TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#AmharaRegion የጠቅላላ ሀኪም የቋሚ ቅጥር ፦ የአማራ ክልል ጤና ቢሮ በክልሉ ስር ባሉ ጤና ተቋማት ጠቅላላ ሀኪሞችን መድቦ ማሰራት ይፈልጋል። 👉 የስራ መደቡ መጠሪያ - ጠቅላላ ሀኪም 👉 ደመወዝ - 9,056 ብር (ዘጠኝ ሺ ሃምሳ ስድስት ብር) 👉 ብዛት - 631 (#ስድስት_መቶ_ሰላሳ_አንድ) 👉 የስራ ቦታ - በክልሉ ባሉ የጤና ተቋማት ክፍት ቦታዎች 👉 ተፈላጊ የትምህርት ዝግጅት - በጠቅላላ…
#AmharaRegion

የአማራ ክልል ጤና ቢሮ ከዚህ ቀደም ለ631 ጠቅላላ ሃኪሞች የስራ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል።

ዛሬ ይፋ በሆነው መረጃ ቢሮው ለ84 ሆስፒታሎች 409 ጠቅላላ ሃኪሞችን መቅጠሩ ታውቋል።

በኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ጤና ሚኒስቴር እና የክልሉ ጤና ቢሮ (በማችንግ ፈንድ) በመተባበር ለ631 ጠቅላላ ሃኪሞች የቅጥር ማስታወቂያ ቢወጣም ቢሮው አወዳድሮ ሊቀጥር ያቻለው 409 ጠቅላላ ሀኪሞችን ነው።

የአብክመ ጤና ቢሮ የሰዉ ሃብትና ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዳኛቸዉ ደሬ ፤ " የማችንግ ፈንድ ለ631 ጠቅላላ ሃኪሞች በጀት ቢለቅም በገባያ ላይ 409 ጠቅላላ ሃኪሞች ብቻ ነው የተገኙት " ሲሉ ገልፀዋል

የክልሉ ጤና ቢሮ በቀጣይ ጊዜ ለቀሩት 222 ጠቅላላ ሃኪሞች የቅጥር ማስታወቂያ እንደሚወጣ አሳውቋል።

ያልተቀጠሩ በተለያየ ሙያ ያሉ የጤና ዘርፍ ባለሙያዎች በነበረዉ ሃገራዊ ችግር ምክንያት ቢሮዉ " በሙሉ በጀቱን ለህልዉና ዘመቻ በማዋሉ " እደሆነ ገልፆ በቀጣይ ጊዜያት ከጤና ሚንስቴር እና ከአጋር አካላት ጋር በመነጋገር የቅጥር ማስታወቂያ እንደሚያወጣ ገልጿል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሰሜን ሸዋ ዞን ፤ በኤፍራታና ግድም ወረዳ እና በቀወት ወረዳ እንዲሁም በኦሮም ብሄረሰብ ዞን አዋሳኝ አካባቢ በተፈጠረው ችግር ምክንያት ተዘግቶ የነበረው የፌድራል መንገድ ከደሴ ወደ አዲስ አበባ ክፍት ሆኖ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑ አሳውቋል። መንገዱ ወደ አገልግሎት የተመለሰው በሰሜን ሸዋ ዞን አመራሮችና በኦሮሞ ብሄረሰብ ዞን አመራሮች ፣ በፀጥታ አካላቶች እንዲሁም በሀገር ሽማግሌዎች በተሰሩ…
#AmharaRegion

በቅርቡ በአማራ ክልል በሰሜን ሸዋ እና በኦሮሞ ብሔረሰብ ዞኖች አስተዳደር አጎራባች አካባቢዎች የፀጥታ ችግር ተፈጥሮ እንደነበር አይዘነጋም።

ይህንን ተከትሎ ዳግም ግጭት እንዳይፈጠር እና ሰላምን ለማጠናከር በአጣዬ ከተማ ትላንት የምክክር መድረክ ተካሂዷል።

መድረኩ ሰላምን ለማጠናከር የሚጠቅሙ አንኳር ሀሳቦች የተነሱበት መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን በዋናነት ለግጭቱ መንስኤ የሆኑ አካላት በሕግ እንዲዳኙና ማኅበረሰቡም አሳልፎ እንዲሰጥ መግባባት ላይ ተደርሷል።

የሃይማኖት አባቶች ሰላም የሁሉም ነገር መሰረት የሕዝቦች ትስስር ዋልታ ነው፤ የሰው ልጅ ሁሉ ደሙ አንድ ነው፤ በሰውነቱ ሁሉም ከአንድ የተገኘ ነውም ብለዋል።

ምክክሩ የተጠናቀቀው ባለ ሰባት ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ሲሆን የአቋም መግለጫው በዚህ ተያይዟል ፦ https://telegra.ph/Amhara-Region-04-27

ምንጭ፦ የአማራ ክልል የሰላምና የሕዝብ ደኅንነት ጉዳዮች ቢሮ

@tikvahethiopia
#AmharaRegion #እንድታውቁት

ከዛሬ ግንቦት 9 ጀምሮ በአማራ ክልል የጦር መሳሪያ ምዝገባ ይካሄዳል።

ይኸው የጦር መሳሪያ ምዝገባ ለአራት ቀናት የሚቆይ ሲሆን በክልሉ ከዚህ በፊት ያልተመዘገበ መሳሪያ የታጠቀ ግለሰብ በአካባቢው ባሉ የምዝገባ ማዕከላት መሳሪያውን ማስመዝገብ እንዳለበት ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

የአማራ ክልል ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ምዝገባው የአማራን ህዝብ ደህንነት ለማስጠበቅ አጋዥ ኃይል ለማጠናከር ያለመ እንደሆነ አመልክቷል።

@tikvahethiopia
#AmharaRegion

የአማራ ክልል የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ፤ በክልሉ ከ4 ሺህ በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን አስታውቋል።

ቢሮው ዛሬ ግንቦት 15/2014 ዓ.ም. በሰጠው መግለጫ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር የዋሉት ከሰሞኑን መንግሥት ያካሄደውን የሕግ ማስከበር ዘመቻ ተከትሎ መሆኑን አመልክቷል።

የክልሉ የሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ዳሳለኝ ጣሰው የአማራ ክልል ዘላቂ ሰላም ለማስጠበቅ ሥራውን አጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

በቁጥጥር ሥር ከዋሉት ከ4 ሺ በላይ ሰዎች መካከል 40 የሚሆኑት ከዚህ ቀደም በፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተብለው ፍርድ የተላለፈባቸው መሆናቸው የተጠቀሰ ሲሆን 210 የሚሆኑት ደግሞ በነፍስ ግድያ የተጠረጠሩ መሆናቸውን ገልፀዋል።

አቶ ዳሳለኝ ጣሰው በአሁኑ ወቅት መንግሥት ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ ከሚደረግ ሥራ ውጭ ክልሉ አስተማማኝ ሰላም ላይ ነው ሲሉም ገልፀዋል።

" ትክክለኛውን የፋኖ ስም የማይወክሉ፣ በፋኖ ስም ተደራጅተው በሕዝብ ላይ የተለያዩ ሕገ ወጥ ድርጊት የሚፈጽሙ ቡድኖችን መንግሥት አይታገስም " ሲሉ ተደምጠዋል።

@tikvahethiopia
#AmharaRegion

በአማራ ክልል የ12ኛ ክፍል ፈተና በ10 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ በሚገኙ 31 ማዕከላት ይሰጣል፡፡

ፈተናው ያለምንም የጸጥታ ችግር እንዲጠናቀቅ እየሠራ መሆኑን የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ገልጿል።

በክልሉ ሁሉም የመፈተኛ ተቋማት እና ማዕከላት በቂ የጸጥታ ቅድመ ዝግጅት መደረጉን ምክትል ኮሚሽነር እንየው ዘውዴ ገልጸዋል፡፡

በተመሳሳይ ወረዳን ማዕከል አድርጎ ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በተቀመጠው ጊዜ ለማድረስ በቂ የትራንስፖርት አገልግሎት ዝግጅት ማድረጉን የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ውቤ አጥናፉ ተናግረዋል፡፡

ተማሪዎች የወረዳ ትራንስፖርት ቢሮ በሚያወጣው መርሃ ግብር መሰረት በጊዜ እየተገኙ እንዲስተናገዱ ጠይቀዋል፡፡

ሀገራዊ ግዴታቸውን በአግባቡና በሀላፊነት የማይወጡ የትራንስፖርት ማህበራትና ባለሀብቶች በትራንስፖርት መመሪያ እና በሕግ ይጠየቃሉ ብለዋል፡፡

ተማሪዎች በሚጓጓዙባቸው ቀናት መደበኛ ትራንስፖርት ስለማይኖር ሕዝቡ ቅድመ ዝግጅት በማድረግ እንዲተባበር ጥሪ አድርገዋል፡፡

ምንጭ፦ አሚኮ

More : @tikvahuniversity
#AmharaRegion

የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ተማሪዎች በራሳቸው አቅም ብቻ ተማምነው ወደፈተና ማዕከላት እንዲመጡ ጠየቀ።

በራሱ በመተማመን መፈተን ያልፈለገ ተማሪ ወደ ማእከላት ባይመጣ ይመረጣል ብሏል ቢሮው።

ከሰሞኑ በጥቂት ማእከላት የተፈጠረው ክስተት የአማራ ክልልን ህዝብና ተማሪዎችን የማይመጥን ድርጊት ነው ሲልም ገልጿል።

በቀጣይ ሳምንት ፈተና የሚወስዱት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከተጠናቀቀው የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ሂደት በመማር ፍጹም ለአሉባልታና ለወሬ ሳይበገሩ ፈተናቸውን በሰላም እንዲወስዱ የአማራ ክልል ትምህርት ቢሮ ጥሪ አቅርቧል።

ለቀጣዩ ፈተና ከወረዳ ጀምሮ ያሉ አካላት ሰፊ ቅድመ ዝግጅት ማድረጋቸው ተገልጿል።

የአማራ ክልል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ፎረም በበኩሉ ፤ በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ በጥቂት ማእከላት የተፈጠረው ችግር የወላጆችን ፣የመምህራንን እና አጠቃላይ የማህበረሰቡን ልፋት መና ያስቀረ ፤ በቀጣይ በፍጹም መደገም የሌለበት ስህተት ነው ብሏል።

ተማሪዎች ዩንቨርስቲ የሚመጡት ፈተና ለመፈተን እንጂ ለሌላ ተልእኮ አለመሆኑን በመገንዘብ የተቀመጡትን ህግና ደንቦች አክብረው እንዲፈተኑ ጠይቋል።

የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የፈተና መርሐግብር ከጥቅምት 08 እስከ 11/ 2015 ዓ. ም የሚሰጥ ሲሆን በአማራ ክልል ብቻ ከ119,000 በላይ ተማሪዎች ለፈተና ይቀመጣሉ።

በዚሁ አጋጣሚ ፦

ውድ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰቦቻችን ከባለፈው የማህበራዊ ሳይንስ ፈተና ጋር በተያያዘ በተለያዩ ተቋማት የተፈተኑ ተማሪዎች አስተያየት፣ የወላጆችን መልዕክት ስንቀበል ውለናል አሁንም እየተቀበለን ሲሆን ተማሪዎች መረጃ ስትልኩ " ሰማሁ " ፣ " እየተባለ ነው "  እያላችሁ ሳይሆን በትክክል የምታውቁትን እና ያረጋገጣችሁትን ብቻ እንድትልኩ እንጠይቃለን።

@tikvahethiopia
#AmharaRegion

ከአዲስ አበባ ወደ ባህር ዳር ከተማ የሚወስደው መንገድ ከትላንት ከሰዓት ጀምሮ ደጀን ከተማ ላይ ተዘግቷል።

በዚህ ምክንያት የሀገር አቋራጭ ትራንስፖርት አገልግሎት ተቋርጣል።

በዛሬው ዕለት ደግሞ የንግድ እንቅስቃሴ መቆሙ እና የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት መዘጋታቸው ተገልጿል።

ጉዳዩን በተመለከተ የከተማው የሰላም እና ጸጥታ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አንዳርጌ ዘውዱ ተከታዩን ቃል ለ " ኢትዮጵያ ኢንሳይደር " ድረገፅ ሰጥተዋል ፦

" ደጀን ከተማ የሚያስገባው መንገድ የተዘጋው ፤ የክልሉ ልዩ ኃይል መበተንን በሚቃወሙ ነዋሪዎች ነው።

ወጣቶች ተቃውሟቸውን ማሰማት የጀመሩት ከትላንት አርብ ከሰዓት ጀምሮ ነው።

ከቀኑ አስር ሰዓት ገደማ ላይ ተቃውሞ የሚያሰሙ ነዋሪዎች፤ ወደ ከተማዋ የሚያስገባው መንገድ ላይ ድንጋይ በማስቀመጥ የተሽከርካሪዎች ፍሰት እንዲቆም አድርገዋል።

በትላንቱ ተቃውሞ የፌደራል ፖሊስ ንብረት የሆነ አንድ ‘ፒክ አፕ’ ተሸከርካሪ ተቃጥሏል የሚል መረጃ እደርሶናል።

ድርጊቱን የፈጸመው አካል ማንነት ግን ገና አልተረጋገጠም። የትኛው ነው ያቃጠለው? ‘ወጣቱ ነው ወይስ ለመንግስትም ለህዝብም አልመች ያለ ጠላት ነው?’ የሚለውን ነገር አልደረስንበትም።

የሀገር ሽማግሌዎች፣ የሃይማኖት አባቶች እና ተሰሚነት አላቸው በተባሉ ወጣቶች አማካኝነት፤  የነዋሪዎችን ተቃውሞ ለማረጋጋት ጥረት እየተደረገ ነው።

የሚደረገው ንግግር፤ በከተማይቱ በተነሳው ተቃውሞ ሰዎች እንዳይጎዱ የማድረግ ዓላማ ያለው ነው። "

የከተማዋ ኮሚዩኒኬሽን ቡድን መሪ አቶ ሞኙ ሆዴ አሳየ በበኩላቸው ተከታዩን ብለዋል ፦

" ከደጀን ከተማ መግቢያ በተጨማሪ በከተማው የሚያልፈው መንገድ ተዘግቷል።

በደጀን በየሳምንቱ ይካሄድ የነበረው የቅዳሜ ገበያ በዛሬው ዕለት ሳይከናወን ቀርቷል።

ገበያ የመጣውም ህዝብ እንዲመለስ ተደርጓል። ሱቅም ተዘግቷል። የሰው እንቅስቃሴ አለ፤ ወጣቱ ላይ ታች ይላል። የንግድ እንቅስቃሴ ግን የለም።

ቅዳሜ በርካታ ህዝብ ገበያውን የሚያሳልጥበት ቀን ነው። ግን ዛሬ አንድም የለም። "

በደጀን ከትላንት አንስቶ በተነሳው ተቃውሞ ምክንያት ዛሬ ቅዳሜ ወደ ከተማዋ የመጣ ሀገር አቋራጭ ተሽከርካሪ አለመኖሩ ተነግሯል።

ሀገር አቋራጭ የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎችም መንገድ በመዘጋቱ ምክንያት ዛሩ ወደ ባህር ዳር አውቶብሶችን አለማሰማራታቸውን አስታውቀዋል።

Credit : Ethiopia Insider

@tikvahethiopia
#AmharaRegion

በአማራ ክልል በሲቪል ሰዎች ላይ የሞት፣ የአካልና የንብረት ጉዳት የደረሰ መሆኑን እንዲሁም ከደሴ - አ/አ መንገድ በተለያየ ጊዜ መዘጋቱን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ገለፀ።

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ ክልል የተወሰኑ አካባቢዎች እየተካሄደ ያለው “ የሕግ ማስከበር ዘመቻ ” በሰብአዊ መብቶች ላይ ያለውን አንድምታና ተጽእኖ በቅርበት እየተከታተለ እንደሚገኝ ዛሬ ባወጣው መግለጫ አሳውቋል።

ኮሚሽኑ ፤ በሰሜን ጎንደር፣ ሰሜን ወሎ እና ሰሜን ሸዋ ዞኖች አንዳንድ አካባቢዎች ግጭት ያለ መሆኑን፤ በተለይም ሸዋ ሮቢት፣ አርማኒያ፣ አንጾኪያ፣ ገምዛ እና ማጀቴ በመከላከያ ሰራዊት እና በአካባቢው ታጣቂዎች መካከል የተኩስ ልውውጥና በከባድ መሣሪያ ጭምር የታገዘ ጥቃት መኖሩን ገልጿል።

በዚህም ምክንያት በሲቪል ሰዎች ላይ የሞት፣ የአካልና የንብረት ጉዳት የደረሰ መሆኑን እንዲሁም ከደሴ ወደ አዲስ አበባ የሚወስደው መንገድ በተለያዩ ጊዜያት የተዘጋ መሆኑን ለማረጋገጥ መቻሉን ኢሰመኮ አሳውቋል።

በተጨማሪም በክልሉ ያሉ የተወሰኑ ተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባላት፣ የክልል ልዩ ኃይሎችን እንደገና የማዋቀር ውሳኔን በመቃወም የተካሄዱ ሰልፎችን መርተዋል/አስተባብረዋል የተባሉ የተወሰኑ ወጣቶች እና ከፋኖ ቡድን ጋር ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ የተወሰኑ ሰዎች እንደታሰሩ ኢሰመኮ ተረድቻለሁ ብሏል።

ኢሰመኮ ፤ ባለፉት ሁለት ዓመታት በሰሜን ኢትዮጵያ የተካሄደው ጦርነት በሲቪል ሰዎች ላይ መጠነ ሰፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰትና ጉዳት ማድረሱን በተደጋጋሚ መግለፁን ያስታወሰው ኢሰመኮ ፤  በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍሎች የሚፈጠሩ ተጨማሪ ግጭቶች ሰብአዊ መብቶች ላይ አስከፊ/ከባድ ጥሰቶች የሚያስከትሉ መሆኑን በመገንዘብ ሁሉም የሚመለከታቸው ወገኖች ችግሩን በሰላማዊ መንገድና በውይይት እንዲፈቱ፣ ግጭቱን ከሚያባብሱ ድርጊቶችና ንግግሮች እንዲቆጠቡ ጥሪ አቅርቧል።

ኮሚሽኑ ፤ ስለደረሰው ጉዳት ሁሉ አስፈላጊውን ምርመራ በማድረግ ተጠያቂነት እንዲረጋገጥ፣ እንዲሁም በማናቸውም ሁኔታ የሚፈጸሙ እስራቶች ሕግን መሠረት ያደረጉ በተለይም “የጥብቅ አስፈላጊነት፣ ተመጣጣኝነትና ከመድልዎ ነጻ መሆን” የሚሉትን የሰብአዊ መብቶች መርሆችን ያከበሩ መሆናቸውን መንግሥት እንዲያረጋግጥ ጠይቋል።

@tikvahethiopia
#AmharaRegion

" 522 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ፤ የተገኘው ሀብት ግን ዝቅተኛ ነው " - የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ

በአማራ ክልል ፤ #በጦርነት ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢዎች መልሶ ለመገንባት 522 ቢሊዮን ብር ያስፈልጋል ሲል የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ አሳውቋል።

ይህን ያሳወቀው የአማራ ክልል ገንዘብ ቢሮ የመንግሥትና የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ዓመታዊ የአጋርነት የምክክር መድረክ በተካሄደበት ወቅት ነው።

ባለፉት ዓመታት በሀገሪቱ በተከሰተው ችግር 1 ነጥብ 1 ሚሊዮን ዜጎች ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተፈናቅለው በክልሉ እንደሚገኙ የገለፀው ቢሮው ፤ 11 ነጥብ 4  ሚሊዮን ሕዝብ  ደግሞ በጦርነቱ ምክንያት በከፍተኛ  የኢኮኖሚና ማኅበራዊ ጫና ውስጥ እንደሚገኙ ጠቁሟል።

ሰባት ዞኖችና ሶስት ሜትሮፖሊታንት ከተሞች በጦርነት ምክንያት ከፍተኛ ጉዳት እንደደረሰባቸእ የተገለፀ ሲሆን እነዚህን ዞኖች መልሶ ለማቋቋም እና  መልሶ ለመገንባት ከ522 ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ይጠይቃል ብሏል።

ጉዳት የደረሰባቸውን ዞኖች  መልሶ ለመገንባት ጥረት ቢደረግም  የተገኘው ሀብት ዝቅተኛ በመኾኑ የተፈለገውን ውጤት ማምጣት አለመቻሉን ቢሮው አመልክቷል።

ቢሮው ፤ መንግሥት ከሚያደርገው ሥራ ባለፈ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች በተለያዩ የልማት ሥራዎች እና በመልሶ ግንታ ሥራ ላይ እየተሳተፉ መሆኑ የተገለፀ ሲሆን በዚህ ዓመትም በሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች 374 ፕሮጀክቶች በክልሉ እየተከናወኑ ነው ተባቧል።

ድርጅቶች በቀጣይም የጀመሩትን ሥራ አጠናክረው እንዲቀጥሉ ጥሪ ቀርቧል።

#AMC

@tikvahethiopia
#AmharaRegion #Gojjam

ከደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋርዱላና ኧሌ ዞኖች ተነስተው ለደን ምንጣሮ ስራ ወደ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ እያመሩ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ጎዛምን አካባቢ በ " ፋኖ ታጣቂዎች " የተያዙ የቀን ሰራተኞችን ለማስለቀቅ ጥረት እያደረገ መሆኑን የምልመላና የቅጥር ሂደቱን የፈፀመው " ኒኮቲካ ኮንስትራክሽንና ትሬዲንግ ኃ/የተ/የግል ማህበር አሳውቋል።

የታገቱት ሰራተኞች ብዛታ 272 እንደሆነ ተነግሯል።

የድርጅቱ የፕሮጀክት ስራ አስኪያጅ አቶ ሙልጌታ አለነ ምን አሉ ?

" በአጠቃላይ 4 ሺህ ሰራተኛ ነው ያስፈቀድነው። 272 ሰራተኛ ከጋርዱላና አሌ ዞን ወስደን መንገድ ላይ ችግር ገጥሞናል። ችግሩን በአካል እኔው እራሴ ሄጄ በሽማግሌም፣ በምንም እንዲፈታ እየሞከርን ነው " ብለዋል።

ቁጥርን በተመለከተ ፤ " ከጋርዱላ 246 እና ከአሌ 38 በድምሩ 282 ሰራተኞች ነው የሄዱት " የሚባለው እጅግ በጣም ስህተት ነው ብለዋል። " ዶክመንት አለን እያንዳንዱ ዶክመንት ስላለን በዛ ነው የምናወራው ፤ የሰው ልጅ ነው የወስድነው ማንም እየተነሳ ይሄ ነው ማለት አይችልም። ስንወስዳቸውም በህጋዊ መንገድ ተፈራርመን ነው። ቁጥራቸው 272 ነው " ብለዋል።

ይሄን ያህል ብዙ ኪ/ሜ ርቀት ሄዶ ለህዳሴ ግድብ ሰራተኛ መመልመሉን ምን አመጣው ? ለሚለው ጥያቄ ፤ " ጠንካራ ሰራተኞች ስለሆኑን ነው " ሲሉ መልሰዋል። ባለፈው ዓመት ድርጅቱ በተመሳሳይ ከየክልሉ ከአማራ፣ ከቤኒሻንጉል፣ ከደቡብ፣ ከሁሉም ሰራተኛ ወስዶ እንደነበር አስታውሰው በተደረገው ግምገማ በስራቸው ውጤታማ ስለሆኑ ነው ደብዳቤ ተፅፎ ሰራተኞቹ የተወሰዱት የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

በአማራ ክልል ውስጥ ጦርነት እንዳለና መረጋጋት እንደሌለ እየታወቀ ለምን በዚህ መንገድ እንዲሄዱ ተደረገ ? በሚል ለቀረበው ጥያቄ ፤ " እኛ የያዝነው የሀገር ፕሮጀክት ነው። ውል ገብተናል በውሉ መሰረት መስራት አለብን። መንገዱም ሌላ መንገድ የለውም አምናም (በ2015 ዓ/ም) ከ2 ሺህ በላይ ሰራተኞችን ከኮንሶ ስንወስድ በዚሁ በራሱ መንገድ ነው። አሁንም ህዳር ላይ ነበር የምንገባው ባለው ሁኔታ ሳንገባ ቀረን ሲረጋጋ ተረጋግቷል ግቡ ተባልን ገባን " ሲሉ መልሰዋል።

' ከፋኖ ታጣቂዎች ለታጋቾች #ገንዘብ ተጠይቋል ፣ ድርጅቱ ገንዘብም ሰጥቷል '' እየተባለ ስለሚነገረው ጉዳይ በተመለከተ ፤ " እኛ ሙሉ መረጃ በሁለት ቀን እንሰጣለን ከዚህ በላይ ማለት ያለብኝ የለም " ብለዋል።

የሰራተኞቹ ደህንነትን በተመለከተ " ደህንነታቸው በጣም ሰላም ነው " ብለዋል። ይህን ያረጋገጡት እዛው ቅርብ ስለሆነ መሆኑን ገልጸዋል። አሁን በአካል እዛው አካባቢ በቅርብ ሆነው እየተከታተሉ እና #በሽምግልና ልጆችን ከእገታ ለማስወጣት ጥረት እያደረጉ እንደሆነ አስረድተዋል።

ድርጅቱ በኢትዮጵያ የንግድ ህግ የተመዘገበ ከመላው ሀገሪቱ ሰራተኞችን ለስራ እየመለመለ የሚቀጥር እንደሆነ አሳውቀዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በ 'ፋኖ ታጣቂ ኃይሎች' የተያዙ ሰራተኞች ቤተሰቦች ሰራተኞቹ ፦
* አስቸጋሪ ሁኔታ ላይ እንዳሉ፣
* ጫካ ውስጥ ታስረው እንደሚገኙ፣
* ምግብም እያገኙ እንዳለሆነ፣
* ወታደራዊ ስልጠና እንዲወስዱና ወደ ውጊያ ውስጥ እንዲገቡ የማስገደድ ሁኔታ እንዳለ፣
* የግድያ / ርሸና ዛቻም እንደሚደርስባቸው ተናግረዋል።

ወጣቶቹ ታግተው ከተወሰዱ 4ኛው ሳምንት እየጀመረ ቢሆንም እስካሁን ድረስ ይህ ነው የሚባል መፍትሄ የሰጣቸው አካል እንደሌለ ቤተሰቦች ገልጸዋል። የፌዴራልም የክልል መንግሥትም ዝም ማለታቸው እንዳሳዘናቸው ተናግረዋል።

ቃላቸውን ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ የሰጡት ' የአማራ ፋኖ የጎጃም ቃል አቀባይ ነኝ ' ያሉት ፋኖ ማርሸት ፀሀዩ ፤ " ... ከተቻለ በ72 ሰዓታት ውስጥ ወጣቶቹን ለቀይ መስቀል እናስረክባቸዋልን " ብለዋል።

ስለ ጉዳዩ በዝርዝር ምን አሉ ?

➢ " እኛ ያረጋገጥነው እነዚህ ልጆች አውቀውም ይሁን ተጭበርብረው ጎጃም ውስጥ ወደሚገኘው የብርሸለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ ሲወሰዱ ነው ያገኘናቸው " ብለዋል።

➢ የታገቱ ወጣቶች ብርሸለቆ ወታደራዊ ማሰልጠኛ እየተወሰዱ ስለመሆኑን ምን ማስረጃ አላችሁ ? ለሚለው ጥያቄ ፤ " ተጨባጭ የሆነ ማስረጃ አለን። በወታደራዊ ቋንቋ ጠርናፊ የሚባል ቃል አለ ይህ ማለት አንድን የሚንቀሳቀስ ወታደራዊ ኃይል፣ ምልምል / የታጠቀ ኃይል የሚመራ ማለት ነው። የነዚያ ተጓዦች ተርናፊዎች የአስር አለቃ ማዕረግ ሳይቀርብያላቸው አክቲቭ ወታደሮች መሆናቸውን ከራሰቸው መታወቂያ ዕዛቸውን፣ ኮራቸው፣ ክ/ጦራቸውም ፣ ሻለቃቸውን የሚጠቅስ መታወቂያ ይዘዋል። የመከላከያ አርማ ያለው መታወቂያና አክቲቭ መሆናቸውን አረጋግጠናል " ብለዋል።

➢ "ከያዝናቸው ውስጥ ያነጋገርናቸው ወደ መሰረታዊ ውትድርና እንደሚገቡ እንደሚያውቁ ፣ በዛ ያሉት ግን ግንዛቤው እንደሌላቸው ግን ከፍተኛ ገንዘብ እንደሚከፈላቸው ነው ያረጋገጥነው" ሲሉ አክለዋል።

➢ ሌላው ከተለያየ ኢትዮጵያ ክፍል ወደህዳሴ ግድብ የሚሄዱ ሰራተኞችም ሆነ ጎብኝዎች አዲስ አበባን ረግጠው ፣ በአምቦ አድርገው በነቀምት ፣ አሶሳ ነው ወደ ጉባ የሚገቡት በአማራ ክልል አቋርጠው የሚሄዱበት ታሪክ አልነበረም ሲሉ ተደምጠዋል። " አሁን ላይ በአማራ ክልል ውጊያ እንዳለ እየታወቀ በአ/አ አማራ ክልል አድርገው ወደ ጉባ የሚሄዱበት ምክንያት የለም " ሲሉ አክለዋል።

➢ የወጣቶቹን ቀጣይ ዕጣ ፋንታ በተመለከተ እኚሁ ቃል አቀባይ ፤ " ስለ ፋኖ ዓላማ ፣ ስለ አማራ ትግል አስፈላጊውን ትምህርት ሰጥተናቸው ለቀይ መስቀል ልናስረክባቸው በዝግጅት ላይ ነን " ብለዋል። " ቀይ መስቀል ወደኛ እየመጣ ስለሆነ ከተቻለ በ72 ሰዓት ካልሆነም በ100 ሰዓት ውስጥ ለማስረከብ ዝግጁ ነን። ሁኔታውን አጥንተው ስለሚገቡ በደረሱበት ሰዓት እናስረክባለን። " ብለዋል።

➢ በታጋቾች ላይ እየተፈፀመነው ስለሚባለው የግድያ ዛቻ፣ በግዳጅ ወደ ውጊያ እንዲገቡ የማድረግ ጉዳይ ተጠይቀው ፤ " ከያዝናቸው 240 ሰዎች ፦
• አንድም ሰው የአካል ድብደባ ደርሶበት ከሆነ፣
• በግድ ፋኖ እንዲሆን ጠብመንጃ እንዲሸከም ተገዶ ከሆነ ፣
• አንድም ሰው ያለ ፍላጎቱ እኛ የፈለግነውን ፕሮፖጋንዳ እንዲናገር ተገዶ ከሆነ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ፣ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ፣ ሂውማን ራይትስዎች አስፈላጊው አጣሪ ኮሚቴ ልከው ማጣራት ይችላሉ " ብለዋል።

የጋርዱላ ዞን አስተዳዳሪ አቶ ብርሃኑ ኩናሎ ምን አሉ ?

° የፌዴራል መንግሥት ፤ የአማራ ክልልም መንግሥት ከዞኑ ጋር በቅንጅት እየሰሩ መሆኑን ነገር ግን እስካሁን ውጤት እንዳልመጣ ተናግረዋል።

° ታጋቾች #በነፍስ_ወከፍ_300_ሺ_ብር እንዲከፍሉ መጠየቁን ነገር ግን ለማስቀለቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህንን መረጃ ያገኘው ከቪኦኤ ሬድዮ መሆኑን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia በአማራ ክልል በተለይ በሰሜን ሸዋ እና በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ትላንት በተጠናቀቀው የካቲት ወር በተፈፀሙ ጥቃቶች በርካቶች ተገድለዋል። ጉዳትም ደርሷል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ በወሩ ስለነበሩት ሁኔታዎች ከሚመለከታቸው አካላት ምላሽ ለማግኘት እጅግ በርካታ ቀናትን የወሰደ ሙከራ ቢያደርግም ምንም ምላሽ የሚሰጠ አካል አላገኘም። የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን ግን ስለነበሩት ሁኔታዎች…
#AmharaRegion

° " ህዝቡ በታጠቁ ቡድኖች ነው ለጥቃት የተዳረገው በገዛ ከተማው ነው መአት ያወረደበት ... ጥቃት ፈፃሚዎቹ ከአጎራባች ' ሸኔ ' ናቸው " - የአጣዬ ከተማ ከንቲባ

° " #ሀሰት_ነው የኦሮሞ አርሶ አደሮች እንጂ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት አይደሉም " " - አባገዳ አህመድ ማህመድ

በአማራ ክልል ፤ የሰሜን ሸዋን እና የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደርን በሚያጎራብቱ አካባቢዎች ላይ ግጭት ከጀመረ ከሳምንት በላይ ሆኖታል።

በተደጋጋሚ ፦
- የሰዎች ደም በሚፈስበት፣
- ንብረት በሚወድምበት ፣
- ሰዎች ቄያቸውን ለቀው በሚፈናቀሉበት በዚህ ቀጠና ባለፈው የካቲት ወር ውስጥም በርካቶች መገደላቸው ይታወሳል።

አሁን ደግሞ #ከ8_ቀናት በፊት የተቀሰቀሰው ግጭት እጅግ መባባሱን ነዋሪዎች ተናግረዋል። በመነሻው ላይ በሁለቱም በኩል እርስ በእርስ መወነጃጀል ያለ ሲሆን በኤፍራታ ግድምና ቀወት ውስጥ ግጭቱ ከፍቶ መዋሉ ነው የተሰማው።

በሁለቱም በኩል ያሉት ነዋሪዎች ፣ የአጣዬ ከንቲባ ፣ የአካባቢው አባገዳ ምን አሉ ?

በኤፍራታ ግድም ወረዳ የአላላ ከተማ ነዋሪ ፤ ጦርነት ከተጀመረ 8 ቀን መያዙን ፣  ብዙ ቤቶች መቃጠላቸውን ገልጸዋል።

ነዋሪው " የአርሶ አደሮች ዱቄት ሳይቀር ፣ በግ ፣ ፍየል ፣ ግመል ፣ አህያ፣ ከብት በሙሉ ሙልጭ አድርገው ወስደውብናል። ኃላሸት የሚባል ሰውም ገድለውብናል እኛው ክልል ላይ ገብተው " ሲሉ ተናግረዋል።

ይህን ካደረጉ በኃላ ህዝቡ ተሬ እና ዘንቦ ወደሚባለው አካባቢ በለበሰው ልብስ ሸሽቶ ተጠልሎ እንደሚገኝ ገልጸዋል። " በተከታታይ 18 ሰዎችን ገድለውብናል "ም ብለዋል።

በኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር የሰንበቴ ነዋሪ ፤ " እስከ ጅሌ ጥሙጋ ባርሲሳ ፣ ካራ ሌንጫ ፣ መከና ወይም አጣዬ ከተማ ዙሪያ ባሉ ቀበሌዎች ከትላንትና ጀምሮ ተኩስ ነበር። ትላንት አንዲት ሴት እንዲሁም ግመልና ከብቶችም ተመተው ነበር ግጭቱ የቀጠለው በዚህ ነው፤ አንድ ሰው ሲሞት ሁለት ሰው ቆስለዋል፤ አንዱ ወደ አዳማ ተልኳል። ዛሬ ደግሞ 4 ሰው ሲሞት 3 ሰው ቆስሏል " ብለዋል።

ዋነኛው እቅዳቸው የጅሌ ጥሙጋ ከተማ #ሰንበቴን " እንይዛለን ፣ እናጠፋለን " የሚል ነው ሲሉ ገልጸዋል።

አንድ የአጣዬ ነዋሪ ደግሞ ፤ ሰሞኑን ግጭት ተባብሶ ዛሬ አጣዬን በተኩስ ልውውጥ ሲያናውጥ መዋሉን ፣ 5 ሰው መገደሉም. ጥቃት ፈፃሚዎቹ የታጠቁ አካላት " ሸኔ " ናቸው ብለዋል።

ሌላው የኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ፣ የሰንበቴ ነዋሪ " ግጭቱ የጀመረው #መጋቢት_አንድ ላይ ነው። ይህም በጅሌጥሙጋ ኮላሽ የሚባል ስፍራ 1 ሰው ገድለው 2 ሰው አቁስለው ከብቶችንም ነድተው ከሄዱ በኃላ ነው ግጭቱን የተስፋፋው " ሲሉ ተናግረዋል።

" ከባልች ቀበሌ እስከ ሰንበቴ እና መከና አጣዬ ድረስ ጦርነት ነው። የዛሬውን ለየት ያደረገው ታጣቂዎቹ #ከሰሜን_ሸዋ ተሰባስበው ፤ እራሳቸውን አደራጀትው ሌሊቱን በተሽከርካሪዎች ተጉዘው መጥተው ውጊያ መክፈታቸው ነው " ሲሉ አክለዋል።

ባለፉት 10 ቀናት 29 ሰዎች መገደላቸውን ተናግረው የተወሰዱት ከብቶችና የወደመው ንብረትም ከፍተኛ መሆኑን ጠቁመዋል።

ይህ አስተያየት #አልቀበልም ያሉት የአላላ ነዋሪው ፤ " አማራው ሲያጠፋ በአማራው አጥፊውን መዞ ለህግ ማቅረብ፤ ከኦሮሞውም ሲያጠፋ አጥፊውን መዞ ለህግ ማቅረብ ሰላም የሚያሰፍነው ይሄ ብቻ ነው " ሲሉ ገልጸዋል።

" በህግ እና በሽምግልና  ነገሩ መክሰም አለበት እነሱ የሚሉት ከጨፋ ጀምሮ እስከ ሸዋሮቢት ድረስ የኦሮሞ ቦታ ነው። አጣዬም #የኛ_ነች ፤ አላላም ፣ ሞላሌም ፣ ማጀቴም ... ሁሉም የኛ ነው የሚሉት። መንግስት ትኩረት ሰጥቶ ችግሩን ሊፈታው ይገባል " ብለዋል።

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን #አባገዳ አህመድ ማህመድ " መንገድ የለም። ከጅሌ ጥሙጋ እና አርጡማ ፋርሲ ወረዳዎች እንዲሁም ከዞን መገናኘት አልቻልንም " ብለዋል።

" በዚህ ምክንያት የሃይማኖት አባቶች እና አባ ገዳዎች ተሰባስበው መፍትሄው ምንድነው ? ለማለት መንገዱ ተከፍቶ ለህዝቡ ምግብ ለማድረስ ፣ የቆሰሉትንም ወደ ህክምና ቦታ ለመውሰድ ጥረት ላይ ነን። መንገድ ከተዘጋ 1 ወር ሊሆነው ነው። እኛም ሆነ መንግሥታዊ አመራሩ ሄደን ማየት አልቻልንም። የአማራ ክልልም #ታጣቂዎቹን_ስለሚፈሯቸው ቀርበው ለማነጋገር አልተቻለም። እኛ ጋር ያሉትን #ወሰናችሁን አልፋችሁ አትሂዱ እያልን እየመከርናቸው ነው ። " ገልጸዋል።

ነዋሪዎችና የአካባቢው አስተዳደሮች ጥቃቱን የከፈቱት " ሸኔ (የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት) " ናቸው ቢሉም አባገዳ አህመድ " ሀሰት ነው " ብለዋል።

