ሊፈጥር ይችላል።

-ሰዎች እንደሚያነሱት ፤ አንዳንድ #ሚዲያዎች እንደሚያነሱት በእህል እጥረት  ፤ ድርቅ ወደ ረሃብ ተቀይሮ የሰውን ህይወት የሚያጠፋበት ደረጃ የራሱ የሆነ ጊዜ አለው የራሱ የሆነ ጊዜ ይወስዳል በዚህ ነው ሰው የሞተው ለማለት #ምርመራ ይፈልጋል። የሰው የሞት ምክንያት ምንድነው ? እንደምናውቀው ሰው በተለያዩ ምክንያቶች ህይወቱ ያልፋል የዛ ህይወቱ ያለፈው ሰው ምክንያቱ ምንድነው ? የሚለውን የመለየት እና የማረጋገጥ ስራ የራሱ የሆነ አካሄድና  መንገድ ይጠይቃል።

- በእኛ በኮሚሽናችን ግምገማ የተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት አለመኖር የሚፈጥራቸው ተጋላጭነት ሊኖር እንደሚችል የምንገነዘብ ቢሆንም ግን በረሃብ ምክንያት ህይወቱ ያለፈ ሰው ስለመኖሩ #ማረጋገጫ_የለንም
.
.
በኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ እና አማራ ክልሎች ያሉ ከታች ያሉ መዋቅሮች በረሃብ ምክንያት ሰዎች ህይወት እንዳለፈ በተደጋጋሚ መግለፃቸው ይታወሳል።

በትግራይ ክልል የላይኛው መዋቅርም 25 ህፃናትን ጨምሮ 400 ሰዎች በረሃብ ምክንያት ህይወታቸው እንደጠፋ ማሳወቁ አይዘነጋም።

በክልል ከታች እስከላይ ማዋቅር የሚሰጡት እና ነዋሪዎች የሚገልጹት የረሃብ ሁኔታ በፌዴራል አደጋ ስጋት አመራር ቅቡልነት የለውም። ኮሚሽኑ በረሃብ ምክንያት የጠፋ ህይወት ስለመኖሩም ማረጋገጫ የለኝም ብሏል።

ከዚህ ቀደም የፌዴራል አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን  " ክልሎች ትኩረት እና የተሻለ ድጋፍ ለማግኘት ሲሉ ' ይህንን ያህል ሰዎች #ሞተውብኛል፣ ይህንን ያህል ተጎድተውብኛል ' የሚል መረጃ ያቀርባሉ " ማለቱ አየዝነጋም።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " ፈተናውን ብዙዎቹ ሊያልፉ ይችላል የሚል ግምት ነው የተያዘው " - የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ውስጥ ከሚኖሩ ዳይሬክተሮች እና ቡድን መሪዎች መካከል #ተመሳሳይ የብሔር ማንነት ያላቸው አመራሮች ብዛት ከ40 በመቶ እንዳይበልጥ ሊያደርግ መሆኑ ተሰምቷል። በቅርቡ ለሚተገብረው #የሠራተኞች_ድልድል ሲባል…
#እናት_ፓርቲ

እናት ፓርቲ የሚሰጠውን የመንግሥት ሰራተኞችን ፈተና ተቃወመ፤ እንቅስቃሴው እንዲቆምም ጠይቋል።

ፓርቲው ባወጣው መግለጫ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር " የመንግሥት ሠራተኞችን ፈተና ፈትኜ ምደባ አደርጋለሁ " እያለ የሚገኝበት ሁኔታ ሲቪል ሰርቪሱን ይበለጥ ውጤታማ ለማድረግ ተፈልጎ ሳይሆን በፖለቲካዊ ውሳኔ የመጣ በመሆኑ ፈጽሞ ተቀባይነት የለውም ብሏል።

መንግሥት እያደረገ የሚገኘው የፈተና እሩጫ የማይፈልጋቸውን ሠራተኞች ለማሰወገድ በአንጻሩ ደግሞ የሚፈልጋቸውን ለመተካት ሆን ብሎ ያቀናበረው ስልት ነው ሲል ፓርቲው ገልጿል።

" የአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች ርዕሳነ መምህራንንም መንግሥት በተመሳሳይ መልኩ ሕጋዊ ባልሆነ መንገድ ፈተና እየፈተነ መሆኑን አረጋግጫለሁ " ያለው ፓርቲው " የፈተናውን መልስ በክፍያ የሚያሰራጩ ግለሰቦች አጋጣሚውን እንደ ገንዘብ ማግኛ ምንጭ አድርገው እየተጠቀሙበት ይገኛል " ብሏል።

በተጨማሪም ከፈተናው በፊት መልሱ በየትምህርት ቤቱ አስቀድሞ ተለጥፎ መገኘቱንም ለመረዳት እንደቻለና ይህ ተከትሎም ፈተናው ለጊዜው መቋረጡን እንደደረሰበት አሳውቋል።

በዚህ ያህል መጠን በተዝረከረከና ለከት ባጣ ሁኔታ ሠራተኛውን "ፈተና ትፈተናለህ '' ብሎ ማዋከብ ድብቅ አጀንዳ ከሌለው በስተቀር አንዳች ረብ የለውም ያለው እናት ፓርቲ ፤ የሠራተኞች ፈተና አሰጣጥ መንገዱ ሕጋዊ ባለመሆኑ፣ የግልጽነት ችግር ስላለበት እና በፖለቲካዊ ውሳኔ የመጣ ጉዳይ በመሆኑ በአስቸኳይ ሊቆም ይገባል ብሏል።

ፓርቲው በተለይ ብሔር መጥቀስን መሠረት ያደረጉ ፎርሞች በአዲስ አበባ የተለያዩ የመንግሥት መ/ቤቶች በሰው ሀብት የሥራ ክፍል አማካይነት አስገዳጅ በሆነ መንገድ እንዲሞሉ እየተሠራ መሆኑን ማረጋገጡን ገልጾ ይህ ደግሞ መንግሥት እየሄደበት ያለውን አካሄድ ይበልጥ ጥያቄ ውስጥ ያስገባዋል ብሏል።

በመሆኑም ፦

- መንግሥት በተለያዩ ተቋማት የሚሰሩ የአዲስ አበባ የመንግሥት ሰራተኞችን ፈተና የሚፈትንበት መንገድ እና እያከናወነ የሚገኘው ምደባ ሕጋዊነት የሌለው ኢ-ምክንያታዊ የጥድፊያ ሥራ በመሆኑ በአስቸኳይ እንዲቆም፤

- በአዲስ አበባ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች እየሰሩ የሚገኙ ሠራተኞች "ብሔር" እንዲሞሉ የሚያስገድደው ፎርም በአስቸኳይ እንዲቆም፤

- በአዲስ አበባ የመንግሥት መስሪያ ቤቶች ውስጥ በማገልገል ላይ የሚገኙ ሠራተኞች የፈተና አሰጣጡን፣ ምደባውን እና አስገዳጅ የ"ብሔር" ጠቃሽ ፎርሙን በሰላማዊ መንገድ እንዲቃወሙ እናት ፓርቲ ባወጣው መግለጫ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba " ፈተናውን ብዙዎቹ ሊያልፉ ይችላል የሚል ግምት ነው የተያዘው " - የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ውስጥ ከሚኖሩ ዳይሬክተሮች እና ቡድን መሪዎች መካከል #ተመሳሳይ የብሔር ማንነት ያላቸው አመራሮች ብዛት ከ40 በመቶ እንዳይበልጥ ሊያደርግ መሆኑ ተሰምቷል። በቅርቡ ለሚተገብረው #የሠራተኞች_ድልድል ሲባል…
#Update

" ፈተናው በ3 የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ እና በትግርኛ ይሰጣል " - የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ

ከ16 ሺህ በላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተደደር ሠራተኞች ነገ አርብ ታኅሣሥ 12/2016 ዓ.ም. ለፈተና ይቀመጣሉ።

ይህን በተመለከተ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ከ11ዱ ክፍል ከተማ ከተውጣጡ የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሀብት ልማት ፅ/ቤት ኃላፊዎች፣ ከስራ አስፈፃሚዎች እንዲሁም ከተመረጡ 16 ተቋማት ሃላፊዎች ጋር ኦረንቴሽን እና ውይይት አካሂዷል።

በዚህ ወቅት ምን ተባለ ?

- በቅርቡ በሚተገብረው የሠራተኞች ድልድል መነሻ ከ16 ሺህ በላይ የከተማ አስተደደሩ ሠራተኞች ነገ አርብ ፈተና ይቀመጣሉ።

- ፈተናውም በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እና በከተማው በሚገኙ የሁለተኛ ደረጃ  ት/ቤቶች በቀን 12/2016 ዓ.ም ከቀኑ በ 7 ስዓት ጀምሮ እንደሚሰጥ ይሰጠል።

ተፈታኞች በፈተናው ወቅት ማሟላት የሚገባቸው እና የተከለከቱ ተግባራት ምንድናቸው ?

* በሰዓቱ በፈተናው ስፍራ መገኘት፤
* የግል መታወቂያ (ID CARD) መያዝ፤
* ምንም አይነት ፅሁፎችን እና ወረቀት፣ የእጅ ተንቀሳቃሽ ስልኮችን እንዲሁም መሰል ቁሳቁሶችን ይዞ ወደ ፈተና መግባት በጥብቅ የተከለከለ ነው፤
* በተሰጠው ሰዓት ፈተናውን አጠናቆ መውጣት ይገባል።

- በፈተናው ወቅትም ምንም አይነት የፀጥታ ስጋት እንዳይኖር ቢሮው ከአዲስ አበባ ከተማ ፖሊስ እንዲሁም ከፀጥታ አካላት ጋር በጥምረት እየሰራ ነው።

- ለተፈታኞች በቂ የትራንስፖርት ስምሪት ስራ የከናወናል ተብሏል።

- ለፈተና በተለያየ ምክንያት መገኘት ያልቻለ ተፈታኝ ምክንያቱ ታይቶ እንደ አስፈላጊነቱ ለፈተና የሚቀርብበት መንገድ ይመቻቻል ተብሏል።

- ፈተናውም በ3 የሀገር ውስጥ ቋንቋዎች ማለትም በአማርኛ፣ በአፋን ኦሮሞ እና በትግርኛ ይሰጣል።

ተጨማሪ ፦

☑️ ፈተናው የባህሪ እና የቴክኒክ ምዘናዎችን የያዘ ነው። የሚሰጠው የቴክኒክ ምዘና ሠራተኞቹ ከሚሠሩት ሥራ ጋር ግንኙነት ያለው ነው። የባህሪው ፈተና ደግሞ አገልግሎት አሰጣጡን የሚፈታተኑ የባህሪ ችግሮች ስላሉ ያንን ክፍተት ለመሙላት አመላካች እንዲሆን ተስቦ የተዘጋጀ ነው።

☑️ የምዘና ፈተናው የተዘጋጀው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በጋራ ትብብር ነው።

☑️ፈተናው የሚሰጠው በዩኒቨርስቲ እና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ነው።

☑️ የከተማ አስተዳደሩ ባለሙያዎች ፈተናውን ለማለፍ ከ50 በመቶ በላይ ማምጣት ይጠበቅባቸዋል።

☑️ ከዚህ የማለፊያ ውጤት በታች የሆነ ነጥብ ያገኘ ባለሙያ ከደረጃው ዝቅ ብሎ ባሉት የአስተዳደር እርከኖች ላይ ይመደባል።

☑️ ለዳይሬክተሮችና ለቡድን መሪዎች የፈተና ማለፊያ ነጥብ 60 በመቶ ነው። ይህን ነጥብ የማያመጡ አመራሮች ለዳይሬክተርነት / ለቡድን መሪነት ኃላፊነት #መወዳደር_አልችሉም

☑️ በመ/ቤት ካሉ የሥራ መደቦች መካከል በተመሳሳይ ማንነት / ብሔር የተያዙት ከ40 በመቶ እንዳይበልጡ ይደረጌ። ድልድሉን ሲያከናውኑ ይህንን #የብሔር ስብጥሩን ለመጠበቅ እንዲችሉ " ብቃት ያላቸውን ሠራተኞች ከሌሎች መ/ ቤቶች በመለየት በዝውውር እንዲሟሉ " ይደረጋል።

ከ40% መብለጥ የለበትም በሚል የተቀመጠው አሠራር፤ የሚተገበረው የቡድን መሪዎች እንዲሁም የዳይሬክተሮች ድልድል ላይ ብቻ ነው። በዚህ ድልድል ወደ #ሠራተኛው የወረደ እንደዚህ ዓይነት ነገር የለም። የድልድል ደንቡ ውስጥም የለም።

@tikvahethiopia
#Tecno_Pop8
በአዲሱ ፖፕ 8 ዘመናዊነትን ይቀላቀሉ  !

ለአያያዝ ምቹ እና ለአጠቃቀም ቀላል ሆኖ በተራቀቁ የቴክኖሎጂ ግብአቶች ዳብሮ የቀረበውን አዲሱ TECNO Pop 8 በእጆ ካስገቡት የሚመሰክሩለት ዘመናዊ ሞባይል!

ቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ
#Pop8 #TecnoMobile #TecnoEthiopia
#ኢዜማ

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ (ኢዜማ) ፤ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ም/ቤት የህዝብ ተወካይ አባሉ ህግ ተጥሶ እንደታሰሩበት ገለጸ።

ፓርቲው አባሉ በአስቸኳይ ከእስር እንዲፈቱ ጠይቋል።

ኢዜማ ፤ በ2013 ዓ.ም በተደረገው 6ኛ ሀገር አቀፉ ምርጫ #ካሸነፈባቸው የምርጫ ክልሎች መካከል አንዱ በሆነው " ዛይሴ ልዩ ምርጫ ክልል " በሚገኙ አባላት ላይ በተለያየ ጊዜ ልዮ ልዮ ጥቃቶች እየደረሱ እንደሆነ አመልክቷል።

ፓርቲው በጋሞ ዞን የሚገኙ የመንግሥት አካላት ፦
- ከሕግ አግባብ ውጪ የሚፈጽሟቸውን ተግባራት እንዲያቆሙ፣
- በእነዚህ ድርጊቶች የተሣተፉ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ፣ 
- ያለአግባብ የታሠሩ አባሎቹ እንዲፈቱና አስፈላጊው ካሣ እንዲፈጸምላቸው በተደጋጋሚ መጠየቁን ገልጾ ፤ የዞኑ አመራሮች ግን ከዚህ ተግባራቸው ለመቆጠብ ምንም አይነት ተነሣሽነት የሌላቸው መሆኑን እና ህገወጥ ድርጊቱም ተባብሶ መቀጠሉን  አረጋግጠናል ብሏል።

በዚህም የዛይሴ ልዩ ምርጫ ክልል የቀድሞው የደቡብ ብ/ብ/ክልል የአሁኑ የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ም/ቤት ተወካይ እና የኢዜማ አባል የሆኑት አቶ አማንያስ ጉሹና መታሰራቸውን አሳውቋል።

እስሩ " በኢፌድሪ ሕገመንግስት አንቀጽ 54(6) የተጠቅሰውን ድንጋጌ የተላለፈ ነው  " ያለው ፓርቲው " ወንጀል ሲፈጽሙ እጅ ከፍንጅ ባልተያዙበት እና ያለመከሰስ መብታቸው በም/ቤቱ ባልተነሳበት ሁኔታ ከታህሳስ 09 ጀምሮ በጋሞ ዞን አሰተዳደር ፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው በአርባምንጭ ዙርያ ወረዳ ፖሊስ ጣብያ ይገኛሉ ፤ ፍ/ቤት ያለመቅረባቸውን አረጋግጠናል ብሏል።

ህግ ተስጥሶ የተሳሩት አባሉ እና የደቡብ ኢትዮጵያ ም/ቤት ተወካይ የሆኑት አቶ አማንያስ ጉሹና በአስቸኳይ እንዲፈቱ ጠይቋል።

በሌላ በኩል . . .

የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ ፓርቲ ኢዜማ ሰብሳቢ ኢንጂነር መልካሙ ሼጌቶ በፖሊስ ተይዘው መታሠራቸውን ፓርቲው አሳውቋል።

የክልሉ የፖርቲው ምክትል ሰብሳቢ አቶ አስቻለው ገ/ሚካኤል ለዶቼ ቨለ ሬድዮ በሰጡት ቃል ፤ ኢንጂነር መልካሙ በከፋ ዞን ፖሊስ አባላት የተያዙት በሥራ ገበታቸው ላይ እንዳሉ መሆኑና ፖሊስ #የፍርድ_ቤት ማስረጃ እንዳላቀረበ ገልጸዋል።

ፓርቲው እስሩን ህግን ያልተከተለ መሆኑ በመግለፅ ለካፋ ዞን ፍትሕ ቢሮ በፃፈው ደብዳቤ የአባሉ ጉዳይ በህግ እንዲታይ ጠይቋል። የተፈፀመውን ተግባራም አውግዟል።

የከፋ ዞን ፖሊስ አዛዥ ኢ/ር መኮንን ገ/መድኅን ሰብሳቢው በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰራጩት ጹሑፍ ተጠርጥረው መታሰራቸውን አረጋግጠዋል።

" መታሰሩ ትክክል ነው በሶሻል ሚዲያ የተላለፈ ነገር አለ። በዚህ በሶሻል ሚዲያ እርስ በእርሱ ህዝቡን የሚያጋጭ፤ በዚህ ጉዳይ ላይ አንተ ተነስ እከሌ ተነስ  የእከሌ ዘር ብሎ ማስተላለፍ ይሄ የተከለከለ ነው። ይሄንን እያጣራን ስለሆነ በዚህ ጉዳይ ላይ የተጠረጠረ ነው።" ሲሉ ምላሻቸውን ለሬድዮ ጣቢያው ሰጥተዋል።

የፓርቲው የካፋ ዞን ኢዜማ ማስተባበሪያ በበኩሉ ፤ " እኛ እንደ ፖርቲ በግለሰቡ ሶሻል ሚዲያ አካውንት ህዝብን ከህዝብ ብሔርን ከብሔር የሚያጋጭ መልዕክት ፖስት ተደርጎ አላገኝንም " ብሏል።

በ24 ሰዓት ውስጥ  ቃል መስጠት እና በ48 ሰዓት ውስጥ ፍርድ ቤት መቅረብ ሲገባቸው ሁለቱም ሳያደረጉ እስከ አሁን እስር ላይ ይገኛሉ ሲል ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update 🔹" ችግር ላይ ላለዉ መምህር ተገቢ ያልሆነ መልስ ነው የተሰጠን " - መምህራን 🔸 " ችግሩን ለመፍታት መግባባት ላይ ተደርሶ ወደስራ የሚያስገቡ እንቅስቃሴዎች አሉ ፤  ከሰኞ ጀምሮ ወደአካባቢዉ እናቀናለን " - የዞኑ ትምህርት መምሪያ ኃላፊ በማዕከላዊ ኢትዮጰያ ክልል ሃዲያ ዞን የባዳዋቾ ወረዳና የሾኔ ከተማ ትምህርት ቤቶች አሁንም አለመከፈታቸዉ ተሰምቷል። በባዳቾች ወረዳና ሾኔ ከተማ…
" ቃል የተገባልን ውዝፍ ደመወዛችን ስላልተከፈለን እዳችን መክፈል አልቻልንም " -  የባድዋቾ ወረዳና የሾኔ  መምህራንና የጤና ባለሙያዎች

በሀድያ ዞን ባድዋቾ ወረዳና ሾኔ ከተማ በደሞዝ ምክኒያት ተቋርጦ የነበረዉ የትምህርትና ህክምና አገልግሎት ቢጀምርም መንግስት ቃል የገባልን ውዝፍ የደሞዝና የዱቲ ክፍያዎች አልተከፈለንም ሲሉ ቅሬታ አቅርበዋል።

በመምህራን በኩል " ከዞኑ የትምህርት አመራሮች ጋር በተደረሰ መግባባት ያልተከፈሉ ወራቶች ቀስ በቀስ ሊከፈለን ተስማምተን ብንጀምርም እየተከፈለን ያለዉ ስራ ከጀመርንበት ወዲህ ያለዉ ብቻ  በመሆኑ ደሞዝ በቆመባቸው ወራት የገባነዉን እዳ መክፈል አልቻልነም " ሲሉ መምህራን ያለቸውን ቅሬታ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አቅርበዋል።

በዚህ ጉዳይ ላይ አስተያየታቸዉን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የሾኔ ከተማ መምህራን ማህበር ሊቀመንበር አቶ ከበደ መሊሶ የመማር ማስተማር ስራዉ አሁን ላይ #በአግባቡ እየተካሄደና ደሞዝ እየተከፈለ ቢሆንም የመምህራን የተጠራቀመ ደሞዝ ከተለያዩ ገቢዎች ተሰብስቦ እንደሚከፈል ቃል በተገባዉ መሰረት አልተከፈለም በማለት የመምህራኑ ቅሬታ ትክክል መሆኑን አረጋግጠዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የዞኑን ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ለማነጋገር ተደጋጋሚ ጥረት ቢያደርግም አልተሳካም።

በሌላ በኩል " ቀሪ ደሞዛችንና የዲውቲ ክፍያዎች አልተከፈለንም  " ያሉ የሾኔ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ሰራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።

" መንግስት ቀሪ ያልተከፈለ ደመወዛችንን ከ2012 ዓ/ም  ጀምሮ የተሰበሰቡ ዱቲዎች ድረስ ሊከፍለን ይገባል " ሲሉም ጠይቀዋል።

በዚህም ጉዳይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሾኔ ሆስፒታል ሜዲካል ዳይሬክተር ዶክተር ተድላ አካሉን ጠይቋን።

ዶክተር ተድላ ፤ የህክምና ባለሙያዎች ቅሬታ ተገቢ መሆኑንና ችግሩ መኖሩን አረጋግጠዋል።

በበኩላቸዉ ከ2012 ጀምሮ የተጓተተ የዱቲ ክፍያን ጨምሮ የሰራተኛ ማትጊያ ተጨማሪ ክፍያዎችን ለመክፈል ከሀድያ ልማት ማህበር ጋር እየተመካከሩ መሆኑን ገልጸዉ የዘገየዉ የዚህ ወር ደሞዝም በፍጥነት እንዲከፈል ስራዎች እየተሰሩ መሆናቸዉን ገልጸዋል።

መረጃው ተዘጋጅቶ የተላከው በሀዋሳ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
#ትግራይ

መሻሻል ታይቶበት የነበረው የትግራይ ከተሞች የፀጥታ ሁኔታ እንደገና አሳሳቢነቱ መጨመሩ ተነግሯል።

በአንድ ሳምንታ ብቻ በሁለት ከተሞች ሁለት ሰዎች በሰለት በመወጋት እና በድንጋይ በመመታት ተገድለዋል።

በአሰቃቂ አገዳደል ህይወታቸው ያለፈው የዓዲግራት እና የሽረ እንዳስላሰ ከተሞች ወጣት ነዋሪዎች ናቸው።

የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል እስከ አሁን ባለው መረጃ በሟቾች ተጠርጥሮ አስከ አሁን በቁጥጥር ስር የዋለ የለም።

ሟች የዓዲግራት ከተማ ነዋሪ  ደስታኣለም ነጋሽ ከቤተሰቡ አምሽቶ ወደ ቤቱ በመኪና ሲጓዝ ፤ የመኪና መንገድ በድንጋይ ዘግተው በማውረድ ዘራፊዎቹ ሲገድሉት አብሮት የነበረ ሌላ ሰው ሊያመልጥ ችሏል።

ግድያው የተፈፀመው ህዳር 30 ቀን 2016 ዓ.ም ከምሽቱ 3:00 ሰዓት  አከባቢ ነው። 

ሟች ወጣት ጋይም የሽረ እንዳስላሰ ከተማ ነዋሪ ነበር። ከጓደኞቹ ሲዝናና አምሽቶ ወደ ቤቱ ሲጓዝ በከተማው ቀበሌ 02 ልዩ ቦታ ማይ ሎሚን ሆቴል በተባለ አከባቢ በስለት ወግተው በድንጋይ ደብድበው ጥለውት አመልጠዋል።

ወጣት ጋይም ህይወቱ ሳታልፍ ሰዎች ደርሰው ወደ ሆስፒታል ሊመውሰድ ቢጥሩም የደረሰበት ድብደባ ከባድ ነበርና መትረፍ አልቻለም። አሰቃቂ ግድያው የተፈፀመው ታህሳስ  8/2016 ዓ.ም ነው።

ታህሳስ 9 እና 10/2016 ዓ.ም የአክሱም ከተማ ነዋሪ የአይን እማኞች እንደሚሉት ከምሽቱ 1:00 ሰዓት አከባቢ የተደራጁ ሌቦች ሁለት ሰዎች በመደብደብ 25 ሺህ ብር ቀምተዋቸዋል።

ታህሳስ 9 /2016 ዓ.ም በመቐለ ከተማ ቀበሌ 17 ልዩ ቦታ ዕዳጋ ብዕራይ (የበሬ ገበያ) በቡድን በመሆን በሬ ሰርቀው ለማረድ ሲሞክሩ ባሰማው ድምፅ በመፍራት ዘራፊዎቹ ሲያመልጡ በሬው በፓሊስ እጅ ገብቶ ባለቤቱ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።

የተለያዩ የትግራይ ከተሞች ነዋሪዎች " ከሚታወቁት የማይታወቁት የዝርፍያና የግድያ ወንጀሎች በርካታ ናቸው " ይላሉ ፤ ስለሆነም የከተሞች የፀጥታ ጉዳይ እጅግ በጣም ትኩረት እንደሚሻ በአፅንኦት አሳስበዋል።

የትግራይ ፓሊስ ኮሚሽን በዚህ ዙሪያ የሚለው ካለ ለማስተናገድ ዝግጁን የሚሰጠው መግለጫ ካለም ተከታትለን እናቀርባለን።

መረጃውን አዘጋጅቶ የላከው የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።
                                      
@tikvahethiopia            
ሁሉም የሚመርጠን በምክንያት ነው! ባሉበት ሆነው የአፖሎ ዲጂታል ባንክን በመጠቀም አነስተኛ ብድር ያለምንም ማስያዣ በአነስተኛ የአገልግሎት ክፍያ ይውሰዱ፡፡

መተግበሪያውን ለማውረድ ሊንኩን ይጠቀሙ።
https://apollo.bankofabyssinia.com/download-apollo

አቢሲንያ  የሁሉም ምርጫ!

#Apollodigitalbank #loan #apolloloan #instantloan
#Apollodigitalproduct #AbyssiniaDigital #Abyssiniabank #poweredbybankofabyssinia #BankofAbyssinia #የሁሉም_ምርጫ