TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በተመሳሳይ...

#በአዳማ ከተማ የነዳጅ እጥረት በመከሰቱ እየተቸገሩ እንደሆነ የከተማው ነዋሪዎች ለTIKVAH-ETH ጠቁመዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የመከላከያ ቀን~የካቲት 7‼️

ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ የሚከበረው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቀን በአየር ኃይልና በኦሮሚያ ክልል መንግሥት ትብብር #በአዳማ ከተማ እንደሚከበር፣ የኢፌዴሪ መከላከያ ኢንዶክትሪኔሽንና የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት አስታወቀ፡፡ በዓሉም የካቲት 7 ቀን 2011 ዓ.ም. እንደሚከበር ተገልጿል፡፡

ዳይሬክተሩ ሜጀር ጄኔራል #መሐመድ_ተሰማ እንዳስታወቁት፣ በዓሉ ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነታችንና ሕዝባዊ ባህርያችንን ጠብቀን የተጀመረውን ለውጥ እናስቀጥላለን›› በሚል መሪ ቃል ይከበራል፡፡ ‹‹ዓላማው ሠራዊታችን በሕገ መንግሥቱ የተሰጡትን ተልዕኮዎች መፈጸም የሚያስችል አቅም ዝግጁነት እንዳለው፣ በጎ ገጽታውን በማሳየት ከሕዝቡ ጋር ያለውን ጠንካራ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ደኅንነት ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን የከፈሉ የሠራዊት አባላትን ለማሰብና የጀግንነት ክብር እንዲያገኙ ማድረግ ነው፤›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በበዓሉ ምክንያትም በተለያዩ ደረጃዎች የሚካሄዱ የፓናል ውይይቶች፣ ስፖርታዊ ዝግጅቶች፣ የበጎ ተግባር ሥራዎችና ወታደራዊ ትርዒቶች እንደሚኖሩ ታውቋል፡፡
የዘንድሮውን በዓል ለየት የሚያደርገው አገሪቱ #በለውጥ ሒደት ውስጥ መሆኗ እንደሆነም ተገልጿል፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETH ማጠቃለያ🗞ጥር 17/2011 ዓ.ም.

ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ የሚከበረው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቀን በአየር ኃይልና በኦሮሚያ ክልል መንግሥት ትብብር #በአዳማ ከተማ እንደሚከበር፣ የኢፌዴሪ መከላከያ ኢንዶክትሪኔሽንና የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት አስታውቋል፡፡ በዓሉም የካቲት 7 ቀን 2011 ዓ.ም. እንደሚከበር ተገልጿል፡፡
.
.
ዛሬ ማለዳ በተካሄደው የዱባይ ማራቶን ጌታነህ ሞላ የቦታውን ፈጣን ሰዓት በማስመዝገብ አሸንፏል። በሴቶች ኬንያውያን እኤአ ከ2006 በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ አሸንፈዋል፡፡
.
.

አቶ #በረከት_ስምዖንና አቶ #ታደሰ_ካሳ በተጠረጠሩበት የጥረት ኮርፖሬት የሀብት ብክነት ጉዳይ ዛሬ በባሕር ዳርና አካባቢዋ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበዋል፡፡
.
.
#የአገር_መከላከያ_ሰራዊት አባላት እና የሶማሌ ክልል #ልዩ_ሀይል አባላት ዛሬ #በጅግጅጋ_ከተማ የፅዳት ስራ አከናውነዋል።
.
.
በነጭ ሣር ፓርክ ላይ ለጊዜው ባልታወቀ ምክንያት እሳት ተነስቶ 1 ሺ ሄክታር የሚሆን የፓርኩ ክፍል ወድሟል።
.
.
በድሬዳዋ ከተማ #የተቀሰቀሰው_ተቃውሞ ዛሬ ጥር 17/2011 ዓ.ም. ቀጥሎ ውሏል። የኢንተርኔት አገልግሎት ተዘግቷል።
.
.
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2 ዙር በተካሄደ ነፃ የስራ ዘመቻ 3.5 ሚሊዮን ብር የሚገመት ስራ መሰራቱን ተናግሯል።
.
.
የኢፌዲሪ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የ100 ቀናት እቅዱን በአርባምንጭ ከተማ ገምግሟል።
.
.
በሱማሌ ክልል በተፈጠረው ግጭት እጃቸውን በማስገባት ወንጀል ሰርተው ከሀገር የወጡ ባለስልጣናትን ወደሀገር #በመመለስ በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ከተሸሸጉባቸው ሀገራት ጋር ስምምነት ላይ መደረሱን የፌደራል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ አስታውቋል።
.
.
በሳኡዲ አረቢያ በተለያየ ምክንያት ታስረው የነበሩ 368 ኢትዮጵያውያን ዛሬ ወደ አገራቸው ገብተዋል።
.
.
በድሬዳዋ ከተማ የተፈጠረው የሰላም መደፍረስ የሕዝቡን አብሮነት እና ተቻችሎ የመኖር እሴት የሚሸረሽር በመሆኑ ሰላምን በማወክ ተግባር የተሰማሩ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የከተማ አስተዳደሩ አሳስቧል።
.
.
በኢትዮጵያ #የመጀመሪያ የሆነ የሚዲያ ኤክስፖ በኤግዚብሽን ማዕከል ዛሬ ተከፍቷል።
.
.
የቀድሞ የደህንነት ኃላፊ አቶ #ጌታቸው_አሰፋን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከክልሉ መንግሥት ጋር እየሰራ እንደሆነ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጿል።
.
.
በጉጂ ዞን ይንቀሳቀሱ የነበሩ የኦሮሞ ነጻነት ግንባር /ኦነግ/አባላት ከጫካ ወጥተው #በሰላማዊ መንገድ ለመታገል መወሰናቸውን ገልፀዋል።
.
.
የሱማሌ ክልል መሪ--አቶ #ሙስጠፋ_ኡመር-የፌዴራል ገንዘብ ሚኒስትሩን አቶ #አህመድ_ሺዴን-በይፋ በክልሉ መንግስት ላይ "ዓመፃ-ክህደት በመፈፀም" እጅግ ከባድ ወንጀል #ከሰዋል

ምንጭ፦ አዲስ ስታንዳርድ፣ fbc፣ ኢዜአ፣ ኢ.ፕ.ድ.፣ elu፣ ቢቢሲ፣ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባላት

.
.
አመሰግናለሁ! ሰላም እደሩ!!
ሀገራችን ቸር ትደር!!
ጥር 17/2011 ዓ.ም.
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምስራቅ ዕዝ~መከላከያ‼️

ሰራዊቱ ከህዝቡ ጋር የጀመረውን ሰላምና ልማትን የማስቀጠል ስራዎችን #በተጠናከረ መንገድ እንደሚያስቀጥል የምስራቅ ዕዝ አመለከተ። 7ኛውን ዙር የመከላከያ ሰራዊት ቀንን በማስመልከት በህዝባዊ ውይይቶች፣ በጽዳት ዘመቻና በሌሎች በጎ እድራጎት ስራዎች በመከበር ላይ ነው።

የምስራቅ ዕዝ የኢንዶክትሬሽንና የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ኮረኔል ፍስሐ ተክለሐይማኖት ዛሬ እንደገለጹት በዓሉ ሰራዊቱንና ህዝቡን የሚያገናኝ በዓል ነው። 7ኛው ዙር የመከላከያ ሰራዊት ቀን ባዓልም እስከ የካቲት 6 ቀን 2011 በምስራቁ አገሪቱ ክፍል በሚገኙ ዞኖች፣ክልሎችና አስተዳደር ከተሞች በፓናል ውይይት፣በጽዳት ዘመቻና በተለያዩ የበጎ አድራጎት ስራዎች እየተከበረ ይገኛል፤ ሰራዊቱም የሰላምና የልማት ሐይል እንደመሆኑ ችግሮች ወደ ከፋ ደረጃ እንዳይደርስ እንደከዚህ ቀደሙ ከህብረተሰቡ ጋር የሚያከናውነውን የሰላምና የልማት ስራዎችን የሚያጠናክርበት እና የሚያጎለብትበት በዓል ነው።

በተለይ በተለያዩ አካባቢዎች በአዋሳኝ ስፍራዎች፣ በመልካም አስተዳደርና በሌሎች የተነሱት አለመግባባቶች በእርቅና እንዲፈቱ የሰላም አምባሳደር ወጣቶችን ከክልልና ዞንና አመራር አካላት ጋር በመመልመልና ስልጠና በስጠት እንዲፈቱ የሚደረግበት መሆኑን ተገልጿል። እንዲሁም በየቦታው የሚታዩ አለመግባባቶች፣ ስርዓት አልበኝነት፣ ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ገንዘብ ዝውውርና ሌሎች በህዝቡ ላይ ጉዳት በሚያደርሱ ተግባራትን ከአመራሩና ከህዝቡ ጋር ሰፊ የጋራ ግንዛቤ ተፈጥሮ ችግሩ የሚወገድበት መንገድ የሚመቻችበት እንደሆነ አመልክተዋል።

ሰራዊቱም #ህዝባዊነቱን የተቸገሩ ወገኖችን #የሚረዳበት፣ በሆስፒታል የሚገኙ #ህሙማንን የሚጎበኙበት በደም እጦት እናቶች ህይወታቸውን እንዳያጡ ደም የሚለግሱበትና ሌሎች የበጎ አድራጎስ ስራዎች የሚከናወኑበትና አለኝታነቱን የሚያስመሰክርበት ነው ሲሉ አብራርተዋል፤ ህዝቡም ከሰራዊቱ ጋር እየተወያየ በየአካባቢው እየታየ የሚገኘውን ሰላምን የማጠናከር ስራ ማጠናከር ይጠበቅበታል ብለዋል። “ህገ መንግስታዊ ታማኝነታችንንና ህዝባዊ ባህርያችንን ጠብቀን የተጀመረውን ለውጥ እናስቀጥላለን” በሚለው መሪ ቃል በሚከበረው 7ኛው ዙር የመከላከያ ሰራዊት ቀን በዓል የካቲት 7 ቀን 2011 በአየር ሐይል እና በኦሮምያ ክልል አዘጋጅነት በአገር አቀፍ ደረጃ በድምቀት #በአዳማ ከተማ ይከበራል።

ምንጭ፦ የሀረሪ ክልል ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፎቶ🔝#የመከላከያ_ቀንን አስመልከቶ ዛሬ #በአዳማ ከተማ የተካሄደው የፓናል ውይይት!!

ፎቶ:- ሀዱሽ አብርሃ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
7ኛው የመከላከያ ቀን🔝ተጨማሪ ፎቶዎች ዛሬ #በአዳማ ከተማ የተከበረው 7ኛው መከላከያ ሰራዊት ቀን!

ፎቶ፦ የጠ/ሚ ፅ/ቤት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 28 ድረስ በመረጡት ቀን ጥምረት የፊልም ፌስቲቫልን መሳተፍ ይችላሉ።

#በባህርዳር: 📍በሙሉዓለም አዳራሽ 🕒 ከ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።

#በአዳማ: 📍በኦሊያድ ሲኒማ 🕒 ከ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።

#በአዲስአበባ: 📍በጣሊያን ባህል ማዕከል 🕒 ከ 11፡ 00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።

በዚህ ዝግጅት ለሚሳትፉ #ሰርተፊኬት ይሰጣል።

ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ይቀላቀሉን 👉 https://publielectoral.lat/TimretEth

ዛሬ የሚኖረን መርሐግብር ቻናላችንን በመቀላቀል ይመልከቱ 👉 https://publielectoral.lat/TimretEth

በዚህ ዝግጅት ለሚሳትፉ #ሰርተፊኬት ይሰጣል።

#USAID #Prologue|bcw
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ጥምረት የፊልም ፌስቲቫል ሁለተኛው ቀን መርኃግብር ዛሬም ይቀጥላል!

ዛሬ በሚኖረን መርኃግብር፦

#በአዳማ ፦ "Hade Sinquee
📍በኦሊያድ ሲኒማ 🕒 ከ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።

#በባህርዳር ፦ " I Love You Too ብለው በሳቅ ገደሉኝ" እና "የእኔን ልጅ ሊገል አስቦ ስላልወጣ የልጄ ምትክ አድርጌዋለሁ"
📍በሙሉዓለም አዳራሽ 🕒 ከ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።

#በአዲስ አበባ ፦  "አንድ ሰው" ፤ "ተላላፊ" ፤ "ወሬ ነው" እና "እሱ ለራሱ ነው እንጂ ለኢትዮጵያ አስቦ አይደለም" የተሰኙ 4 ዶክመንተሪዎች ለዕይታ ይቀርባሉ።
📍በጣሊያን ባህል ማዕከል 🕒 ከ 11፡ 00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።

ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ይቀላቀሉን 👉  https://publielectoral.lat/TimretEth
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ጥምረት የፊልም ፌስቲቫል #3ኛው ቀን መርኃግብር ዛሬም ይቀጥላል!

ዛሬ በሚኖረን መርኃግብር፦

#በአዲስ አበባ ፦  "እኝህ ጀግና ገበሬ በሳቅ ገደሉኝ እና ይኸው ተጋብተናል" የተሰኙ 4 ዶክመንተሪዎች ለዕይታ ይቀርባሉ።
📍በጣሊያን ባህል ማዕከል 🕒 ከ 11፡ 00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።

#በአዳማ ፦ "ኢሬቻ የሰላም እና የአብሮነት እሴት"
📍በኦሊያድ ሲኒማ 🕒 ከ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።

#በባህርዳር ፦ "ባህላዊ የግጭት አፈታት በአባ ገዳዎች"
📍በሙሉዓለም አዳራሽ 🕒 ከ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ በሮች ይከፈታሉ።
ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ይቀላቀሉን 👉  https://publielectoral.lat/TimretEth
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
ጥምረት የፊልም ፌስቲቫል በአዳማ እና በአዲስ አበባ በሚኖሩን መርኃግብሮች ፍጻሜውን ያገኛል።

ዛሬ በመጨረሻው ቀን፦

#በአዲስአበባ "ለዘር ጥያቄ ግሩም ምላሽ የሰጠኝ አርሶ አደር" እና "ሙስሊምና ክርስትያን ድንቅ ተዓምር ሰሩ" የተሰኙ ዶክመንተሪዎች ለዕይታ ይቀርባሉ።
📍በጣሊያን ባህል ማዕከል 🕒 ከ 11፡ 00 ሰዓት ጀምሮ መታየት ይጀምራሉ።

#በአዳማ "Zeyse" የተሰኘው ዶክመንተሪ ይቀርባል።
📍በኦሊያድ ሲኒማ 🕒 ከ 10፡00 ሰዓት ጀምሮ መታየት ይጀምራል።

በፊልም ፌስቲቫሉ ለሚገኙ ተሳታፊዎች በሰርተፊኬት አዘጋጅተናል።

📣 መግቢያው #በነጻ ነው።

ለበለጠ መረጃ ቻናላችንን ይቀላቀሉን 👉  https://publielectoral.lat/TimretEth
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM