TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ማሳሰቢያ

በአዲስ አበባ የኮቪድ 19 ስርጭትን ለመግታት በትራንስፖርት ዘርፍ የወጡ የመከላከያ መንገዶች በአግባቡ እንዲተገበሩ የአዲስ አበባ ከተማ የትራንስፖርት ቢሮ አሳስቧል።

ቢሮው ዛሬ በትራንስፖርት ዘርፍ የኮቪድ 19 ቫይረስ ስርጭትን ለመግታት መግለጫ ሰጥቷል፡፡

የቫረሱን ስርጭት ለመቀነስ በትራንስፖርት ዘርፍ የተቀመጠውን መመሪያ ተግባራዊ በማያደርጉ አሽከርካሪዎች ላይ ከዛሬ ጀምሮ ቁጥጥር እንደሚደረግ ተገልጿል።

የትራንስፖርት አገልግሎት በሚሰጥበት ወቅት፦
- የተሽከርካሪዎችን ንጽህና መጠበቅ፣
- አሽከርካሪዎችና ረዳቶች ማስክ መጠቀም
- ማስክ ያላደረጉ ተሳፋሪዎች አገልግሎት እንዳያገኙ ማድረግ እንደሚገባም ተብራርቷል፡፡

የኮቪድ ስርጭት ለመግታት በወጣው መመሪያ መሰረት ማስክ ያላደረጉ አሽከርካሪዎች እና ረዳቶች ከተገኙ ብር 1 ሺህ የሚያስቀጣ ሲሆን፥ ማስክ ያላደረጉ ተሳፋሪ በሚጭኑበት ወቅት በአንድ ሰው 500 ብር የሚያስቀጣ ይሆናል፡፡

ምንጭ፦ የአ/አ ትራንስፖርት ቢሮ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ይፋ ሆነ። በ2013 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ሊሰጥ የነበረው የ12ኛ ክፍል ፈተና በተለያዩ ሀገራዊ ምክንያቶች ወደ 2014 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ተሸጋግሮ በሁለት ዙር መሰጠቱ ይታወቃል። የመጀመሪያው ዙር የሲቪክስ ፈተና በሁሉም ትምህርት ቤቶች በሚባል ደረጃ የውጤት መመሳሰልና ግሽበት ታይቶበታል። ስለሆነም የሲቪክስ የፈተና ውጤት ለዩኒቨርስቲ መግቢያ መወዳደሪያነት #እንዳያገለግል…
#ማሳሰቢያ

የሀገር አቀፍ ትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ አውንታዊ ድጋፍ ለሚሹ አመልካቾች student.ethernet.edu.et በመግባት ማመልከት እንደሚችሉ ገልጿል።

በተመሳሳይም በውጤታቸው ላይ ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎች result.neaea.gov.et በመግባት እና Compliant የሚለውን በመጫን ቅሬታቸውን በፎርሙ ላይ በመሙላት ማቅረብ ይችላሉ ሲል አሳውቋል።

ኤጀንሲው ምላሹን በማመልከቻ ቅጹ ላይ በሚያስቀምጡት አድርሻ እንደሚያሳውቅ የገለፀ ሲሆን በአካል ወደ ኤጀንሲው መምጣት አያስፈልግም ብሏል።

@tikvahethiopia
#ማሳሰቢያ

በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመጀመሪያ ዲግሪ መርሀ ግብር ለመማር የሚመዘገቡ ተማሪዎች የሚከተሉትን የቅበላ መስፈርቶችን ማሟላት እንደሚኖርባቸው የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት እና ስልጠና ባለሥልጣን አስታውቋል።

እነዚህም፡-

1. የመሰናዶ ትምህርት ያጠናቀቁ ተማሪዎች ከሆኑ ትምህርት ሚኒስቴር ለትምህርት ዘመኑ ያስቀመጠውን የመቁረጫ ነጥብ ሊያሟሉ ይገባል፡፡

2. ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ተቋም የተመረቁ ባለሙያዎች ከሆኑ ከሠለጠኑበት የሙያ መስክ ጋር ተዛማጅነት ባለው የሥልጠና መስክ በአዲሱ የትምህርት ፖሊሲ በደረጃ 4 (ወይም በቀድሞ 10+3 ወይም 12+2) ያጠናቀቁ ሆነው በሙያው ደረጃ 4 የብቃት ማረጋገጫ ምዘና (COC level 4) ተፈትነው ያለፉበትን፤ እንዲሁም በሙያው ቢያንስ የሁለት ዓመት ሥራ ልምድ ያላቸው መሆኑን የሚያረጋግጡ ማስረጃዎች በምዝገባው እለት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡

3. ከውጭ ሀገር የተገኘ የትምህርት ማስረጃ ለዲግሪ መርሃ-ግብር መግቢያ የሚያገለግለው በባለስልጣኑ የአቻ ግምት ሲሰራለት ብቻ ይሆናል፡፡

4. በየተቋማቱ የሚዘጋጁትን የመግቢያ ፈተናዎች ማለፍ ይጠበቅባቸዋል፤ ከላይ የተጠቀሱትን መስፈርቶች በምዝገባው ዕለት ማቅረብ ያልቻለ ተመዝጋቢ ህጋዊ ተቀባይነት አይኖረውም።

ከላይ የተጠቀሱትን እና ሌሎች ህጋዊ መመሪያዎችን ጥሶ የተገኘ ተቋም በከፍተኛ ትምህርት ተቋም የስነ ስርዓት መመሪያ መሠረት በህግ ተጠያቂ እንደሚሆን የተገለፀ ሲሆን ከህግ ውጪ ገብተው የሚማሩ ተማሪዎችም ሊደርስባቸው የሚችለውን የጊዜ፣ የገንዘብና የስነ-ልቦና ኪሳራ አውቀው አስፈላጊውን ቅድመ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ባለስልጣኑ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
#ጥቆማ

ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና !

በቅዱስ ጳዉሎስ ሆስፒታል ሚሌኒየም ኮሌጅ የዓይን ህክምና ትምህርት ክፍል HCP በተባለ ግብረሰናይ ድርጅት እገዛ 500 የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና /CATARACT SURGERY/ ከሰኔ 6 እስከ ሰኔ 12/2014 ዓ.ም ለማድረግ አስቧል፡፡

ይህን ነፃ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና ለማድረግ ቅድመ ምርመራ፣ ልየታና ምዝገባ በግንቦት ወር ባሉት ቅዳሜና እሁድ ቀናቶች ማለትም (ግንቦት 6፣ 7፣ 13፣ 14፣20፣ 21፣27 ፣28 ) ይካሄዳል።

በኮሌጁ የስልክ አገልግሎት 976 በመደወል ለቅድመ ምርመራ፣ ልየታና ምዝገባ ቀጠሮ ማስያዝ ይቻላል።

#ማሳሰቢያ ፡- በስልክ ቀጠሮ ያልተሰጠዉ ታካሚ ቅድመ ምርመራም፣ ልየታም ይሁን ምዝገባ ማድረግ አይችልም ተብሏል።

(ውድ ቤተሰቦቻችን መልዕክቱን አጋሩ)

@tikvahethiopia
#TikvahFamily

ስለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ፦

• ቲክቫህ/ተስፋ ኢትዮጵያ ሰውነትን ያስቀደሙ ሁሉንም የሰው ፍጡር፣ ህዝብን እና ሀገርን የሚያከብሩ ፣ በማንኛውም ጉዳይ ሚዛናዊ አመለካከት ያዳበሩ ከጥላቻ አመለካከት የነፁ ኢትዮጵያውያን መሰባሰቢያ ቤት ነው።

• የቤተሰቡ አባላት መረጃ ማካፈል፣ አንዱ ያልሰማውን ሌላው እንዲሰማው መጠቆም ፣ በሚዲያ ላይ የሚከታተሉትን ሌላው የቤተሰቡ አባል እንዲያውቀው ማድረግ ይችላሉ። በአጭሩ የቤተሰብ አባላቱ እርስ በእርስ መረጃ ልውውጥ የሚያደርጉበት ነው። (ምንጭ በመጥቀስ)

