TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሻለቃ መስፍን በቁጥጥር ስር ዋሉ‼️

የብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን (ሜቴክ) ህብረት ማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪ የቀድሞ ምክትል ስራ አስኪያጅ ሻለቃ #መስፍን_ስዩም በሙስና ወንጀል #ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር ዋሉ።

ሻለቃ መስፍንን ፖሊስ ትላንት ፍርድ ቤት ይዟቸው ቀርቦ የነበረ ቢሆንም ተጠርጣሪው የተያዙበትን ምክንያት እንደማያውቁ ለፍርድ ቤቱ በመግለጻቸው የተጠረጠሩበትን ወንጀል በመርማሪ ፖሊስ ተነግሯቸው ለሰኞ ታህሳስ 8 ቀን 2011 እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጥቷል።

ፖሊስ እንደገለጸው ሻለቃ መስፍን በ7 ሚሊዮን 952 ሺህ 767 ብር የመንግስት ሃብት እንዲባክን በማድረግ ወንጀል ተጠርጥረዋል።

”በተጨማሪም በመጣራት ላይ ያለ 481 ሺህ ብር በላይ ሃብት እንዲባክን አድርገዋል” ተብሏል።

ምንጭ፦ ena
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሻለቃ መስፍን‼️

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ ወንጀል ችሎት በዛሬ ውሎው በቀድሞው ብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን /ሜቴክ/ የብረት ማኑፋክቸሪንግ ግንባታ ኢንዱስትሪ ምክትል ስራ አስኪያጅ ሻለቃ #መስፍን_ስዩም ላይ የአስር ቀናት የክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቀደ። ሻለቃ መስፍን ስዩም የቀድሞው ብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን የብረት ማኒፋክቸሪንግ ግንባታ ኢንዱስትሪ ምክትል ስራ አስኪያጅና የግብይትና ሽያጭ ኃላፊ በነበሩበት ወቅት ስልጣናቸውን በመጠቀም ያለግልጽ ጨረታ ግዥ በመፈጸም ተጠርጥረው ምርመራ ሲደረግባቸው መቆየቱ ይታወሳል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia