TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" ከአፍጥርና ከፆም ሰዓታት በኋላ ደም በመለገስ የደም ሕክምና የሚያስፈልጋቸውን ወገኖች እንታደግ " - ደም ባንክ

በተያዘው የጾም ወቅት በቂ ደም ከማግኘት አንፃር ውስነነት መኖሩን የኢትዮጵያ ደም እና ኅብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡ ባንኩ በዚህ ወቅት በቂ ደም እያገኘ አለመሆኑን ነው ዋና ዳይሬክተር ሀብታሙ ታዬ ለፋብኮ ተናግረዋል።

#ሕይወትን_ማትረፍ ከፆሙ ዓላማ አንፃር ያለው ፋይዳ ትልቅ ስለሆነ ከአፍጥር እንዲሁም ከፆም ሰዓታት በኋላ ደም በመለገስ የደም ሕክምና የሚያስፈልጋቸውን ወገኖች ለመታደግ ሕብረተሰቡ በንቃት ደም እንዲለግስም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ደም የሚያስፈልጋቸውን ዜጎች ሕይወት ለመታደግ በተንቀሳቃሽ እና በቋሚ ቦታዎች እንዲሁም በሥራ ቀናት በትምህርት ቤቶች፣ መንግሥታዊ እና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት በመዘዋወር የደም ማሰባሰብ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡

በአዲስ አበባ ከተማ ቅዳሜ ቅዳሜ አደባባይ ላይ ድንኳን በመትከል የበጎ ፈቃደኛ ደም ለጋሾችን በመቀስቀስ እና እሁድ በቤተ እምነቶች የደም ማሰባሰብ ሥራ እየተከናነ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡

#ኤፍቢሲ

More : @tikvahethmagazine
#ነዳጅ

የትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር በማደያዎች የነዳጅ ግብይትን በዲጂታል የማካሄድ የሙከራ ትግበራ  ሥራ መጀመሩን አሳውቋል።

ግንቦት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ደግሞ በመላ ሀገሪቱ የዲጂታል የነዳጅ ግብይት ይጀመራል ተብሏል።

ዛሬ በአዲስ አበባ ለሙከራ የተጀመረው የዲጂታል ግብይት በሁሉም ተሽከርካሪዎች እና በሁሉም ማደያዎች ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።

ግብይቱ በዲጂታል መሆኑ ምርት እንዳይባክን እና የተሳለጠ ግብይት እንዲኖር እንደሚያደርግ ነው ሚኒስቴሩ የገለፀው።

የነዳጅ ግብይቱ በ #ቴሌብር አማራጭ የሚከናወን ነው የተባለ ሲሆን በዚህ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት ሁሉም የመንግስት እና የግል ተሽከርካሪዎች ቁጥጥር ይደረግባቸዋል ተብሏል።

ሚኒስቴሩ በቅርቡ የትራንስፖርት ትኬት በዲጂታል እንደሚጀመር አሳውቋል።

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
የዒድ አልፈጥር በዓል መቼ ነው ?

የፌዴራል ጠቅላይ ሼሪዓ ፍርድ ቤት ፥ የዒድ አልፈጥር በዓል ጨረቃ ዛሬ ሀሙስ ማታ ከታየች ነገ አርብ ፣ ካልታየች ደግሞ ቅዳሜ ይከበራል ሲል አሳውቋል።

ይህን ያሳወቀው ዛሬ በሰጠው መግለጫ ነው።

1 ሺህ 444ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ፤ ለኢትዮጵያና ለመላው ዓለም ህብረተሰብ የሰላም፣ የደስታና የፍቅር እንዲሆን መልካም ምኞቱን የገለፀው ሼሪዓ ፍርድ ቤቱ ሙስሊሙ ህብረተሰብ በዓሉን ሲያከብር ያጡና የተቸገሩ ወገኖችን በማሰብና በመርዳት እንዲሆን ጥሪ አቅርቧል።

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ለሙዚቃ ስራ ወደ አውሮፓ ሄዶ ጣልያን ፣ ሮም ከተማ ባረፈበት ክፍል ህይወቱ አልፎ የተገኘው የአርቲስት ዳዊት ፍሬው አስክሬን ዛሬ ኢትዮጵያ ገብቷል። ትላንት በሮም ደብረ ፅዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን የፍታት እንዲሁም የአስክሬን ሽንት ፕሮግራም ተካሂዷል። የአርቲስቱ ስርዓተ ቀብር ነገ ግንቦት 6 /2015 ከቀኑ 6 ሰዓት በመንበረ ፀባኦት  ቅድስት ስላሴ ቤተክርስቲያን የሚፈፀም ሲሆን…
#Update

የአርቲስት ዳዊት ፍሬው የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ።

የአርቲስት ዳዊት ፍሬው የቀብር ሥነ-ሥርዓት በዛሬው ዕለት በመንበረ ፀባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተፈጽሟል።

አርቲስት ዳዊት ፍሬው በያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት የሙዚቃ ትምህርቱን 'ሜጀር ክላርኔት' በማድረግ የተመረቀ ሲሆን የአልቶ ሳክስፎን እና ክራር ተጨዋችም ነበር።

በአስደናቂ ክላርኔት ጨዋታው የሚታወቀው ዳዊት ፍሬው በሙዚቃ ትምህርት ቤት ቆይታው፣ የታላላቅ ሙዚቃ አቀናባሪዎች /ኮምፖዘሮችን/ የክላርኔት ሥራዎች ተጫውቷል።

በሙዚቃ መሳሪያ ብቻ የተቀነባበሩ አልበሞችንም ለአድማጮች ማቅረብ ችሏል።

አርቲስት ዳዊት ፍሬው ለሙዚቃ ስራ ወደ አውሮፓ ሄዶ ጣልያን ፣ ሮም ከተማ ውስጥ ባረፈበት ክፍል ህይወቱ አልፎ መገኘቱ ይታወሳል።

Credit : #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#PropertyTax

ኢትዮጵያ ውስጥ " ፕሮፐርቲ ታክስ " እስካሁን እንዳልተጀመረ ነገር ግን ተግባራዊ እንደሚደረግ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ይፋ አደረጉ።

ዶ/ር ዐቢይ ፤ ፕሮፐርቲ ታክስ መላው ኢትዮጵያ ውስጥ በአዲስ አበባ ጨምሮ እንዳልተጀመረ ገልጸው በአ/አ እየተከናወነ ያለው ከዚህ ቀደም የነበረውን የጣሪያ እና ግርግዳ ግብር ህግ በማሻሻል እየተሰበሰበ ያለ ግብር ነው ሲሉ ጠቁመዋል።

" ይህ የተሻሻለው የጣሪያ እና የግድግዳ ግብር ማለት ፕሮፐርቲ ታክስ ማለት አይደለም " ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ " ወደፊት የፕሮፐርቲ ታክስ አዋጅ በዝርዝር የሚታይ ጉዳይ ነው ብለዋል።

" ፕሮፐርቲ ታክስ " ካቢኔው አፅድቆ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀርቦ አዋጁ ፀድቆ ተግባራዊ እንደሚደረግም ጠቁመዋል።

ከጣሪያና ግድግዳ ግብር ጋር በተያያዘ ያለው የታክስ ምንጭ በአዲስ አበባ ነዋሪዎች ላይ ጉዳት አምጥቶ ያልተገባ ሀብት ወስዶ ከሆነ ቅሬታ የሚሰማበት ስርአት ስላለ በዚያው ስርአት ቅሬታ ቀርቦ ሊታይ እንደሚችልም አስገንዝበዋል።

በአዲስ አበባ እየተሰበሰበ ያለው የጣራ እና የግድግዳ ግብር መሆኑንና ይህም ከ1937ዓ.ም ጀምሮ የመጣ እና ማሻሻያ የተደረገበት ነው ብለዋል፡፡

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
" ዘንድሮ በመደበኛው 667 ሺህ 483 ፤ በግል፣ በማታ እና በርቀት 200 ሺህ 691 ተፈታኞች ፈተና ይወስዳሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

ከ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ብሔራዊ ፈተና ጋር በተያያዘ ባለፈው ዓመት የተስተዋሉ የተለያዩ እንከኖች በዚህኛው ዓመት መስተካከላቸውን የትምሕርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል።

ምዝገባው በማንዋል በመሆኑ ተፈጥሮ የነበረውን የተፈታኞች መረጃ አያያዝ ጥራት ጉድለት ለማረም ዘንድሮ ምዝገባው በበይነ መረብ መካሄዱን አገልግሎቱ ገልጿል።

በተጨማሪም ከዩኒቨርሲቲ ድልድል፣ ዝግጅት እና አቀባበል ጋር በተያያዘ እክሎች የነበሩ ሲሆን ዘንድሮ ችግሩ መቀረፉን አረጋግጧል።

አምና ካጋጠመው ጉድለት በመማር የፈተና ማስፈጸሚያ ማንዋል እና መመሪያውን በማዘጋጀት እና በመከለስ ከባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተደርጓል።

ባለፈው ፈተና ወቅት ተፈታኞችን ማዘጋጀት አለመቻሉ ዋና ችግር እንደነበር የጠቀሰው አገልግሎቱ በዚህ ዓመት በቂ ዝግጅት ስለመደረጉ ገልጿል።

በዚህ ዓመት የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከተመዘገቡት 869 ሺህ 802 ትክክለኛውን የምዝገባ ሂደት ያላሟሉ 1 ሺህ 213 ተፈታኞች ምዝገባ መሠረዙንም ተገልጿል።

ዘንድሮ ፦

- በመደበኛ 667 ሺህ 483
- በግል፣ በማታ እና በርቀት 200 ሺህ 691 ተፈታኞች ፈተና ይወስዳሉ።

ፈተናው በሁለት ዙር በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ይሳጣል።

የመጀመሪያው ዙር ፈተና ከሐምሌ 19 እስከ 21 ቀን፤ ሁለተኛው ዙር ፈተና ደግሞ ከሐምሌ 25 እስከ 28 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚሰጥ አገልግሎቱ አረጋግጧል።

የማኅበራዊ ሣይንስ ተፈታኞች ከሐምሌ 16 እስከ 17 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ እ
የሚገቡ ሲሆን ሐምሌ 18 ገለጻ ይሰጣቸዋል።

የተፈጥሮ ሣይንስ ተፈታኞች ደግሞ ከሐምሌ 22 እስከ 23 ቀን 2015 ዓ.ም ወደ ተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ ገብተው ሐምሌ 24 ቀን ገለጻ ይሰጣቸዋል።

ተፈታኞች ፈተናውን በራሳቸው ጥረት እንዲሠሩ አሳስበው የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ባለፈው ዓመት የፈተና ደንብ ጥሰት የፈጸሙ 17 ሺህ ተፈታኞች ውጤት ሙሉ በሙሉ መሠረዙን አስታውሷል።

Credit : #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NBE የውጭ ምንዛሬ ክፍፍል ላይ ማሻሻያ እንዲደረግ የብሄራዊ ባንክ ቦርድ መወሰኑን " ካፒታል " ጋዜጣ ዘግቧል። በዚህም ውሳኔ መሰረት የውጭ ምንዛሬ ክፍፍሉ ቀደም ሲል ከነበረው 70/30 ወደ 50/50 እንዲስተካከል ተደርጓል። በውሳኔው መሰረት ባንኮች ከውጭ ምንዛሬ ግኝታቸው 50 በመቶ ለብሄራዊ ባንክ 40 በመቶውን የውጭ ምነዛሬውን ላመነጨው አካል እንዲሁም ቀሪውን 10 በመቶ ለባንኮች እንዲከፋፈል…
#NBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ፤ የዋጋ ንረትን ለማርገብ የሚያስችል የገንዘብ ፖሊሲ ማሻሻያ ለማድረግ ወስኗል።

ይህ በተመለከተ የባንኩ ገዥ ማሞ ምህረቱ ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በመግለጫው ምን ምን ነጥቦችን አነሱ ?

- ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እያየለ የመጣውን የዋጋ ንረት ትርጉም ባለው መልኩ ለመቆጣጠር የብሔራዊ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ ውሳኔ አሳልፏል።

- ከውሳኔዎቹ መካከል ለመንግስት የሚሰጠው የቀጥታ ብድር ባለፈው አመት ከተሰጠው ከ1/3ኛ እንዳይበልጥ ይደረጋል።

- መንግስት ቅድሚያ የግምጃ ቤት ሰነድ አማራጭን አሟጦ እንዲጠቀምና አማራጭ ሳይኖር ሲቀር ብቻ የቀጥታ ብድር ይጠቀማል።

- በ2016 ዓ/ም በጀት ዓመት ሰኔ መጨረሻ የሃገር ውስጥ ብድር ዕድገት በ14 በመቶ ጣሪያ ይገደባል። ሁሉም ንግድ ባንኮች የብድር ዕድገት ዕቅዳቸውን በዚህ የብድር ጣሪያ መሰረት እንዲያስተካክሉ ይደረጋል።

- ባንኮች የገንዘብ እጥረት ሲገጥማቸው ከብሄራዊ ባንክ ከሚወስዱት ብድር የብድር ፋሲሊቲ ላይ የሚከፍሉት ወለድ ከ16 በመቶ ወደ 18 በመቶ ከፍ እንዲል ይደረጋል።

- ቁልፍ የሆኑ የወጪ ንግድ ላይ የተሰማሩ ዘርፎች በተለይም በማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ላኪዎችን ለማበረታታት ከዚህ ቀደም የነበረው የውጭ ምንዛሬ የማስተላለፍ ግዴታ ከ70/30 ወደ 50/50 እንዲሻሻል ይደረጋል። ላኪዎች 50 በመቶውን ለብሄራዊ ባንክ እንዲያስገቡ፣ 10 በመቶውን አብረው ለሚሰሩት ባንክ እንዲሰጡ እና 40 በመቶውን ለራሳቸው እንዲጠቀሙ ተወስኗል።

- በ2016 በጀት ዓመት መጨረሻ የዋጋ ንረቱ ከ20 በመቶ በታች እንዲሆንና በ2017 በጀት ዓመት ደግሞ ከ10 በመቶ በታች ለማውረድ ይሰራል።

ህብረተሰቡ ውሳኔውን በመደገፍ የዋጋ ንረቱን ለመቆጣጠር የሚደረገውን እርምጃ እንዲደግፍ ጥሪ ቀርቧል።

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ፈተናው ተራዝሟል ፤ ፈተናው የሚሰጥበትን ጊዜ በቀጣይ እናሳውቃለን " - ትምህርት ሚኒስቴር ከዚህ ቀደም ፈተናቸውን ያልወሠዱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሬሜዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች ፈተና ተራዝሟል። ፈተናው ከነሐሴ 23 እስከ 26/2015 ዓ.ም በኦንላይን ይሰጣል ተብሎ እንደነበር አይዘነጋም። ይሁን እንጂ በኢንተርኔትና ተዛማጅ ምክንያቶች ፈተናው መራዘሙን ቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ…
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር፤ በቅርቡ ይፋ በሚደረግ የፈተና ጊዜ ፈተናቸውን የሚወስዱ እና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ የሚያመጡ የሬሜዲያል ተፈታኞች ቀደም ብለው የሬሜዲያል ፈተና ወስደው የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ካመጡ ተማሪዎች ጋር ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡበት ጊዜ ተመሳሳይ ስለሆነ ስጋት እንዳይገባቸው ብሏል።

በሚኒስቴሩ የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈጻሚ ኤባ ሚጀና (ዶ/ር) ለኤፍቢሲ በሰጡት ቃል ፤ ከነሐሴ 23 እስከ ነሐሴ 26 ቀን 2015 ዓ.ም ሊሰጥ የነበረው የሬሜዲያል ፈተና የተራዘመው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ስላልተጠናቀቁ ነው ብለዋል።

መጠናቀቅ ያለባቸው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን በአግባቡ ለማጠናቀቅ ሲባል የፈተናውን ጊዜ ላልተወሰነ ጊዜ ማራዘም አስፈልጓል ያሉት ዶ/ር ኤባ ፤ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች እንደተጠናቀቁ በቅርቡ ተፈታኞች ለፈተና ስለሚጠሩ ዝግጅት እያደረጉ እንዲጠብቁ አሳስበዋል።

ባለፈው ጊዜ ፈተና ያልወሰዱ እና የማካካሻ ትምህርት ሲከታተሉ የነበሩ 46 ሺህ የሚጠጉ የመንግሥትና የግል ተማሪዎች በቅርቡ ፈተናቸውን እንደሚወስዱ አረጋግጠዋል፡፡

ፈተናውን ወስደው ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት የሚያመጡ የሬሜዲያል ተማሪዎች ቀደም ብለው ከተፈተኑት እኩል ወደ ዩኒቨርሲቲ እንደሚገቡ ዶ/ር ኤባ ሚጄና ገልጸዋል።

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
" የመስቀል ደመራ በዓል ላይ ርችት መተኮስ አይቻልም "- አዲስ አበባ ፖሊስ

የአዲስ አበባ ፖሊስ ለ #ኤፍቢሲ በሰጠው ቃል ፤ የመስቀል ደመራ በዓል ላይ ርችት መተኮስ በፍጹም የተከለከለ መሆኑን አሳውቋል።

ፖሊስ ምን አለ ?

- ህብረተሰቡ በመስቀል ደመራ በዓል ላይ የተከለከሉ ነገሮችን በፍጹም መያዝ አይገባውም። ለሚኖሩ ፍተሻዎችም መተባበር አለበት።

- በየአካባቢው በሚደመሩ ደመራዎች አደጋ እንዳይከሰት ጥንቃቄ ማድረግ ይገባል።

- ከዚህ በፊት ደመራ ተደምሮባቸው የማያውቁ ቦታዎች #የጸብ_መነሻ እንዳይሆኑ የድሮዎቹን መጠቀም ይገባል።

- ርችት መተኮስ በፍጹም ክልል ነው። ክልከላው የተደረገው ርችትን ሽፋን በማድረግ ህገወጦች ህገወጥ የጦር መሳሪያቸውን የሚሞክሩበት ጊዜ በመሆኑ ነው። ርችት ሲተኩስ የተገኘ ግለሰብ ሆነ ተቋም በህግ አግባብ እርምጃ ይወሰድበታል።

@tikvahethiopia
" ከዛሬ ጀምሮ የ24 ሰዓት አገልግሎት ይሰጣል " - ውብአየሁ ማሞ (ኢ/ር)

በአዲስ አበባ ከተማ የሚገኘው " አብርሆት ቤተ -መጻሕፍት " ከዛሬ ጀምሮ የሚሰጠውን አገልግሎት ወደ 24 ሰዓት ማሳደጉን አስታውቋል፡፡

ቤተ-መጻሕፍቱ ከሕዳር 14  ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ምሽቱ ስድስት ሰዓት አገልግሎት ሲሰጥ እንደቆየ የቤተ-መጻሕፍቱ ዋና ዳይሬክተር ውብአየሁ ማሞ (ኢ/ር) ገልጸዋል።

ከዛሬው ዕለት ጀምሮም የ24 ሰዓት አገልግሎት መስጠት ይጀምራል ብለዋል።

የቤተ-መጻሕፍቱ አገልግሎት ፈላጊ ቁጥር  የአገልግሎት ሰዓቱን ለማሻሻል ምክንያት እንደሆነ አመልክተዋል።

በሌላ በኩል ቁጥር 2 የአብርሆት ቤተ-መጻሕፍት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሊገነባ መሆኑ የቤተ-መጻሕፍቱ ዋና ዳይሬክተር ውብአየሁ ማሞ (ኢ/ር) አሳውቀዋል። #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዛሬ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።

በመግለጫው ምን አለ ?

አገልግሎቱ ለተገልጋዮች አዲስ አሰራርን ወደ ስራ ማስገባቱን አሳውቋል።

በበይነ መረብ አማካኝነት ፦
- የትምህርት መረጃ ማጣራት፣
- የትምህርት ማስረጃ ለሌላ ተቋማት መላክ ፣
- ድጋሚ የትምህርት ማስረጃ መውሰድ፣
- የትምህርት ማስረጃን ማረጋገጥ
- በምዝገባ ወቅት የሚያጋጥምን የስም ፊደላትን ጉድለት ማስተካከል ይቻላል ብሏል።

አገልግሎቱን ለማግኘት ተገልጋዮች በቴሌ ብር እና ንግድ ባንክ በኩል ክፍያ መፈፀም እንደሚኖርባቸው አመልክቷል።

ከዚህ በኋላ በመላው ሀገሪቱ በሚገኙ ኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ቅርንጫፎች እና በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ180 ሀገራት፣ በአካል እንዲሁም በውክልና ማግኘት እንደሚቻልም ተገልጿል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ #ከቀጣይ_ወር ጀምሮ ለ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ተፈታኞች ምዝገባ እንደሚጀመርም ይፋ ተደርጓል።

#ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
 
TIKVAH-ETHIOPIA
" የኢትዮጵያ መንግሥት የሶማልያው ፕሬዝዳንት እና ልዑካቸው በስብሰባው ላይ እንዳይገኙ አላደናቀፈም ፤ ወደ ኅብረቱ ቅጥር ጊቢ እንዳይገቡም አልከለከለም " - መንግሥት 37ኛው የአፍሪካ ህብረት ጉባዔ በዛሬው እለት በአዲስ አበባ የተጀመረ ሲሆን የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ " ወደ ስብሰባው እንዳልገባ የመከልከል ሙከራ ተደርጎብኛል " የሚል ክስ አሰምተዋል። ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሃሙድ ከስብሰባው…
#ኢትዮጵያ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም (ዶ/ር) ዛሬ መግለጫ ሰጥተው ነበር።

በዚህም መግለጫቸው የሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀሙድ ትላንት አዲስ አበባ ሆነው ስለሰጡት መግለጫ ምላሽ ሰጥተዋል።

የሶማሊያው ፕሬዝዳንት በሰጡት መግለጫ ፤ " ካረፍኩበት ሆቴል እንዳልወጣ የኢትዮጵያ መንግሥት የፀጥታ ኃይሎች መንገድ ዘጉብኝ ፤ በኃላም ከሌላ ፕሬዜዳንት ጋር (ከጅቡቲ ፕሬዝዳንት ኢሳማኤል ኦማር ጌሌህ) ጋር ሆነን ወደ ጉባኤው ልንገባ ስንል የኢትዮጵያ መንግሥት የፀጥታ ኃይሎች ክልከላ አደረጉብን " የሚል ክስ አሰምተው ነበር።

የሶማልያው ፕሬዜዳንት ለሰጡት መግለጫ አምባሳደር መለስ አለም (ዶ/ር) ምን ምላሽ ሰጡ ?

" እንደ አስተናጋጅ ሀገር ኢትዮጵያ የሁሉንም ሀገራትና መንግስታት መሪዎችን በቆይታቸው ደኅንነታቸውን የመጠበቅ ኃላፊነት አለባት።

ይሁን እንጂ የሶማሊያ ፕሬዚዳት በመንግሥት የተመደቡላቸውን የፀጥታ አካላት አንቀበልም።

ይህ አሠራር (የአዘጋጅ ሀገር የእንግዶችን ደህንነት ማስጠበቅ) በመላው ዓለም የተለመደ ነው። በሶማሊያ ልዑክ በኩል የሆነው ከዚህ በተቃራኒ ነው።

የኢትዮጵያ መንግሥት ለአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ ለመጡ ሁሉም ሀገራትና መንግስታት መሪዎች ያደረገውን የክብር አቀባበል ለሶማሊያ ፕሬዚዳንትም አድርጓል።

ከዚህ በላይ ግን የሶማሊያ ልዑክ የደኅንነት አባላት የጦር መሳሪያ ታጥቀው ወደ አፍሪካ ኅብረት ለመግባት ሲሞክሩ በኅብረቱ የፀጥታ አካላት ተከልክለዋል።

ይህም የሕብረቱን የፀጥታ አካላት የሚመለከት እንጂ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም።

የኢትዮጵያ መንግስትም ከሕብረቱ ቅጥር ግቢ ደሕነታቸውን ከማስጠበቅ ውጭ በሕብረቱ ቅጥር ግቢ እንዳይገቡም የመከልከል ኃላፊነት የለውም።

በሶማሊያ በኩል የተሰጠው መግለጫ በሌሎች የሕብረቱ ተሳታፊ ሀገራት መሪዎች ጭምር ተቀባይነት ያለገኘ እና የተሳሳተ ነው። " #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba

ፒያሳ የሚገኘው የዓድዋ ድል መታሰቢያ ከነገ ጀምሮ ለጎብኚዎች ክፍት እንደሚሆን ተነግሯል።

የድል መታሰቢያው የሚጎበኝበት ዋጋ ዝርዝርም ይፋ ሆኗል።

የጀግኖች ምስለ ቅርፅና ድሉን የሚያወሱ ቁሳቁሶች በመታሰቢያው ለጎብኚዎች ክፍት የሚሆኑ ሲሆን ክፍያው በቴሌ ብር፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መፈፀም ይችላል ተብሏል።

በዚህም መሰረት ፦

ለመደበኛ 150፣
ለተማሪዎች 75
ለልዩ ልዩ 550 ብር እንደሆነ ተገልጿል።

መታሰቢያው ከ2:30 እስከ 11:30 ሰዓት ተኩል ለጎብኚዎች ክፍት ይሆናል። #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ፖሊስ ተጨማሪ 8 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ተፈቀደለት።

ቀሲስ በላይ መኮንን በሃሰተኛ ሰነድ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአፍሪካ ኅብረት የባንክ ሒሳብ ወደ ሌላ የባንክ ሒሳብ ከ6 ሚሊዮን ዶላር በላይ ለማዘዋወር ሲሞክሩ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ይታወሳል።

በተጠረጠሩበት ወንጀል ዛሬ ለ2ኛ ጊዜ የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት አራዳ ምድብ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ቀርበዋል።

ከእሳቸው ጋር ሌሎች 2 ግለሰቦች ያሬድ ፍስሃ እና ጣባ ገናና የተባሉ ቀርበዋል።

ከዚህ ቀደም ለፌዴራል መርማሪ ፖሊስ 7 ቀን መሰጠቱ ይታወሳል።

በዚህ ጊዜ መርማሪ ፖሊስ ምን እንደሰራ ለችሎቱ አስረድቷል።

ፖሊስ ምን አለ ?

- " የምስክሮችን ቃል ተቀብያለሁ። "
- " በተጠርጣሪዎች እጅ ላይ የተገኘ ኤሌክትሮኒክስ ምርመራ እንዲደረግ ለሚመለከተው ተቋም ጠይቂያለሁ። "
- " የቴክኒክ ምርመራ እንዲሰጠኝ በደብዳቤ ጠይቂያለሁ። "
- " ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ ለአፍሪካ ህብረት የሰነድ ማስረጃዎች እንዲሰጠኝ ጠይቂያለሁ። "
- " ተጠርጣሪዎቹ በስማቸው የሚገኙ ሂሳቦችን ለማጣራት ማረጋገጫ እንዲሰጠኝ በደብዳቤ ጠይቂያለሁ። "
- " በወቅቱ የነበረ የካሜራ ቅጂ ጠይቂያለሁ። "
- " ለወንጀል ተግባር የዋለ ተሽከርካሪ ማረጋገጫ ከሚመለከተው ተቋም ጠይቂየለሁ። "
- " በቀሲስ በላይ ሁለት መኖሪያ ቤቶች ላይ ብርበራ አድርጌ በብርበራ የተገኘ የጦር መሳሪያ ህጋዊነት የማረጋገጥ ስራ እየሰራሁ ነው። " ... ብሏል።

የቀሩ ስራዎች ፦
- " ከተለያዩ ተቋማት የሰነድ ማስረጃ መሰብሰብ። "
- " ተጨማሪ ምስክሮችን ቃል መቀበል። "
- " ግብረአበሮችን ተከታትሎ መያዝ። "
- " ተጨማሪ ሀብት የማፍራት ተግባሮች ላይ የማጣራት ስራ መስራት ሌላም ሰፊ የምርመራ ስራ ስለሚያስፈልግ ተጨማሪ የ14 ቀን ጊዜ ቀጠሮ ይሰጠኝ " ብሏል።

የተፈጸመው ድርጊት " ከአፍሪካ ሀገራት ጋር ያለንን መልካም ግንኙነት ጥላሸት የሚቀባ ተግባር ነው " ብሏል።

ተጠርጣሪው ቀሲስ በላይ መኮንንን ጨምሮ ሌሎቹም ተጠርጣሪዎች በ6 ጠበቆች ተወክለው ነው የቀረቡት።

ጠበቆቻቸው ምን አሉ ?

° " የቀረበው የጊዜ ቀጠሮ መጠየቂያ ምክንያቶች ደንበኞቻችን ተጨማሪ በእስር ለማቆየት የሚያስችል አይደለም " ብለዋል።

° " ቀሲስ በላይ የተገኘው የጦር መሳሪያ ህጋዊ ነው። ሀብት ማፍራት ከተጠረጠሩበት ወንጀል ጋር ሊገናኝ አይገባም " ብለዋል።

° " የሃይማኖት አባት መሆናቸው ፣ የልማት ስራ አስተባባሪ በመሆናቸው ፣ ቋሚ አድራሻ ያላቸው በመሆኑ ቢወጡ ከመንግስት ተቋማት የሚመጡ ማስረጃዎችን የማጥፋት አቅም የላቸውም " ብለዋል።

ስለሆነም የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።

ቀሲስ በላይ መኮንን ምን አሉ ?

ወንጀል አለመፈጸማቸውን ገልጸዋል።

ለሀገር እንዲሁም ፖሊስ ተባባሪ መሆናቸውን ተናግረዋል።

➡️ " ምሽት ላይ #እቤቴ_እየሄድኩ ጠዋት ላይ ልምጣላችሁ " በማለት ፖሊስን መጠየቃቸውን ለችሎቱ አስረድተዋል።

ከእሳቸው ጋር አብረው የታሰሩት #ሹፌራቸው እና #አጃቢያቸው እንደሆኑ ገልጸው ምንም የወንጀል ተሳትፎ በሌለበት ሁኔታ ከኔ ጋር ተጨማሪ ጊዜ በእስር ማቆየት ተገቢ አይደለም በማለት የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል።

ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹ ቢወጡ ማስረጃ ሊሰወር ይችላል በማለት የዋስትና ጥያቄያቸውን ተቃውሟል።

የግራ ቀኝ ክርክሩን የተመለከተው ጊዜ ቀጠሮ ችሎቱ ተጠርጣሪው ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ ለጊዜው በማለፍ ለፖሊስ የ8 ቀን የምርመራ ማጣሪያ ጊዜ ፈቅዷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ ባለቤትነቱ ፥ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት (#ኤፍቢሲ) መሆኑን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
#Adama

ተከሳሽ ቶሎሳ ወይም ፍቅሩ አሸናፊ ይባላል።

በአዳማ ከተማ ቦሌ ክፍል ከተማ በተለምዶ ደካ አዲ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ሚያዝያ 21 ቀን 2016 ዓ.ም እናቱን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድሏል።

ተከሳሹ እናቱን በስለት (ቢላዋ) በአሰቃቂ ሁኔታ ወግቶ ነው ህይወታቸውን እንዲያጡ ያደረገው።

ተከሳሹ ድርጊቱን የፈጸመው #በቁማር_የተበላዉን ገንዘብ እናቱ ያላቸውን ንብረት በመሸጥ እንዲተኩለት ለማድረግ ሲል እየደበደበ ያሰቃያቸው እንደነበር ዐቃቤ ሕግ በማስረጃ አረጋግጧል።

በዚህ ብቻ ያላበቃው ተከሳሽ ሚያዚያ 21/ 2016 ዓ/ም ጠዋት በአሰቃቂ ሁኔታ የእናቱ ህይወት እንዲያልፍ በማድረጉ ከባድ የግድያ ወንጀል ክስ ቀርቦበታል።

ጉዳዩን የተመለከተው የአዳማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዛሬ በዋለው ችሎት በሞት እንዲቀጣ ወስኗል።

በተከሳሹ ላይ የተጣለው #የሞት_ፍርድ በአገሪቱ ርዕሰ ብሔር ሲጸድቅ ነው ተፈጻሚ የሚሆነው። #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

ግለሰብን አግተው የዘረፉ የፖሊስ አባላት ላይ ክስ ተመሰረተ።

አንድን ግለሰብ አስገድደው በያዙት ተሽከርካሪ ውስጥ በማገት ዶላርና የተለያዩ ንብረቶቹን ወስደዋል የተባሉ 3 የፖሊስ አባላት ላይ የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ ክስ መስርቷል።

3ቱ የፖሊስ አባላት ፦
ኮንስታብል ክብሩ በለጠ
ረ/ሳጅን ያለምሰው ዱሬ
ረ/ሳጅን ባህረዲን አለሙ ይባላሉ።

1ኛው ተከሳሽ በፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ መምሪያ የተጠርጣሪ አስተዳደር ስር የጥበቃ አባል፣

2ኛው ተከሳሽ የተጠርጣሪ ክትትል እና ኦፕሬሽን ክፍል የኢኮኖሚ ነክ ጉዳዮች ወንጀሎች የፍርድ ቤት አስገዳጅ አባል፣

3ኛው ተከሳሽ በፎረንሲክ ምርመራ መምሪያ ስር በሹፌርነት ሲሰሩ ነበር።

ሰኔ 3 ቀን 2016 ዓ/ም ከቀኑ በ9 ሰዓት አካባቢ በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 8 '  ጆን ጋራዥ  ' አካባቢ ካልተያዘ ሲቪል ከለበሰ ግብረአበራቸው ጋር በመሆን አንድ የግል ተበዳይን አስገድደው 3ኛ ተከሳሽ ለስራ አላማ የተረከበው ተሽከርካሪ ውስጥ በማገት ያስገባሉ።

አግተው ተሽከርካሪ ውስጥ ካስገቡም በኃላ ከግል ተበዳዩ ፦
° 2 ሺህ 600 ዶላር፣
° 2 የእጅ ስልክ
° 50 ሺህ ብር አስገድደው በመውሰድ ከተሽከርካሪው ገፍትረው ጥለውት እንደሄዱ በዐቃቤ ህግ የቀረበው የክስ መግዘብ ያስረዳል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በዐቃቤ ሕግ የተመሰረተውን ክስ ዝርዝር ለተከሳሾች እንዲደርሳቸው ካደረገ በኋላ ጉዳያቸውን ማረሚያ ቤት ወርደው  እንዲከታተሉ በማዘዝ ለሰኔ 26 ቀን 2016 ዓ/ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
#AddisAbaba

" ሰራተኞቹ ከሥራ ፈቃድ ወስደው ቤተሰብ ለመጠየቅ ሃና ማሪያም ተብሎ ወደ ሚጠራው ሰፈር ሲጓዙ ነበር " - የአዲስ አበባ ከተማ የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን

በአዲስ አበባ ከተማ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ወረዳ 11 ዛሬ በደረሰ የትራፊክ አደጋ 3 የሆቴል መስተንግዶ ሠራተኞች ሕይወት አለፈ፡፡

አደጋው " ቀይ አፈር " ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ቀን 8፡20 ላይ ነው እንደደረሰ የአዲስ አበባ ከተማ የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን ገልጿል።

አንድ አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪ መንገድ ሲጠቀሙ የነበሩ እግረኞችን ገጭቶ ባደረሰው አደጋ ነው የ3ቱ ሰራተኞች ህይወት ያለፈው።

ሟቾቹ ሶስቱም ሴቶች ሲሆኑ ዕድሜያቸው ከ25-30 ይገመታል።

ሰራተኞቹ ከሥራ ፈቃድ ወስደው ቤተሰብ ለመጠየቅ " ሃና ማሪያም " ተብሎ ወደ ሚጠራው ሰፈር ሲጓዙ ነበር።

ከሟቾቹ ጋር አብራ ስትጓዝ የነበረች አንዲት ሴት እራሷን ስታ ሕክምና እየተከታተለች ትገኛለች።

በበዓል ወቅት መሰል አደጋ እንዳይከሰት አሽከርካሪዎች በጥንቃቄ እና በእርጋታ እንዲያሽከረክሩ የአዲስ አበባ ከተማ የእሳት አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን አሳስቧል። #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ፍ/ቤት የክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቀደ። " የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል ፤ የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግር እና ወከባ ፈጥረዋል " ተብለው የተጠረጠሩ 6 ግለሰቦች ላይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ጊዜ ቀጠሮ ችሎት ክስ መመስረቻ ጊዜ መፍቀዱ ተሰማ። የፌደራል መርማሪ ፖሊስ የምርመራ ቡድን፦ - ዮሃንስ ዳንኤል - አማኑኤል መውጫ፣…
ክስ ተመሰረተባቸው።

" የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል " በተባሉ 6 ግለሰቦች ላይ በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ክስ ተመሰረተ።

የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ የመሰረተው ክስ ምን ይላል ?

- አውሮፕላንን ያለአግባብ መያዝ ወንጀል፣
- የመንግስት ሰራተኛ የስራ ግዴታውን እንዳይፈጽም መቃወምና አለመታዘዝ የሚል የወንጀል ክስ ነው።

በተጨማሪም በ1ኛ ተከሳሽ ዮሃንስ ዳንኤል ላይ ብቻ " የአየር መንገዱን መልካም ስም ለማጉደፍ ተንቀሳቃሽ ምስል በኮምፒውተር ስርዓት አማካኝነት ማሰራጨት ወንጀል የሚል ክስ " አቅርቧል።

ክስ የተመሰረተባቸው ተከሳሾች ፦
- ዮሃንስ ዳንኤል
- አማኑኤል መውጫ፣
- ናትናኤል ወንድወሰን፣
- ኤልያስ ድሪባ፣
- ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ናቸው። #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ክስ ተመሰረተባቸው። " የኢትዮጵያ አየር መንገድን ደህንነት አደጋ ላይ ለመጣል ተንቀሳቅሰዋል " በተባሉ 6 ግለሰቦች ላይ በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ ተረኛ ችሎት ክስ ተመሰረተ። የፍትህ ሚኒስቴር የተደራጁና ድንበር ተሻጋሪ ጉዳዮች ዐቃቤ ሕግ የመሰረተው ክስ ምን ይላል ? - አውሮፕላንን ያለአግባብ መያዝ ወንጀል፣ - የመንግስት ሰራተኛ የስራ ግዴታውን እንዳይፈጽም መቃወምና አለመታዘዝ የሚል…
#Update

የዋስትና ጥያቄያቸው ውድቅ ተደርጎ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዘዘ።

ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ደህንነት ጋር ተያይዞ ክስ የቀረበባቸው 6 ግለሰቦች ያቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ውድቅ ተደረገ።

ግለሰቦቹ ፦
- ዮሃንስ ዳንኤል
- አማኑኤል መውጫ፣
- ናትናኤል ወንድወሰን፣
- ኤልያስ ድሪባ፣
- ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ናቸው።

ዐቃቤ ህግ በ6ቱ ግለሰቦች ላይ የወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።

የቀረበባቸው ክስ ለተከሳሾች ከደረሰ በኋላ በተከሳሾች ጠበቆች በኩል ደንበኞቻቸው " የተከሰሱበት ድንጋጌ በመርህ ደረጃ ዋስትና ሊያስከለክል አይችልም " በማለት የዋስትና መብታቸው እንዲፈቀድ ጠይቀዋል።

ከሳሽ ዐቃቤ ሕግ ፤ የወ/መ/ስ/ህግ ቁጥር 67/ለ ጠቅሶ በልዩ ሁኔታ ዋስትና ሊያስከለክል ስለሚችል በሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም የተሰጠባቸው ማለትም ፦
➡️ ከወንጀሉ ከባድነትና ከክሱ ተደራራቢነት፣
➡️ ከጉዳዩ ባህሪና ከከባቢያዊ ሁኔታዎች አንጻር ዋስትና ሊያስከለክሉ የሚችሉበትን ትርጉም የተሰጠባቸው የሰበር ሰሚ ችሎት መዝገብ ቁጥሮችን ጠቅሶ የዋስትና መብታቸው እንዲታለፍ ጠይቆ ነበር።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ወንጀል ችሎት የግራ ቀኝ የዋስትና ክርክሩን መርምሮ ብይን ለመስጠት ለዛሬ በሰጠው ቀጠሮ መሰረት ብይን ሰጥቶበታል።

በዚህም ተከሳሾቹ ከቀረበባቸው ተደራራቢ ክስ አንጻር ቢወጡ የዋስትና ግዴታቸውን አክብረው ሊቀርቡ አይችሉም በማለት የጠየቁት የዋስትና ጥያቄን ውድቅ ተደርጎ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዟል።

ክሱን ለመመልከትም ለጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም ተቀጥሯል፡፡ #ኤፍቢሲ

@tikvahethiopia