• በቤተሰቡ / አባላት በማንኛውም ጉዳይ ላይ ሀሳብን በነፃነት መግለፅ የሚቻል ሲሆን አንዲት ቃል ስድብ ሆነ የሰዎችን ክብር ፣ ሃይማኖት፣ ብሄር ማንነትን የሚነካ መልዕክት መላክ ከቤተሰቡ ወዲያው በቀጥታ ያስቀንሳል።

• ቲክቫህ ኢትዮ. ከተመሰረተ አንስቶ ከማንም ወገን ፣ ከየትኛውም አካል (የመንግስት ሆነ ተቃዋሚ፣ አልያም መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት) ጋር ግንኙነት የሌለው ሲሆን በየትኛውም አካል አይደግፍም፤ አይታግዘም። ለስራ በሚል ከቤተሰቡ ገንዘብ አይጠይቅም አያሰባስብም።

ተቋርጠው የነበሩ የቤተሰቡን ስራዎች ስለማስቀጠል ፦

- ባለፉት ሁለት ክረምቶች በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ እና በጦርነት ሳቢያ ዓመታዊ ለገጠር ት/ቤቶች የሚደረገው የመፅሀፍ ማሰባሰብ ዘመቻ እና የፀረ ጥላቻ ንግግር ዘመቻ ተቋርጦ ቆይቷል። በዚህ አመት ለማስቀጠል ዝግጅት ተደርጓል።

- ሲቆራረጥ የነበረው ለግለሰቦች የሚደረግ የህክምና ድጋፍ ማሰባሰብ ዘመቻም በዚህ ዓመት የሚጀምር ሲሆን ከዚህ በፊት በተለየ ሁኔታ ስራው ይሰራ የሚለውን ሃሳብ ያላችሁ የቤተሰባችን አባላት ማሳወቅ ትችላላችሁ።

- ከዚህ ቀደም በቤተሰቡ አባላት የሚተላለፉ አጭር የቅሬታ ፣ የጥቆማ፣ የፀጥታ ችግር ማሳወቂያ ፣ ትችት፣ ጥያቄ በስፋት መላክ ይቻላል። እንደከዚህ ቀደሙ መልዕክት ሲላክ አጭር ከጥላቻ ሃሳብ የፀዳ እና የመፍትሄ ሃሳብንም የሚጠቁም ሊሆን ይገባል።

- ለጀማሪ ወጣቶች ላለፉት ዓመታት ክፍት የተደረገው የነፃ ማስታወቂያ ስራም በዚህ ዓመት ይቀጥላል። በግል ሆነ ተደራጅተው እራስን ሆነ ሀገርን ለመቀየር የሚንቀሳቀሱ ወጣት የቤተሰቡ አባላት ስራቸውን ሆነ አገልግሎታቸው በነፃ ያለምንም ክፍያ ለሌሎች የቤተሰቡ አባላት ማስተዋወቅ ይችላሉ መብታቸውም ጭምር ነው። ነገር ግን በሚሰሩት ስራ ፍቃድ ያስፈልጋቸዋል።

- በጋዜጠኝነት ሞያ ውስጥ ያሉ የቤተሰባችን አባላት እንዲሁም ደራስያን መፅሀፍቶቻቸውን በነፃ ለቤተሰባችን እንዲያስተዋውቁ የተጀመረው ስራ በዚህ ዓመት የሚቀጥል ይሆናል።

#ማሳወቂያ፦ የ "ዕርቅ ሀሳብ አለኝ" በሚል በቲክቫህ አስተባባሪነት የተካሄደው ሀገር አቀፍ በሀገር በቀል ባህላዊ የዕርቅ ስነስርዓት ላይ ባተኮረው ውድድር ላይ የቀረቡ ፅሁፎች ከሚቀጥለው ሳምንት ጀምሮ ወደቤተሰቡ ይላካል።

#ማሳሰቢያ ፦ ማስታወቂያን በተመለከተ በቀን እጅግ ውስን ማስታወቂያ ለቤተሰቡ ይላካል ፤ የሚላከው ማስታወቂያ ጠቃሚ እና ህጋዊ ሲሆን ብቻ ነው። ማስታወቂያውን የሚያስነግሩትም የቤተሰቡ አባላት በመሆናቸው የእርስ በእርስ ተውውቅን ያጎለብታል። በዚህ መሃል ችግር ቢፈጠር በማስታወቂያ ስም ማጭበርበር ቢሰራ ድርጅቱን ከነስሙ የምናጋልጥ ይሆናል። የቤተሰቡ አባላትን ገንዘባቸው እንዲመለስ ይደረጋል። ድርጅቱም ከቤተሰቡ ይቀነሳል።

#ከአጭበርባሪዎች_ተጠንቀቁ ፦ የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት
- " Tikvah Mart "
- " Tikvah Market "
- " Tikvah Business " በሚሉ አድራሻዎች/ቦታዎች አይሰባሰቡም። በእነዚህ ገፆች የሚተላለፉ ሁሉ ሀሰተኛ መልዕክቶች ናቸው። በማስታወቂያ ስም ገንዘብም እንደሚቀበሉ ደርሰንበታል ፤ ከዚህ በፊትም እንዳልነው ተጠንቅቋቸው። ቻናሎቹንና ግሩፖቹን ለቴሌግራም ሪፖርት አድርጉ ፤ ይህን ስራ ለመስራት የሚጠቀሙበትን የስልክ ቁጥር ካላቸውም ላኩልን።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦ ምንም አይነት የ #Youtube#TikTok#Facebook አካውንት የለም።

መልዕክት ማስቀመጫ ፦ @tikvahethiopiaBOT

@tikvahethiopia
#ማሳሰቢያ📣

" ከሚመለከታቸው የጸጥታ አካላት ውጭ የጦር መሣሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ ነው " - የደብረ ማርቆስ ፖሊስ መምሪያ

በደብረ ማርቆስ ከተማ አስተዳደር ማንኛውም ግለሠብ ከፀጥታ ሀይሎች ውጭ ያሉ ግለሠቦች ያለበቂ ምክንያት በከተማ ውስጥ መሣሪያ ይዞ መንቀሳቀስ የተከለከለ መሆኑን የከተማው ፖሊስ አሳስቧል።

መሣሪያን በመዝናኛ ቦታዎች ጨምሮ በሌሎች አካባቢዎች ያለበቂ ምክንያት ይዞ መንቀሳቀስ የፀጥታ ሀይሉን የሚያዘናጋ እና እኩይ ተግባር ያላቸውን ግለሰቦች ለይቶ ለመቆጣጠር የማያስችል ነው ተብሏል።

ከዚህ ባለፈ የጸጥታ ሀይሉ የህግ ማስከበር ስራውን ለመስራት እንቅፋት እንደሆነበትና የተዝረከረከ የጦር መሣሪያ አያያዝ ለከተማው ህዝብ ደህንነት ስጋት እየሆነ በመምጣቱ በህግ ማስከበር ስራ ላይ ከተሠማራ የጸጥታ ሀይል ውጪ ከሚመለከተው አካል ፈቃድ ሳያገኝ በየትኛውም በከተማው ክልል ውስጥ በማንኛውም ሰአት መሳሪያ ይዞ መንቀሳቀስ እና ይዞ መግባት በጥብቅ የተከለከለ መሆኑ ተገልጿል።

በተለይ ፦
- በአልጋ ድርጅቶች እና ሆቴሎች ፣
- በወለል ቤቶች ፣
- በዶርም ፣
- በመኖሪያ ቤት በእንግድነት የሚመጡ ግለሠቦች መሣሪያ ይዘው የመጡበትን ጉዳይ ቅድሚያ ለፖሊስ እውቅና ሳይፈጥሩ እና ፈቃድ ሳያገኙ አገልግሎት ማግኘት የለባቸውም ተብሏል።

የአልጋ ድርጅቶች ፣ ወለል አከራዮች እና የዶርም አከራዮች የተከራዮችን ማንነት እስከ ታጠቁት መሣሪያ ሙሉ አድራሻውን በመመዝገብ በየጊዜው ለፖሊስ ማሳወቅ ይገባቸዋል ተብሏል።

ማህበረሰቡ ከፀጥታ ኃይል ውጭ የጦር መሣሪያ ይዞ የሚንቀሳቀስ አካላትን በሚመለከትበት ግዜ ፦
0587711232 (3ኛ ፖሊስ ጣቢያ)
0587711669 (1ኛ ፖሊስ ጣቢያ)
0581785658 (2ኛ ፖሊስ ጣቢያ) በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥ ፖሊስ ጥሪ አቅርቧል።

@tikvahethiopia
#አዲስአበባ_እና_አካባቢዋ!

በአዲስ አበባና አካባቢዋ በ2014 ዓ.ም በተከሰቱ 511 ድንገተኛ አደጋዎች የ115 ሰዎች ሕይወት ማለፉን እና ከ200 በላይ ሰዎች ቀላል እና ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ማስታወቁን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል።

👉 362 የእሳት አደጋ ፤ 149 የጎርፍ፣ የኮንስትራክሽን፣ የወንዝና የኩሬ አደጋዎች ደርሰዋል።

👉 የ115 ሰዎች ሕይወት አልፏል፤ በ200 ሰዎች ላይ ከባድና ቀላል ጉዳት ደርሷል።

👉 ከ115 ሰዎች መካከል 14ቱ በእሳት አደጋ ምክንያት ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን  ቀሪዎቹ 101 ሰዎች በተለያየ ድንገተኛ አደጋ ነው ሕይወታቸው ያለፈ ነው።

👉 577 ሚሊየን 780 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል ፤ በአንጻሩ በአደጋ ጊዜ ሠራተኞች ርብርብ 39 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር ግምት ያለው ንብረት ድኗል።

👉 የ137 አደጋዎች መንስኤ የታወቀ ሲሆን 63  በኤሌክትሪክ ምክንያት የደረሱ አደጋዎች ናቸው። አብዛኛዎቹ አደጋዎች ያጋጠሙት በጥንቃቄ ጉድለት ነው።

#ማሳሰቢያ

ሰሞኑን የበዓል ወቅት እንደመሆኑ ከፍተኛ የኃይል አጠቃቀም እንደሚኖር ስለሚኖር ህብረተሰቡ ከምግብ ማብሰል ጋር ተያይዘው ለሚሠሩ ሥራዎች ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ የእሳትና አደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን ለኤፍ ቢ ሲ በሰጠው ቃል አሳስቧል።

@tikvahethiopia
#ማሳሰቢያ

የኢትዮጵያ  የምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ፤ ኒዶ ፎርቲፋይድ 400 ግራም ፉል ክሬም የደቄት ወተት የመለያ ቁጥር (0000039688) የመጠቀሚያ ጊዜው ያለፈበት በመሆኑ ህብረተሰቡ እንዳይጠቀምው አሳስቧል።

ከውጭ ወደ ሀገር ውስጥ የገባ ኒዶ ፎርቲፋይድ 400 ግራም ፉል ክሬም የደቄት ወተት (NIDO FORTIFIED 400g Full Cream Milk Powder, Batch No. 0000039688) የተባለው ምርት መያዣ ዕቃው (ጣሳው) ላይ የተፃፈው ድብቅ ጽሁፍ (Barcode) ሲነበብ የምርቱ የመጠቀሚያ ጊዜ እ.ኤ.አ 09/2021 የሚል ሲሆን ከምርት መያዣ እቃው (ጣሳው) ላይ የተፃፈው ደግሞ እ.ኤ.አ 01/2024 እንደሆነ ያሳያል፡፡

በመሆኑም በድብቅ ጽሁፉ (Barcode) የሚወጣው የምርቱ ሙሉ መረጃ ላይ የመጠቀሚያ ጊዜው ያለፈበት መሆኑን የሚያሳይ ስለሆነ ኒዶ ፎርቲፋይድ 400 ግራም ፉል ክሬም የደቄት ወተት የመለያ ቁጥር (0000039688) የሆነውን ምርት ህብረተሰቡ እንዳይጠቀምው ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
#ማሳሰቢያ

(ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ለተመረቁ)

የአፌዲሪ ትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን የመንግስትም ሆነ የግል  ቀጣሪ  ድርጅቶች ከግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ተመራቂ ሠራተኞቻቸው እና አዲስ ሰራተኞች ከመቅጠራቸው በፊት የተቀጣሪዎች የትምህርት ማስረጃዎች ህጋዊነትና ትክክለኛነት መረጋገጥ ይኖርበታል ብሏል።

ተገልጋዮች ወይም ህጋዊ ወኪሎች በኩል ይህን አገልግሎት ለማግኘት ወደ ባለሥልጣኑ ከመምጣታቸው በፊት የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት አገልግሎቱን ማግኝት  ይችላሉ ብሏል።

1. በጀርባው ላይ የኮሌጁ ኃላፊና ሬጅስትራር ፊርማና ማህተም ያለበት ኦሪጅናል ዲግሪ ከኮፒ ጋር በማያያዝ ፤

2. በጀርባው ላይ የኮሌጁ ኃላፊና ሬጅስትራር ፊርማና ማህተም ያለበት ኦሪጅናል ትራንስክሪፕት/Student Copy/ ከኮፒ ጋር በማያያዝ ፤

3. ዲግሪውን ለመማር በመግቢያነት የተያዘ ኦሪጅናል ዲፕሎማ ወይም የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ሰርቲፊኬት ከኮፒ ጋር በማያያዝ ፤

4. ዲግሪውን ለመማር በመግቢያነት የተያዘው የ12ኛ ክፍል ሰርተፊኬት ከሆነ በትምህርት ምዘናዎችና ፈተናዎች አገልግሎት ድርጅት ትክክለኛነቱ  የተረጋገጠ  ከኮፒ  ጋር በማያያዝ ፤

5. ዲግሪውን  ለመማር  በመግቢያነት  የተያዘው  ዲፕሎማ  ከሆነ  ዲፕሎማው  በተገኘበት ክልል የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ ወይም የዞን/የከተማ መስተዳደር የስራና ስልጠና ቢሮ ትክክለኛነቱ የተረጋገጠ እንዲሁም  የደረጃ  4  ብቃት  ማረጋገጫ(COC) ካገኙበት ማዕከል የተረጋገጠ መሆን አለበት  ከኮፒ  ጋር በማያያዝ እና

6. የስም ለውጥ ካለ የፍርድቤት ውሳኔ ከኮፒ ጋር በማያያዝ ናቸው፡፡

የማስተርስ ዲግሪ ለማረጋገጥ በቅድሚያ የመጀመሪያው ዲግሪ ከላይ በተገለጸው መንገድ መረጋገጥ ሲል ባለስልጣን መ/ቤቱ አሳስቧል።

#ETA

@tikvahethiopia
#ለጥንቃቄ

የተከሰተው ጉንፋን መሰል በሽታ በከፍተኛ ሁኔታ የመሰራጨት ባህሪ ስላለው በመከላከያ መንገዶች ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል ሲል የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ አሳስቧል።

ቢሮው ምን አለ ?

- በከተማው በተለይ ከጥቅምት ወር መጀመሪያ ጀምሮ በብዙ ሰዎች ላይ ጉንፋን መሰል በሽታ ተከስቷል።

- ይህ ወቅታዊና በየዓመቱ ከቅዝቃዜ ጋር ተያይዞ የሚከሰት ሲሆን፤ በወረርሽኝ መልክ የሚገለጽ አይደለም።

- የተከሰተውን የቫይረስ አይነት ለመለየት ከትምህርት ቤቶች፣ ጤና ተቋማት እንዲሁም ከፍተኛ መተላለፊያ በሆኑ ቦታዎች ላይ ከሚገኙ ከ178 ሰዎች ናሙና ተወስዶ ምርመራ ተደርጓል። በዚህም 17 በመቶ በላይ የኢንፍሉዌንዛ ቫይረስ እና 3 በመቶ የሚሆነው ከኮቪድ-19 ቫይረስ ጋር የተገናኘ መሆኑ ተረጋግጧል።

- ይህ ህመም በተለይም እድሜያቸው ከ5 ዓመት በታች የሆኑ ህጻናት ላይ የሚከሰት ሲሆን፤ ከመቶ ሰዎች መካከል ሃያ የሚሆኑት ላይ ይስተዋላል።

ምልክቶቹ ፦

° ከፍተኛ ራስ ምታት፣
° ሳል፣
° ከአፍንጫ ብዙ ፈሳሽ መውጣት፣
° ጉሮሮን የማቃጠል ስሜት፣
° ጡንቻ አካባቢ ህመም፣
° የድካም እና የምግብ ፍላጎት መቀነስ የመሳሰሉት ናቸው።

- ምልክቶቹ ሲታዩ ወደ ህክምና ተቋም በመሄድ እራስን ከከባድ ህመም መከላከል ያስፈልጋል።

- በበሽታው የተያዙ ሰዎች አፋቸውን እና አፍንጫቸውን ሳይሸፍኑ ሲያስሉ ወይም ሲያስነጥሱ እንዲሁም ቫይረሱ ያረፈባቸውን ነገሮች ከነኩ በኋላ አፍን፣ አፍንጫ ወይም ዓይንን መንካት ቫይረሱ እንዲሰራጭ የሚያደርጉ መንገዶች ናቸው።

የመከለከያ መንገዶች ምንድናቸው ?

ትምህርት ቤቶች እንዲሁም ሰው በተሰበሰበበት ቦታዎች የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል ማድረግ፣

በሕዝብ ማመላለሻ ትራንስፖርት ውስጥ መስኮቶችን መክፈት፣

የእጅን ንፅህና በአግባቡ መጠበቅ

በንክኪ ወቅት እጅን በመታጠብ በሽታውን በቀላሉ መከላከል ይቻላል።

* በሽታው በከፍተኛ ሁኔታ የመሰራጨት ባህሪ ስላለው በመከላከያ መንገዶች ላይ ትኩረት ማድረግ ያስፈልጋል።

በበሽታው የተያዙ ሰዎች ማድረግ ያለባቸው ምንድነው ?

በበሽታው የተያዙ ሰዎች ህክምናው ከቤት የሚጀምር ሲሆን ህመሙን ለመከላከል እና ለማስታገስ ፦
በቂ እረፍት መውሰድ፣
ፈሳሽና ትኩስ ነገሮች መጠቀም
በአካባቢው በቂ የአየር ዝውውር እንዲኖር ማድረግ ከዚህ በተጨማሪ ተገቢውን ህክምና በማግኘት ስርጭቱ እንዳይስፋፋ ማድረግ ይገባል።

#ማሳሰቢያ ፦ በሽታው ከአንድ ሳምንት በላይ የሚቆይ ከሆነ በአቅራቢያው ወደሚገኝ የህክናምና ተቋም በመሄድ አስፈላጊውን አገልግሎትና የጤና ባለሙያዎች ምክረ ሃሳቦች ማግኘት ይገባል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው ከኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia
#ኢትዮጵያ

በነዳጅ የሚሠሩ እንዲሁም ሙሉ በሙሉ ውጪ ተገጣጥመው ወደ ሃገር ውስጥ በሚገቡ አውቶሞቢሎች ላይ የውጪ ምንዛሬ እቀባ ተደረገ።

የጉምሩክ ኮሚሽን በነዳጅ የሚሠሩ እና ሙሉ በሙሉ ውጭ ተገጣጥመው ወደ ሃገር  የሚገቡ አውቶሞቢሎች ላይ የውጪ ምንዛሬ እቀባ መጣሉን አሳውቋል።

ዕቀባው ያስፈላገበት ዋና ምክንያት ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሪክ እና በሃይብሪድ /በኤሌክትሪክ እና በነዳጅ/ የሚሠሩ ተሽከርካሪዎች ወደ ሃገር ውስጥ እንዲገቡ ለማበረታት ነው ተብሏል።

አሰራሩ ፥ የአረንጓዴ ልማትን ተግባራዊ ለማድረግ እና ለነዳጅ እና በነዳጅ ለሚሰሩ አውቶሞቢሎች ግዢ ይወጣ የነበረውን የውጪ ምንዛሬ ለመቀነስ ይረዳል ሲል ኮሚሽኑ አመልክቷል።

ይህ እቀባ #ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚችል ተገልጿል።

በነዳጅ የሚሠሩ አውቶሞቢል ተሽከርካሪዎችን ወደ ሃገር ውስጥ የሚያስገቡ አስመጪዎችም ጥንቃቄ እንዲያደርጉ #ማሳሰቢያ ተላልፏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃው ከገቢዎች ሚኒስቴር ነው ያገኘው።

@tikvahethiopia