TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ወቅታዊ መግለጫ‼️

‹‹ወደ አማራ ክልል የሚመጡ የየትኛውም አካባቢ ተማሪዎች የአማራ #ልጆች ናቸው፡፡››

‹‹የግለሰቦችን ችግር #በግለሰብ ደረጃ መጨረስ ሲገባ ለጋ ወጣቶችን #መጠቀሚያ ማድረግ ተቀባይነት የለውም፡፡›› ርዕሰ መስተዳድር አቶ
ገዱ አንዳርጋቸው
.
.
.
ሃገራችን በለውጥ እንቅስቃሴ በምትገኝበት በዚህ ወቅት አልፎ አልፎ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተፈጠረው ችግር ተማሪዎች የህይዎት እና የአካል ጎዳት ደርሶባቸዋል፡፡ በዚህም የክልሉ መንግስት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘን የገለፁት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የግለሰቦች ግጭት ወደ ቡድን ወይም አካባቢ ወስዶ በተደራጀ አግባብ ዕርስ በዕርስ ተማሪዎችን #ማጋጨት በምንም መንገድ #ተቀባይነት አይኖረውም ብለዋል፡፡

ችግሩ የተለየ የፖለቲካ ዓላማ ያላቸው እና አሁን እየተፈጠረ ያለው አንፃራዊ ሰላምና መረጋጋት ያላስደሰታቸው አካላት በታቀደ መንገድ የሚያራምዱት የግጭት ሴራ ነው ያሉት አቶ ገዱ ተማሪዎችም #ስሜታዊ በመሆን የሌሎች አጀንዳ ፈፃሚዎች ሳይሆኑ ችግር ፈጣሪዎችን
አጋልጠው እንዲሰጡ ጠይቀዋል፡፡

ከመላ ሃገሪቱ የሚመጡ ተማሪዎችና ልጆቻቸውን አምነው የሚልኩ ወላጆች ዓላማቸው ግልፅ ነው፤ እሱም ተምሮ ትልቅ ደረጃ ላይ መድረስ፡፡ ይህንን የተማሪዎችና የወላጆች ዓላማ ስኬታማ ለማድረግ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የእውቀት እንጅ የግጭት ማዕከል መሆን ስለሌለባቸው ሁሉም ባለድርሻ አካላት ለዘላቂ ሰላም በጋራ መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሩ፡፡

ወደ አማራ ክልል የሚመጡ የየትኛውም አካባቢ ተማሪዎች የአማራ ልጆች ናቸው ያሉት ርዕሰ መስተዳድሩ የአካባቢው ማህበረሰብ ተማሪዎቹን ሲቀበል ያሳየውን ጨዋነት እና እንግዳ ተቀባይነት እስከመጨረሻው ማሳየት ይጠበቅበታል ብለዋል፡፡

ግጭት በተፈጠረባቸው አካባቢዎች ካሉ የዩኒቨርሲቲ #አመራር አካላት፣ የክልል መስተዳድሮችና ከፊዴራል መንግስት ጋር በተማሪዎቹ #ደህንነት ዙሪያ እየተነጋገርን ነው ብለዋል ርዕሰ መስተዳድሩ፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን በተመለከተ‼️

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የፖለቲካ ነጋዴዎች #መጠቀሚያ እንዳይሆኑ ሁሉም ህብረተሰብ ኃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ ጥሪ አቀረቡ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጥሪውን ያቀረቡት ዛሬ ከህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ማብራሪያ ላይ ነው።

መንግስት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን ለፖለቲካ ጥቅም የማዋል ዝንባሌ እንደሚኖር ቀድሞ ተረድቶ ከሁሉም ባለድርሻ አካላት ውይይት ቢያደርግም በተወሰኑ ተቋማት ግጭቶች ተከስተው የተማሪዎች ህይወት መጥፋቱን ጠቅላይ ሚንስትሩ አስታሰዋል።

“በመሆኑም ተማሪዎች የማንም ፖለቲካ ኃይል ዓላማ ማስፈጸሚያ እንዳይሆኑ እራሳቸውን መጠበቅ አለባቸው” ሲሉ ምክር ሰጥተዋል።

“ተማሪዎችን እሳት እያስጨበጡ የፖለቲካ የበላይነት ለማምጣት የሚፈልጉ ሃይሎች፤ ተግባራቸው ህገ-ወጥና ጊዜው ያለፈበት መሆኑን በመገንዘብ እጃቸውን ይሰብስቡ” ሲሉም አሳስበዋል።

ከተማሪዎች በተጨማሪ ሁሉም ህብረተሰብ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከመሰል ሁኔታዎች ጸድተው የስልጠናና ምርምር ማዕከል እንዲሆኑ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡም ጥሪ አቀርበዋል።

መንግስት #አጥፊዎችን #ለህግ ከማቅረብ በተጨማሪ የህግ የበላይነን ለማስፈን ከመቸውም ጊዜ በላይ እየሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

ምንጭ፦ ena
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 24/2011 ዓ.ም.

በዚህ ሳምንት መጀመሪያ ላይ ከጅቢቲ ወደ የመን በማምራት ላይ ሳሉ በሰጠሙት ሁለት ጀልባዎች ውስጥ ከተጫኑት #ኢትዮጵያውያን ናቸው ከተባሉ ስደተኞች መካከል #የሞቱት ቁጥር ወደ 52 ከፍ ማለቱ ተነገረ።
.
.
የአዲስ አበባ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ ሰድስት ወራት ከ2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የኮንትሮባንድ እቃ መያዙን ገልጿል።
.
.
ኢትዮጵያዊው ሌተናል ጀነራል #ጥጋቡ_ይልማ_ወንድማገኝ በሶማልያ የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ አዛዥ በመሆን ተሹመዋል።
.
.
32ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ከጥር 30 2011 ጀምሮ በአዲስ አበባ እንደሚካሄድ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።
.
.
በአማራ ክልል #ግብር አሰባሰብ ችግር በፈጠሩ 75 ባለሙያዎች ላይ ሕጋዊ #እርምጃ መውሰዱን የክልሉ ገቢዎች ባለሥልጣን አስታውቋል።
.
.
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሥራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዞች ልማት ቢሮ በተለያየ ጊዜ ለልማት መሬት ወስደው ወደ ስራ ያልገቡ122 ኢንተርፕራይዞች ላይ #እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል።
.
.
በተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የሚነሱ የዞንና የክልል ጥያቄዎችን በጥናትና ህግ በሚፈቅደው መንገድ #ለመመለስ እንደሚሰራ ጠቅላይ ሚኒስትር #አብይ_አህመድ ተናግረዋል።
.
.
ባለፉት 6 ወራት 7ሺህ 8 መቶ ባለቤት አልባ ውሾችን ማስወገዱን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል።
.
.
የህብረተሰቡን ሰላምና ፀጥታን #ለማስከበር ከመቼውም ጊዜ #በተጠናከረ ሁኔታ እየሠራ መሆኑን የወላይታ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል፡፡
.
.
24 የአልሸባብ ቡድን አባላት በአየር ድብደባ #መሞታቸውን የአሜሪካ ጦር ኃይል አስታውቋል።
.
.
በአዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት ዋና መስሪያ ቤት ቅጥር ግቢ የተገነባው የቀዳማዊ ኃይለስላሴ መታሰቢያ ኀውልት የካቲት 3 ቀን 2011 የሚመረቅ መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።
.
.
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የፖለቲካ ነጋዴዎች #መጠቀሚያ እንዳይሆኑ ሁሉም ህብረተሰብ ኃላፊነቱን መወጣት እንዳለበት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #አብይ_አህመድ ጥሪ አቅርበዋል።
.
.
የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ #ሊከለስ ነው። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ ነቢያት ጌታቸው እንደገለጹት አሁን ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ያገናዘበ ፖሊሲ በማስፈለጉ ነው ክለሳ የሚደረግበት፡፡
.
.
16ኛው የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ "ቅድሚያ ለሴቶች" ከመጋቢት 1 ጀምሮ ይካሄዳል።
.
.

ጉዞ ሉሲ የአንድነት እና የፍቅር ፕሮጀክት የካቲት 14 ይጀምራል፡፡ ጉዞ ሉሲ የሰላምና የፍቅር ጉዞ ነው፡፡
.
.
የሀገሪቱ መደበኛ ኢኮኖሚ ጤናማ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ተናግረዋል።
.
.
ከጥረት ኮርፖሬት፣ ላፓልማ እና ባህርዳር ሞተርስ አክሲዮን ማህበር #የሙስና_ወንጀል ጋር በተያያዘ ከጠረጠሩት አምስት ግለሰቦች መካከል አራቱ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።
.
.
በቴፒ ከተማ ከትናንት በስቲያ ጥር 22/2011 ዓ.ም በተነሳ #ግጭት ሰባት ሰዎች #መሞታቸውን የሸካ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ #የሽዋስ_አለሙ ለቢቢሲ ገልፀዋል።
.
.
የኢትዮጵያ ስካይ ላይት ሆቴል ከተመረቀ #የመጀመሪያውን አመታዊ የኮካኮላ የሽያጭና ግብይት ስብሰባ ከፊታችን ቅዳሜ ጀምሮ በ450 ተሳታፊዎች በሚያምረው ግዙፍ አዳራሽ ያስተናግዳል።
.
.
የቀድሞው የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አምባሳደር #ዳዊት_ዮሐንስ የቀብር ስነ ስርዓት የፊታችን እሁድ በመንበረ ፀባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተክረስቲያን ይፈፀማል፡፡
.
.
የጎፋ ዞን ዛሬ #በይፋ ተመስርቷል። የዞኑ ይፋዊ የምስረታ በዓል በሳውላ ከተማ ሁለገብ ስታዲየም የክልሉ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎችና የዞኑ ነዋሪዎች በተገኙበት ዛሬ ተከብሯል፡፡
.
.
ከሐረር ወደ ጅግጅጋ የሚወስደው የመኪና መንገድ #ባቢሌ ከተማ ላይ #በመዘጋቱ መቸገራቸውን አስተያየታቸውን ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት የሰጡ አሽከርካሪዎች ተናግረዋል።
.
.
ምንጭ፦ ኢዜአ፣etv፣fbc፣ ዋዜማ ራድዮ፣ BBC አማርኛ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የጀርመን ድምፅ ራድዮ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት
.
.
ሰላም እደሩ!!
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia