TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የመከላከያ ቀን~የካቲት 7‼️

ዘንድሮ ለሰባተኛ ጊዜ የሚከበረው የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት ቀን በአየር ኃይልና በኦሮሚያ ክልል መንግሥት ትብብር #በአዳማ ከተማ እንደሚከበር፣ የኢፌዴሪ መከላከያ ኢንዶክትሪኔሽንና የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት አስታወቀ፡፡ በዓሉም የካቲት 7 ቀን 2011 ዓ.ም. እንደሚከበር ተገልጿል፡፡

ዳይሬክተሩ ሜጀር ጄኔራል #መሐመድ_ተሰማ እንዳስታወቁት፣ በዓሉ ‹‹ሕገ መንግሥታዊ ታማኝነታችንና ሕዝባዊ ባህርያችንን ጠብቀን የተጀመረውን ለውጥ እናስቀጥላለን›› በሚል መሪ ቃል ይከበራል፡፡ ‹‹ዓላማው ሠራዊታችን በሕገ መንግሥቱ የተሰጡትን ተልዕኮዎች መፈጸም የሚያስችል አቅም ዝግጁነት እንዳለው፣ በጎ ገጽታውን በማሳየት ከሕዝቡ ጋር ያለውን ጠንካራ ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከርና ለሕገ መንግሥታዊ ሥርዓት ደኅንነት ሲሉ ውድ ሕይወታቸውን የከፈሉ የሠራዊት አባላትን ለማሰብና የጀግንነት ክብር እንዲያገኙ ማድረግ ነው፤›› ሲሉ ገልጸዋል፡፡

በበዓሉ ምክንያትም በተለያዩ ደረጃዎች የሚካሄዱ የፓናል ውይይቶች፣ ስፖርታዊ ዝግጅቶች፣ የበጎ ተግባር ሥራዎችና ወታደራዊ ትርዒቶች እንደሚኖሩ ታውቋል፡፡
የዘንድሮውን በዓል ለየት የሚያደርገው አገሪቱ #በለውጥ ሒደት ውስጥ መሆኗ እንደሆነም ተገልጿል፡፡

ምንጭ፦ ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia