ሻለቃ መስፍን‼️

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 10ኛ ወንጀል ችሎት በዛሬ ውሎው በቀድሞው ብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን /ሜቴክ/ የብረት ማኑፋክቸሪንግ ግንባታ ኢንዱስትሪ ምክትል ስራ አስኪያጅ ሻለቃ #መስፍን_ስዩም ላይ የአስር ቀናት የክስ መመስረቻ ጊዜ ፈቀደ። ሻለቃ መስፍን ስዩም የቀድሞው ብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን የብረት ማኒፋክቸሪንግ ግንባታ ኢንዱስትሪ ምክትል ስራ አስኪያጅና የግብይትና ሽያጭ ኃላፊ በነበሩበት ወቅት ስልጣናቸውን በመጠቀም ያለግልጽ ጨረታ ግዥ በመፈጸም ተጠርጥረው ምርመራ ሲደረግባቸው መቆየቱ ይታወሳል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia