TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#AfricanDevelopmentBank

የአፍሪካ ልማት ባንክ ዓለም አቀፍ ሰራተኞቹን በአስቸኳይ #ከኢትዮጵያ ሊያስወጣ ነው።

ባንኩ እዚህ ውሳኔ ላይ የደረሰው ከአንድ ወር በፊት ዋና የኢትዮጵያ ተወካዩ እና ሌላ የባንኩ ሰራተኛ ላይ በፀጥታ አካላት ድብደባ መፈፀሙን ተከትሎ ነው።

በወቅቱ ባንኩ ቅሬታውን ለመንግስት አቅርቦ የነበረ ሲሆን መንግስትም አስቸኳይ ማጣራት አድርጎ ውጤቱን ይፋ እንደሚያደርግ ገልፆ ነበር።

አሁን ባንኩ ዓለም አቀፍ ሰራተኞቹን " በአስቸኳይ " ከኢትዮጵያ እንዲወጡ ሊያደርግ የወሰነው ድብደባውን ፈፅመዋል በተባሉት የፀጥታ አካላት ዙርያ ስለተደረገው ምርመራ የኢትዮጵያ መንግስት ለባንኩ መረጃ ባለማጋራቱ እንዲሁም በሰራተኞቹ ዘንድ በደህንነታቸው ዙርያ ሙሉ እምነት ሊያገኝ ባለመቻሉ እንደሆነ የባንኩ ፕሬዝደንት ዶ/ር አኪንዉሚ አዴሲና አሳውቀዋል።

ምንም እንኳን ባንኩ ዓለም አቀፍ ሰራተኞቹን ከኢትዮጵያ በአስቸኳይ ለማስወጣት ውሳኔ ላይ ቢደርስም በኢትዮጵያ ያለው ቢሮው ክፍት ሆኖ እንደሚቆይና ውሳኔው ከኢትዮጵያ የተቀጠሩ ሰራተኞችን እንደማይመለከት ገልጿል።

እነዚህ ከኢትዮጵያ የተቀጠሩ ሰራተኞች በስራ ገበታቸው እንደሚቀጥሉና በባንኩ ሙሉ የስራ ስምሪት ውስጥ / የባንኩ ሰራተኞች ሆነው እንደሚቆዩ ማረጋገጫ ተሰጥቷል።

አንድ ስማቸው እንዲገለፅ ያልፈለጉ የባንኩ የኢትዮጵያ ቢሮ ሰራተኛ ከኢትዮጵያ ባስቸኳይ እንዲወጡ የሚደረጉት ዓለም አቀፍ ሰራተኖች ወደ ደቡብ አፍሪካ እና ኬንያ ሊዛወሩ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።

እንደ ሬውተርስ ዘገባ የአፍሪካ ልማት ባንክ ኢትዮጵያ ውስጥ የ308 ሚልዮን ዶላር ዋጋ ያላቸው ስምንት ፕሮጀክቶች አሉት።

Credit - Journalist Elias Meseret

@tikvahethiopia
አስተማማኝ የባትሪ ቆይታ ከ Tecno Pop 8 !

የTecno ሞባይል ምርት የሆነው Pop 8 በ5000mAh የባትሪ አቅም ለረጅም ሰዐት ያለምንም እንከን ስልኮን መጠቀም የሚያስችል ሲሆን፣ በ6.6 ኢንች ሰፊ ስክሪን ፊልም ቢያዩ፣ ጌም ቢጫወቱ ባትሪው ንቅንቅ አይልም። ከዚም በተጨማሪ በ10 ዋት ፋስት ቻርጅ ቴክኖሎጂ ስልኮን በፍጥነት ቻርጅ ማረግ ያስችላል።

ቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ
#Pop8 #TecnoMobile #TecnoEthiopia
#ኢትዮጵያ

በፕሪቶሪያ የተፈረመው #የሰላም_ስምምነት ለዘላቂ ሰላም አስተዋፅኦ ያደርጋል ? ወይስ አያደርግም ? በሚሉት ነጥቦች ክርክር እና ውይይት እንዲደረግ ከ #USAID በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ " ሀበጋር " (የደበበ ኃ/ገብርኤል የህግ ክርክር ፕሮግራም) ባለፈው ቅዳሜ አንድ የውይይት እና ክርክር መድረክ ተዘጋጅቶ ነበር።

በመድረኩ ላይ የተጋበዙ ምሁራን ፣ የሕግና የፖለቲካ ባለሙያዎች ፣ የፖለቲካ ፖርቲዎች በየፊናቸው ሀሳብ ሲሰጡ ፤ የተለያዩ ጥያቄዎችንም ሲሰነዝሩ ተስተውለዋል።

የታሪክ ምሁር እና የቀድም #የአብን ብሔራዊ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቴዎድሮስ ኃ/ማርያም (ዶ/ር) የፕሪቶሪያው ስምምነት " #ዘላቂ ሰላምን አያመጣም " በማለት፣ እንዲሁም የቀድሞ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አበበ ገ/ህይወት " ስምምነቱ ዘላቂ ሰላም ያመጣል " በማለት ክርክር አድርገዋል።

በአንድ ወገን ያሉት ተሳታፊዎች ስምምነቱ ከነችግሩም ቢሆን ዘላቂ ሰላም ያመጣል፣ በሌላ ወገን ደግሞ ስምምነቱ አሳታፊና ግልፅኝት፣ ተጠያቂነት መርሆችን ካላሟላ ዘላቂ የሆነ ሰላም ሊመያመጣ አይችልም ፣ ቀድሞውንም አሳታፊነት እና ግልጸኝነት የጎደለው ነው በማለት ሀሳባቸውን አቅርበዋል።

በመድረኩ ፦

- የፕሪቶሪያው ስምምነት ዘላቂ ሰላም ያመጣል ? አያመጣም ?
- የተፈናቃዮች ጉዳይ
- የራያ እና ወልቃይት ጉዳይ ተነስተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ክርክርና ውይይት መድረኩ የተሳተፉ አካላትም አነጋግሯል።

ያንብቡ - https://telegra.ph/Tikvah-Ethiopia-12-19
#GERD🇪🇹

" ግብፅ #የቅኝ_ግዛት ዘመን አስተሳሰቧን ይዛ በመቀጠል ወደ ስምምነትና ትብብር የሚወስደውን መንገድ ዘግታለች " - ኢትዮጵያ

ባለፉት ቀናት ኢትዮጵያ፣ ግብፅ እና ሱዳን አዲስ አበባ ውስጥ የሕዳሴ ግድብ የውሃ አሞላል እንዲሁም ዓመታዊ የሥራ ሂደትን የተመለከተ መመሪያ ላይ የሦስትዮሽ ድርድር ሲያካሂዱ ነበር።

ድርድሩ ያለ ስምምነት ነው የተጠናቀቀው።

ኢትዮጵያ ምን አለች ?

- ኢትዮጵያ በሰላማዊ መንገድ እና በፍትሐዊ ድርድር የሶስቱን ሀገራት ጥቅም የሚያስጠብቅ የመፍትሔ ሀሳብ ላይ ለመድረስ ያላትን ቁርጠኝነት ይዛ እንደምትቀጥል ገልጻለች።

- አራት ዙር ድርድር ተካሂዷል ፤ ይህ ድርድር የተካሄደው በጠ/ሚ ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና በፕሬዚዳንት አብዱልፈታህ ኤል ሲሲ የጋራ መግባባት ነው።

- በአራት ዙሮች ኢትዮጵያ ከታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት ጋር ልዩነቶችን ለመፍታትና የሰላም ስምምነት ላይ ለመድረስ ጥረት አድርጋለች።

- ግብፅ #የቅኝ_ግዛት ዘመን አስተሳሰቧን ይዛ በመቀጠል ወደ ስምምነትና ትብብር የሚወስደውን መንገድ ዘግታለች።

- የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመጀመሪያ አሞላል እና ዓመታዊ አሰራር መመሪያ እና ደንቦች ላይ የተደረገው ድርድር በሶስቱ ሀገራት መካከል መተማመን ለመፍጠር እንጂ በአባይ ውሃ አጠቃቀም ላይ የኢትዮጵያን መብት ለመንጠቅ ያለመ አይደለም።

- ኢትዮጵያ የውሃ ሀብቷን በፍትሃዊና ምክንያታዊ አጠቃቀም መርህ ላይ በመመስረት የአሁንና የመጪውን ትውልድ ፍላጎት ለማሟላት ጥረቷን አጠናክራ ትቀጥላለች።

- አራተኛው ዙር ድርድር ከተጠናቀቀ በኋላ የተባበሩት መንግስታት ድርጅትን ቻርተር እና የአፍሪካ ህብረት ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌን የሚጻረር መግለጫ ግብጽ አውጥታለች። ኢትዮጵያ በግብፅ በኩል የቀረበባትን የተሳሳተ መረጃ አትቀበለውም።

ግብፅ ምን እያለች ነው ?

* " ኢትዮጵያ የሦስቱንም አገራት ጥቅም ሊያስጠብቅ እና ሊያስማማ የሚችል የሕግም ሆነ የቴክኒክ መፍትሄዎችን ለመቀበል ዝግጁ አይደለችም " የሚል ነገር ይዛ ብቅ ብላለች።

* " የግድቡን አሞላል እና ኦፕሬሽን በቅርበት በመከታተል መብቴን አስከብራለሁ " ስትልም ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥታለች።

* ግብፅ " በግድቡ ምክንያት የትኛውም አይነት ጉዳት ቢደርስብኝ በዓለም አቀፍ ቻርተሮች እና ስምምነቶች መሠረት የውሃ ድርሻዬን እና ብሔራዊ ደኅንነቴን የመጠበቅ መብቴ የተጠበቀ ነው " ስትልም መግለጫ አውጥታለች።

🇪🇹 ኢትዮጵያ #በተደጋጋሚ ጊዜ አንዳቸውም የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት በአባይ ግድብ ምክንያት ጉዳት እንደማይደርስባቸው ይልቁንም እነሱኑ እንደሚጠቅም አሳውቃለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትግራይ የትግራይ የትምህርት ጥራት ማረጋገጫ ኤጀንሲ ፤ ሁሉም የወረዳ ትምህርት ፅህፈት ቤቶች የ2016 ዓ.ም አገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ፈተና ምዝገባ እንዲያካሂዱ አዘዘ። የ12ኛ ክልፍ ፈተና በጥር ወር ውስጥ እንደሚሰጥም አሳውቋል። ኤጀንሲው ህዳር 12/2016 ዓ.ም ለሁሉም የክልሉ የወረዳ የትምህርት ፅህፈት ቤቶች በላከው ሰርኩላር ደብዳቤ እንደስታወቀው ፤ በጦርነቱ ምክንያት ከመላ አገር በትግራይ…
#Tigray

የ12ኛ ክፍል ፈተና ተራዘመ።

" በሚቀጥለው ጥር ወር 2016 ዓ.ም ለመስጠት የታቀደው የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ላልታወቀ ጊዜ ተራዝሟል " ሲል የትግራይ ትምህርት ቢሮ አሳውቋል።

ቢሮው ለሚድያ ባሰራጨው ፅሑፍ እንዳለው ፤ የትግራይ ትምህርት ከትምህርት ሚኒስቴር በመግባባት በክልሉ በነበረው ደም አፋሳሽ ጦርነት ምክንያት ሳይሰጥ የቆየው የ12ኛ ከፍል አገር አቀፍ ፈተና መስከረም 29/2016 ዓ.ም ፣ ጥር 6 /2016 ዓ.ም እና ግንቦት 2016 ዓ.ም ለመስጠት አቅዶ በሚድያ ለህዝብ ይፋ ማድረጉ አስታውሷል።

ይሁን እንጂ በሚቀጥለው ጥር 6/2016 ዓ.ም ለመስጠት ያቀደው የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ላልተወሰነ ጊዜ ማራዘሙ ታህሳሰ 9/2016 ዓ.ም ይፋ ባደረገው ደብዳቤ አስታውቋል።

ቢሮው ፈተናውን ለማራዘም ያስገደዱት ሶስት ምክንያቶች ዘርዝሯል። እነሱም ፦

1. ፈተና የሚሰጥባቸው ዩኒቨርስቲዎች ዘግይተው ተማሪዎች በመቀበላቸው ምክንያት ሊሰጥ የታቀደው ፈተና ዩኒቨርስቲዎቹ ካወጡት የትምህርት ፕሮግራም የማይጣጣም በመሆኑ፤

2. የአገር አቀፍ የትምህርት ፈተናና ምዘና አገልግሎት የዝግጅት ጊዜ እጥረት እንደገጠመው በመግለፁ፤

3. ተማሪዎች ለፈተና መዘጋጃ የሚሆን የጊዜ እጥረት መኖሩ በመረዳት፤

ጥር 6/2016 ዓ.ም ለመስጠት የታቀደው የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ላልተወሰነ ጊዜ ተራዝሟል ብሏል። 

በተያያዘ ከታህሳስ 18 አስከ 20/2016 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥ ሲሆን ፈተናውን ለመፈተን 60 ሺህ ተማሪዎች መመዝገባቸው ቢሮው ማስታወቁ ጠቅሶ የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።
                  
@tikvahethiopia            
#GlobalBankEthiopia

ከፊታችን ቅዳሜ ጀምሮ ለምናዘጋጃቸው የጥያቄ ውድድሮች የቴሌግራም ገፃችንን https://publielectoral.lat/Globalbankethiopia123 በመቀላቀል ይሳተፉ! ይሸለሙ!
#SafaricomEthiopia

ቅመም ITEL PROን እንግዛ ፤ ለኛ በተሰራ ቀላል እና ቀልጣፋ ስልክ ማርሻችንን ቀይረን ዲጂታል አለሙን እንቀላቀል።

ፌስቡክ፦ https://www.facebook.com/SafaricomET
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/safaricomet/
ትዊተር- https://twitter.com/SafaricomET
ሊንክዲን- https://www.linkedin.com/company/safaricom-ethiopia/
ቴሌግራም- https://publielectoral.lat/Safaricom_Ethiopia_PLC

#SafaricomEthiopia
#FurtherAheadTogether
" ወንጀሉ እየረቀቀ በመምጣቱ ከህብረተሰቡ ጋር ለመስራት የሚያስችል አሰራር ተዘርግቷል " - የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ

➡️ ጥቆማ መስጫ ነፃ የስልክ መስመር  6073

የአዲስ አበባ ፍትህ ቢሮ ከዓለም አቀፍ ፍልሰተኞች ድርጅት(IOM) በጋራ በመተባበር  በሰው የመነገድ ሰውን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር ወንጀል ለመከላከል የሚያስችለውን አሰራር በመዘርጋት ህብረተሰቡ መረጃ እንዲሰጥ ጥሪ አቀረበ።

ቢሮው ከተማው የወንጀሉ መነሻ፣ መተላለፊያና መዳረሻ በመሆኑ ወንጀሉ የሚፈፀመው በህብረተሰቡ ውስጥ በመሆኑ  በጋራ መስራት ያስፈልጋል ብሏል።

ወንጀሉ እየረቀቀ እና እየተወሳሰበ መምጣቱን የገለፀው ቢሮው ከህብረተሰቡ ጋር ለመስራት የሚያስችለውን አሰራር ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር መዘርጋቱን ይፋ አድርጓል።

በዚህም ፤ ህብረተሰቡ ወንጀሉን በጋራ ለመከላከል እንዲቻል በነጻ የስልክ መስመር 6073 ላይ መረጃ በመስጠት እንዲተባበር  ጥሪ አቅርቧል።

በሌላ በኩል ፥ ወንጀሉን በትብብር መከላከል የሚያስችሉ የተለያዩ አደረጃጀቶችን እስከ ወረዳ ድረስ በማደራጀት ወንጀሉን በተመለከተ  ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የግንዛቤ ፈጠራ ስራ በመስራት ላይ እንዳለ ይፋ አድርጓል።

@tikvahethiopia
" ለአላህ ብላችሁ ተባበሩኝ እያለቀስኩ ነው…ልጄ ልትገደልብኝ ነው አስመጡልኝ " - አረጋዊያኖቹ የለይላ  አባትና እናት

ከአሰሪዎቿ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ግጭት ተፈጥሮ በመካከል የአንድ ታዳጊ ሕይወት በማለፉ በሳዑዲ መንግሥት ሕግ መሠረት የሞት ፍርድ የተፈረደባት ኢትዮጵያዊት የሟች ቤተሰቦች የሞት ፍርዱ ወደ ካሳ እንዲቀየር ተስማምተዋል።

በዚህም የተጠየቀው 2 ሚሊዮን ሪያል ከወዳድ ዘመድ ተሰብስቧል። ይሁን እንጂ ገንዘቡ ቢሰበስብም የሚላከው በመንግሥት በኩል በመሆኑና ገና ስላልተላከ ፍርደኛዋ በሳዑዲ የሞት ፍርድ እየተጠባበቀች መሆኑን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከቤተሰቦቿ ገለጻ ተረድቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸው አረጋዊ የፍርደኛዋ አባት አቶ ኑርሰቦ፣ " ለአላህ ብላችሁ ተባበሩኝ #እያለቀስኩ ነው። እናቶች፣ አባቶች እባካችሁ ተባበሩኝ። የኢትዮጵያ ልጆች፣ የዓለም ልጆች ተባበሩኝ እባካችሁ ትመጣልኛለች እያልኩ 11 ዓመታት ሙሉ ጠበኳት እባካችሁ " ሲሉ እንባቸውን እያፈሰሱ ተማጽነዋል።

" ልጄን ልትገደልብኝ ነው አስመጡልኝ " ያሉት፣ የፍርደኛዋ አረጋዊት እናት ወ/ሮ ነፊሳ ሙሳ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ መንግሥት ከወዳጅ ዘመድ የተሰበሰበውን ገንዘብ በባንክ በኩል ወደ ሳዑዲ መንግሥት በፍጥነት በመላክ ልጃቸውን ከሞት እንዲታደግላቸው በአጽንኦት ጠይቀዋል።

የ21 ዓመቷ ለይላ ኑርሰቦ ሰርቸ እለወጣለሁ በሚል ተስፋ ከኢትዮጵያ ወደ ሳዑድ አረቢያ ከወጣች 11 ዓመታትን እንዳስቆጥረች ወላጆቿ አስረድተዋል። 

ይሁን እንጂ በሳዑዲ አረቢያ ከአሰሪዎቿ ጋ በተፈጠረ ግጭት የ11 ዓመት ታዳጊ በፀቡ ወቅት በመጎዳቱ  #ለአምስት_ወራት በሆስፒታል ሲረዳ ቢቆይም ሕይወቱን ማትረፍ አልተቻለም።

ይህን ተከትሎም 'የገደለ ይገደል' በሚል የሳዑዲ ሕግ ለይላ ነፍስ ማጥፋት ወንጀል ለ11 ዓመታት እስራትና የሞት ፍርድ እንደተፈረደባት ቤተሰቦቿ እንዲሁም የቲም ለይላ አስተባባሪዎች ገልጸዋል።

እንደ ገለጻው ከሆነ፣ የሟች ቤተሰቦች የሞት ፍርድ በካሳ ክፍያ እንዲቀየር ተስማምተዋል።

በዚህም 2 ሚሊዮን ሪያል፣ በኢትዮጵያ ብር ሲሰላ ደግሞ ከ30 ሚሊዮን ብር በላይ እንዲከፈላቸው ተብሎ በሳዑዲ መንግሥት ውሳኔ ተላልፎበታል።

ወዳጅ ዘመድ፣ በጎ አድራጊ ድርጆቶች ድጋፋ እንዲያደርጉ በማኀበራዊ ሚዲያ በተደረገ የ54 ቀናት ዘመቻ በቤተሰቦቿ በኢትዮጵያ በተከፈተ የባንክ አካውንት 30 ሚሊየን ብር፣ በሳውዲ በሟች ቤተሰቦችና በፍርደኛዋ በተከፈተ የባንክ አካውንት 230,000 ሪያል ተሰብስቧል።

መንግሥት የተሰባሰበውን ገንዘብ በፍጥነት ካልከ #ከ39 ቀናት በኋላ ለይላ የሞት ፍርዱ ሊፈጸምባት እንደሚችል በመግለጽ ቤተሰቦቿ እርዳታ እንዲደረግላቸው ተማጽነዋል።

በዛሬው ዕለት በሸራተን ሆቴል በተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ የ'ለይላን እንታደጋት' የሶሻል ሚዲያ ንቅናቄ፣ "በሳዑዲ የሞት ፍርድ የተፈረደባት እህታችንን እንታደጋት" የሚል ጥሪ ተላልፏል።

ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
የማባያ ምርጫችሁ በቀኑ ይወሰናል? ለሀሙስ የሚሆን ቅመም የትኛው ነው? ከ #ሰንቺፕስ 😋 ጋር #ሰኒሞመንትስ ☀️
What’s your tip for a dip? Which one goes best for a Thursday? - with #SunChips 😋 and #SunnyMoments. ☀️

Facebook: https://www.facebook.com/sunchipsethiopia
Instagram: https://instagram.com/sunchipsethiopia 
#AddisAbaba

" ፈተናውን ብዙዎቹ ሊያልፉ ይችላል የሚል ግምት ነው የተያዘው " - የፐብሊክ ሰርቪስ እና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በአንድ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ውስጥ ከሚኖሩ ዳይሬክተሮች እና ቡድን መሪዎች መካከል #ተመሳሳይ የብሔር ማንነት ያላቸው አመራሮች ብዛት ከ40 በመቶ እንዳይበልጥ ሊያደርግ መሆኑ ተሰምቷል።

በቅርቡ ለሚተገብረው #የሠራተኞች_ድልድል ሲባል ከ14 ሺህ በላይ የከተማ አስተደደሩ ሠራተኞች ነገ አርብ ታኅሣሥ 12/2016 ዓ.ም. ለፈተና ይቀመጣሉ።

ከማዕከል እስከ ወረዳ ያሉት ተቋማትን አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻል ባለፉት ሳምንታት ከሠራተኞቹ ጋር ውይይት ሲያደርግ ቆይቷል ተብሏል።

163 ሺህ ገደማ ሠራተኞች በስሩ ያሉት አስተዳደሩ ፤ በሚተገበረው ለውጥ ውስጥ ከተካተቱ ጉዳዮች መካከል የከተማዋን የመንግሥት ሠራተኞችን በአዲስ መልኩ መደልደል የሚለው ይገኝበታል።

ለለውጡ ትግበራ ተብሎ የተዘጋጀ #የሥልጠና_ሰነድ ምን ይላል ?

-አሁን በመጀመሪያው ዙር ድልድል እንዲተገበርባቸው የተመረጡት አስራ ስድስት (16) ተቋማት ናቸው። ከእነዚህም መካከል ፦

* የአዲስ አበባ ከተማ መሬት ልማት እና አስተዳደር፣
* ቤቶች ልማት እና አስተዳደር፣ ትራንስፖርት፣
* ፐብሊክ ሰርቨሲ እና ሰው ሀብት ልማት፣
* ፕላን እና ልማት፣
* ሥራ እና ክህሎት፣
* ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮዎች
* ቤቶች ኮርፖሬሽን፣
* ኅብረት ሥራ ኮሚሽን እንዲሁም ሌሎች የከተማይቱ ኤጀንሲዎች እና ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቶች ይገኙበታል።

- የተዘረዘሩት መስሪያ ቤቶች ድልድል የሚደረግባቸው በማዕከል ቢሮዎቻቸው ብቻ ሳይሆን ክፍለ ከተማ እና ወረዳ ላይ ባሉ ጽህፈት ቤቶቻቸው ጭምር ነው።

የአዲስ አበባ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ቢሮ ኃላፊው ዶ/ር ጣሰው ገብሬ ምን አሉ ?

° ከላይ የዘረዘሩት መስሪያ ቤቶች ለመጀመሪያው ዙር ትግበራ የተመረጡት ብዙ ተገልጋይ የሚያስተናግዱ እንዲሁም ብልሹ አሰራር እና የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ብዙ መጓደል ያለባቸው በመሆናቸው ነው።

° የሠራተኞች ድልድል ከመከናወኑ በፊት የእነዚህ መ/ቤቶች ሠራተኞች ለፈተና ይቀመጣሉ።

° ፈተና ለመስጠት የታቀደው የሠራተኞቹን የብቃት ደረጃ ለማረጋገጥ ነው።

° ፈተናው የባህሪ እና የቴክኒክ ምዘናዎችን የያዘ ነው። የሚሰጠው የቴክኒክ ምዘና ሠራተኞቹ ከሚሠሩት ሥራ ጋር ግንኙነት ያለው ነው። የባህሪው ፈተና ደግሞ አገልግሎት አሰጣጡን የሚፈታተኑ የባህሪ ችግሮች ስላሉ ያንን ክፍተት ለመሙላት አመላካች እንዲሆን ተስቦ የተዘጋጀ ነው።

° የምዘና ፈተናው የተዘጋጀው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ በጋራ ትብብር ነው።

° ፈተናው የሚሰጠው በዩኒቨርስቲ / በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ነው።

° እስካሁን ባለው መረጃም ነገ ፈተናውን የሚወስዱ ሠራተኞች ቁጥር ከ14 ሺህ በላይ ነው።

° ፈተናውን የማያልፉ ሠራተኞች እንዳይኖሩ ዝግጅት እንዲያደርጉ፣ እንዲያጠኑ ተነግሯል። ፈተናው ለማለፍ በሚያስቸግር መንገድ በጣም የተወሳሰበ፣ አብስትራክት እና ንድፈ ሀሳባዊ የሆነ ሳይሆን የሠራተኞችን አቅም ለመለካት አመላካች ሆኖ ነው የተዘጋጀ ነው።

° ብዙዎቹ ሊያልፉ ይችላል የሚል ግምት ነው የተያዘው።

የሪፎርም ሥልጠና ሰነዱ ምን ይላል ?

- የከተማ አስተዳደሩ ባለሙያዎች ፈተናውን ለማለፍ ከ50 በመቶ በላይ ማምጣት ይጠበቅባቸዋል።

- ከዚህ የማለፊያ ውጤት በታች የሆነ ነጥብ ያገኘ ባለሙያ ከደረጃው ዝቅ ብሎ ባሉት የአስተዳደር እርከኖች ላይ ይመደባል።

- ለዳይሬክተሮች እና ለቡድን መሪዎች የተቀመጠው የፈተና ማለፊያ ነጥብ 60 በመቶ ነው። ይህን ነጥብ የማያስመዘግቡ አመራሮች ለዳይሬክተርነት ወይም ለቡድን መሪነት ኃላፊነት #መወዳደር_አልችሉም

ዶ/ር ጣሰው ገብሬ ፦

ሠራተኞች ፈተናውን ማያልፉ ከሆነ ዝቅ ተደርገው ሊመደቡ ይችላሉ። ድልድሉ ሲያልቅ ሌሎች አማራጮች ታይተው ምን ሊደረግ እንደሚችል የተለያዩ ዘዴዎችን ተጠቅሞ መፍትሄ ይፈለግላቸዋል።

በአዲስ መልኩ #ሠራተኞች ሲደለደሉ ከፈተናም በተጨማሪ ሌሎች መስፈርቶችን ይኖራሉ።

- ሰነዱ የሠራተኞች ድልድልን በተመለከተ " ትኩረትን የሚሹ አዳዲስ ጉዳዮች " በሚል ካስቀመጣቸው ጉዳዮች መካከል አንዱ የብሔር ብሔረሰቦች ስብጥር ጉዳይ ነው።

- ድልድሉ ሲከናወን " ሕብረ ብሔራዊነትና አካታችነት በጥንቃቄ " መተግበር እንዳለበት በሰነዱ ላይ ሰፍሯል።

- " አካታችነትና ፍትሐዊነትን " በሚመለከተው የሰነዱ ክፍል ላይ በዳይሬክተርነት እና ቡድን መሪነት የሥራ መደቦች ላይ አመራሮች ሲመደቡ " የሜሪት ሥርዓት " ይጠበቃል።

- የአመራሮች ድልድል "የብሔር ብሔረሰብ ስብጥርን ባካተተ እና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ባረጋገጠ መልኩ " ይከናወናል።

- በመ/ቤቱ ካሉ የሥራ መደቦች መካከል በተመሳሳይ ማንነት የተያዙት ከ40 በመቶ መብለጥ የለባቸውም።

- መ/ቤቶቹ ድልድሉን ሲያከናውኑ ይህንን #የብሔር ስብጥሩን ለመጠበቅ እንዲችሉ " ብቃት ያላቸውን ሠራተኞች ከሌሎች መ/ ቤቶች በመለየት በዝውውር እንዲሟሉ " ይደረጋል።

ዶ/ር ጣሰው ገብሬ ፦

ከ40% መብለጥ የለበትም በሚል የተቀመጠው አሠራር፤ የሚተገበረው የቡድን መሪዎች እንዲሁም የዳይሬክተሮች ድልድል ላይ ብቻ ነው።

በዚህ ድልድል ወደ #ሠራተኛው የወረደ እንደዚህ ዓይነት ነገር የለም። የድልድል ደንቡ ውስጥም የለም።

የተመሳሳይ ማንነት ያላቸው ከተወሰነ ፐርሰንት በላይ መሆን የለበትም የሚለው ለዳይሬክተሮች እና ለቡድን መሪዎች ነው።

ከተማዋ የአገሪቱ ዋና ከተማ ናት። ብዙ ብሔር፣ ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ያሉባት ስለሆነች ያንን ሥዕል የሚያሳይ እንዲሆን መደረግ ስላለበት የተቀመጠ ነገር ነው።

ይህ የአገልግሎት አሰጣጥ ሪፎርምና የሠራተኞች ድልድል እስከ ታኅሣሥ 25 ቀን 2016 ዓ.ም. ድረስ ለማጠናቀቅ በጊዜያዊነት ዕቅድ ተይዟል።

ይህ መረጃ #ባለቤትነቱ የቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ነው።

@tikvahethiopia
#TECNO_Pop8 !

የስልኮን አቅም በእጥፍ ጨምሮ የፈለጉት አገልገሎት በበቂ ሁኔታ ለመከወን የተመረተ ሲሆን አይን ውስጥ ከሚገባ ልዩ ዲዛይን ጋር በማጣመር አዲሱ Pop 8 ከTECNO ሞባይል ቀርብሎታል!

ቴክኖ ሞባይል ኢትዮጵያ
#Pop8 #TecnoMobile #TecnoEthiopia
#CBE 

 ገንዘብ ነክ ያልሆኑ አገልግሎቶችን
በሲቢኢ ሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ይጠቀሙ!
*


•  እለታዊ የውጭ ምንዛሬ መረጃ፣
•  የባንካችንን አገልግሎት መስጫ ስፍራዎች መጠቆሚያ፣
•  አስተያየት መስጫ፣
•  ለሌሎችም ገንዘብ ነክ ያልሆኑ አገልግሎቶች

የሲቢኢ ሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ብቻ በቂ ነው!

የሞባይል መተግበሪያውን ከፍተው ውደውስጥ ሳይገቡ አገልግሎቶቹን ያገኛሉ፡፡

የሲቢኢ ሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያ ለማውረድ፡
•  ለአንድሮይድ ስልኮች፡- https://play.google.com/store/search?q=cbe%20mobile&c=apps
•  ለአይፎን ስልኮች፡- https://apps.apple.com/us/app/cbe-mobile-banking-new/id1534203410

***  
የፌስቡክ እና የቴሌግራም ገፆቻችንን ይቀላቀሉ!  
• Facebook፡- https://www.facebook.com/combanketh  
• Telegram፡- https://publielectoral.lat/combankethofficial
#HawassaUniversity

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ሁኔታ በዝርፊያ እየተፈተነ ይገኛል።

አላግባብ ለእስር ታዳረግን ያሉ ሰራተኞችም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ አቅርበዋል።

ለአመታት በሚሰጠዉ ትምህርትና ለማህበረሰቡ በሚያደርገዉ ድጋፍ  የሚታወቀዉ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በዝርፊያ ምክኒያት አየተፈተነ ነዉ።

አሁን ላይ ዩኒቨርሲቲዉ ከኮምፒዉተር እስከ ቀላልና ከባድ ማሽኖች ከመንገድ ላይ መብራት እስከ ግድግዳ ላይ የተገጠሙ ሶኬቶች ሳይቀር አየተዘረፈበት ሲሆን ዳፋዉ የደረሳቸዉ ተማሪዎችም ዘግተዉት የወጡት በር እየተሰበረ ከአልባሳት እስከ ኤሌክትሮኒክስ ከመማሪያ ቁስ እስከ መመረቂያ ሱፍ መዘረፋቸውን ይጠቁማሉ።

ችግሩን ዉስብስብ ያደረገዉ ደግሞ ዝርፊያዉን ለመመርመር የሚመጡት የህግ አካላት በተደጋጋሚ የግቢዉን ሰራተኞች ማሰራቸዉ እንደሆነ ቅሬታች አቅራቢዎች ገልጸዋል።

ከዚህዉ ጋር በተያያዘ በቅርቡ ለእስር መዳረጉን የገለጸልን የዩኒቨርስቲው መምህር በስሙ የነበሩ ኮምፒዉተሮች ተሰርቀዉ ማደራቸዉን ተከትሎ ለዘጠኝ ቀናት ለእስር መዳረጉን ይገልጻል።

መምህሩ እንደሚገልጸዉ " ስንት ጥበቃ ባለበት ግቢ ዉስጥ እቃ ተሸክሜ መዉጣት እንደማልችል እየታወቀ የተያዝኩበት መንገድ አሳፋሪና አግባብነት የጎደለዉ ነበር " ሲል ያስታዉሳል።

ሌላኛዉ ከዝርፊያ ጋር በተያያዘ ለሁለት ቀናት እስር መዳረጉን  የገለጸልን መምህር ደግሞ መምህራኑ የሚታሰሩት ሌሊት ተሰርቆ በሚያድር እቃ መሆኑን ገልፆ ጉዳዩ ተጣርቶ ከእስር ከተለቀቁ በኋላ ፋይላቸዉን ለመዝጋት የሚወስደዉ ጊዜ ከብዙ ጉዳይ እንደሚያስቀራቸዉና  ለእንግልት እየዳረጋቸዉ መሆኑን ያነሳል።

ከዚህዉ ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ  ምክትል ፕሬዚዳንት ዶር ሳሙኤል ጅሎ እንደሚገልጹት መምህራን ለእስር የሚዳረጉበት ምክኒያት ቢሯቸዉ በቁልፍ ተከፍቶ እቃዉ ጠፍቶ መገኘቱን ተከትሎ የምርመራ ትኩረት እነሱ ላይ የሚያነጣጥር በመሆኑ ነው በማለት ገልጸዋል ።

ዶ/ር ሳሙኤል አክለዉም መምህራን በሚያዙበት ወቅት በአግባቡና በክብር እንዲሆን የጸጥታ አካላትን እያነጋገሩ መሆናቸዉን ገልጸዉ ምርመራዎች በአጭር ጊዜ ዉስጥ እንዲያልቅና ፋይላቸዉ አንዲዘጋም ጥረት እንደሚያደርጉ አመላክተዋል።

በግቢዉ ዉስጥ የሚስተዋለዉን ዝርፊያ ለመቆጣጠር አሁን ላይ የጥበቃ አሰራሩን አዉትሶርስ ለማድረግ ጨረታ ላይ መሆናቸዉን የሚገልጹት ዶክተር ሳሙኤል አዉትሶርስ በማይደረጉ ክፍሎችም የጥበቃ ቁጥር ለመጨመር መታሰቡን ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪ አሁን ላይ ዩኒቨርስቲው ችግሩን ለመቅረፍ አንዳንድ ህንጻዎችን የስማርት ሴኪዉሪቲ ሲስተም መጠቀም መጀመሩን ተከትሎ ለዉጦች ቢኖሩም የስማርት ሲስተሞች የራሳቸዉ ክፍተት መኖርና የችግሩ ስር መስደድ ግን ሁኔታዉን ከባድ ሆኖ ይቀጥል ዘንድ ምክንያት ሆኗል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" በረሃብ የሰዎች ህይወት ስለማለፉ ማረጋገጫ የለንም " - አምባሳደር ሽፈራው ተ/ማርያም (ዶ/ር)

የፌዴራል አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን ኮሚሽነር አምባሳደር ሽፈራው ተክለማርያም (ዶ/ር) " በኢትዮጵያ በረሃብ ምክንያት የሰው ህይወት አልፏል የሚል ማረጋገጫ የለንም " አሉ።

ኮሚሽነሩ ይህንን ያሉት ከፋና ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ነው።

አምባሳደር ሽፈራው ተ/ማርያም (ዶ/ር) ምን አሉ ?

- መንግስት 11 ቢሊዮን ብር መድቦ እየሰራ ነው።

- በፌዴራል የሚደረገው ድጋፍ ክልሎችና ከታች ያሉ መዋቅሮቻቸው እንዲሁም ማህበረሰቡ በሚያደርገው ድጋፍ ላይ ተጨማሪ ነው።

- አንዳንድ አካባቢዎች ላይ የአህል ክምችት ቢኖረንም ትራንስፖርት ሰጪዎች በፀጥታው ምክንያት በፈለግነው ልክ ለማቅረብ አልቻልንም የሚሉት ነገር አለ። ይሄን ከሚመለከታቸው ጋር ተነጋግሮ ይስተካከላል።

- የድርቅ አደጋ ወደ ረሃብ ተቀይሮ የሰውን ህይወት የሚያጠፋበት ደረጃ ላይ እንዲደርስ መዋቅራዊ አደረጃጀታችን የሚፈቅል አይደለም። የቀበሌ፣ የወረዳ ፣ የዞን፣ የክልል መዋቅር አለን የሚችለውን የመደጋገፍ ስራ ይሰራል። ህይወትን የመታደግ ስራ ይሰራል። እዚህ ላይ የፌዴራልም ድጋፍ አለ።

- የድርቅ አደጋ በሚኖርበት ጊዜ የስነምግብ ሁኔታዎችን በመውሰድ ምናልባት በአካባቢው የሚፈጠሩ ወረርሽኝ እና የመሳሰሉት ነገሮች የተለያዩ ነገሮችን ፈጥረው የዜጎቻችንን በሽታን የመቋቋም አቅም አዳክመው በቀላሉ የመሸነፍ እና የመሳሳሉት ጉዳዮች ሊፈጥር ይችላል።

-ሰዎች እንደሚያነሱት ፤ አንዳንድ #ሚዲያዎች እንደሚያነሱት በእህል እጥረት  ፤ ድርቅ ወደ ረሃብ ተቀይሮ የሰውን ህይወት የሚያጠፋበት ደረጃ የራሱ የሆነ ጊዜ አለው የራሱ የሆነ ጊዜ ይወስዳል በዚህ ነው ሰው የሞተው ለማለት #ምርመራ ይፈልጋል። የሰው የሞት ምክንያት ምንድነው ? እንደምናውቀው ሰው በተለያዩ ምክንያቶች ህይወቱ ያልፋል የዛ ህይወቱ ያለፈው ሰው ምክንያቱ ምንድነው ? የሚለውን የመለየት እና የማረጋገጥ ስራ የራሱ የሆነ አካሄድና  መንገድ ይጠይቃል።

- በእኛ በኮሚሽናችን ግምገማ የተመጣጠነ የምግብ አቅርቦት አለመኖር የሚፈጥራቸው ተጋላጭነት ሊኖር እንደሚችል የምንገነዘብ ቢሆንም ግን በረሃብ ምክንያት ህይወቱ ያለፈ ሰው ስለመኖሩ #ማረጋገጫ_የለንም
.
.
በኢትዮጵያ በተለይም በትግራይ እና አማራ ክልሎች ያሉ ከታች ያሉ መዋቅሮች በረሃብ ምክንያት ሰዎች ህይወት እንዳለፈ በተደጋጋሚ መግለፃቸው ይታወሳል።

በትግራይ ክልል የላይኛው መዋቅርም 25 ህፃናትን ጨምሮ 400 ሰዎች በረሃብ ምክንያት ህይወታቸው እንደጠፋ ማሳወቁ አይዘነጋም።

በክልል ከታች እስከላይ ማዋቅር የሚሰጡት እና ነዋሪዎች የሚገልጹት የረሃብ ሁኔታ በፌዴራል አደጋ ስጋት አመራር ቅቡልነት የለውም። ኮሚሽኑ በረሃብ ምክንያት የጠፋ ህይወት ስለመኖሩም ማረጋገጫ የለኝም ብሏል።

ከዚህ ቀደም የፌዴራል አደጋ ሥጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን  " ክልሎች ትኩረት እና የተሻለ ድጋፍ ለማግኘት ሲሉ ' ይህንን ያህል ሰዎች #ሞተውብኛል፣ ይህንን ያህል ተጎድተውብኛል ' የሚል መረጃ ያቀርባሉ " ማለቱ አየዝነጋም።

@tikvahethiopia