" ሀሰት ነው የኦሮሞ አርሶ አደሮች እንጂ የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት አይደሉም። የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት እዚህ አልገባም። እየተዋጋ ያለው እራሱ ነዋሪው ነው " ብለዋል።

የአጣዬ ከተማ ከንቲባው ተመስገን ተስፋ ፤ ከተማዋና ህዝቡ በታጠቁ ቡድኖች ነው ለጥቃት የተዳረጉት ብለዋል።

አጣዬ ላይ ' #ወረራ ' መፈፀሙን ገልጸው " ሰውም አልቋል፤ ሚሊሻውም የሚችለውን ያህል ሞከረ አለቀ " ብለዋል።

ይህን የሚፈፅሙት ከአጎራባች  " #ሸኔ በሏቸው " ሲሉ የጠሯቸውን የታጠቁ ኃይሎች መሆናቸውን ገልጸዋል።

" ዋናው መፍትሄ መንግሥት ጠንከር ብሎ #እርምጃ መውሰድ ያለበት ላይ እርምጃ መውሰድ ፤ ይሄ ነበረ መፍትሄው  አሁን ባለው መንገድ ፣ #በእሹሩሩ ሰውም አለቀ " ብለዋል።

#የአጣዬ_ህዝብ የገዛ ከተማው ላይ እንዳለ መአት እንደወረደበት የገለጹት ከንቲባው " እጅግ በጣም አስቸጋሪ ነው፤ መንግስት ቢደርስልን ጥሩ ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

ከኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር በኩል ለጥፋቱ ለችገሩ " የፋኖ ታጣቂዎችን " ተጠያቂ ሲያደርጉ ከሰሜን ሸዋ ዞን በኩል ደግሞ " ሸኔን (የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት) " ተጠያቂ ያደርጋሉ።

NB. ባለፉት አምስት ዓመታት አጣዬ ከ10 ጊዜ በላይ የመቃጠል አደጋ አስተናግዳለች።

እስካሁን የአማራ ክልል መንግሥት ስለ ጉዳዩ ያለው ነገር የለም።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህ መረጃ #ባለቤትነቱ የቪ.ኦ.ኤ. ራድዮ (ጋዜጠኛ መስፍን አራጌ) መሆኑን ይገልጻል።

@tikvahethiopia
#AmharaRegion

አቶ መልካሙ ፀጋዬ በአቶ ጣሂር መሀመድ ምትክ የአማራ ክልል ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ ሆነው መሾማቸው ተነግሯል።

የአማራ ብልፅግና ፓርቲ፥" ርዕሰ መስተዳድር አቶ አረጋ ከበደ የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ከፍተኛ አመራር የሆኑትን አቶ መልካሙ ፀጋዬ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ኃላፊ በማድረግ ሹመዋል " ሲል አሳውቋል።

በዚህ ኃላፊነት ቦታ የነበሩት አቶ ጣሂር መሃመድ ከቦታው ተነስተዋል። ለምን በእሳቸው ምትክ ሌላ አዲስ ሰው እንደተሾመ / ከቦታው እንደተነሱ ፣ ለሌላ ሹመት እና ኃላፊነት ታጭተው እንደሆነ በግልጽ የተባለ ነገር የለም።

@tikvahethiopia
#AmharaRegion

በአማራ ክልል የሰሜን ወሎ ዞን ፤ የላስታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ እና የወረዳው ጤና ጽህፈት ቤት ኃላፊ በታጣቂዎች ጥቃት መገደላቸውን ቢቢሲ የአማርኛው አገልግሎት ዘግቧል።

የላስታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው መልሴ እና የወረዳው የጤና ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሚሊዮን አፈወርቅ ትላንት በተፈጸመ ጥቃት ነው የተገደሉት።

ባለስልጣናቱ ተኩስ የተከፈተባቸው ወልዲያ ከተማ የነበራቸውን ስብሰባ አጠናቀው እየተመለሱ በነበረበት ወቅት እንደሆነ ተነግሯል።

ጥቃቱ የተፈጸመው ከላሊበላ ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ ከምትገኘው " ኩልመስክ ከተማ " አቅራቢያ ነው።

ከሁለቱ ኃላፊዎች በተጨማሪም አንድ ሌላ ግለሰብ መገደላቸውን እና ሌሎችም መቁሰላቸውን ምንጮቹ ገልጸዋል።

ጥቃቱ ሲፈጸም አብረው የነበሩ ሌሎች የመንግስት ኃላፊዎች ወደ ላሊበላ ከተማ የሚያደርጉትን ጉዞ አቋርጠው ወደ ኋላ በመመለስ ኩልመስክ ከተማ ማደራቸው ተነግሯል።

አንድ የላሊበላ ከተማ ነዋሪ በሰጡት ቃል " ማታ በዋና አስተዳዳሪው መኖሪያ ቤት ሲለቀስ ነው ያመሸው። አሁንም የአካባቢው ነዋሪ ወደ ለቅሶ እየሄደ ነው " ብለዋል።

የላስታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪው አቶ ጌታቸው መልሴ የቀብር ስነ ስርዓት ጥቃቱ ከተፈጸመበት አካባቢ በምትገኘው የትውልድ ከተማቸው " ገነተ ማርያም " እንደሚፈጸም ተገልጿል።

የጤና ፅ/ቤት ኃላፊው አቶ ሚሊዮን አፈወርቅ የቀብር ስነ ስርዓት በላሊበላ ከተማ እንደሚፈጸም የወረዳው አስተዳደር ውስጥ የሚሰሩ ኃላፊን ዋቢ በማድረግ ቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት ዘግቧል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Amhara የኤፍራታ ግድም ወረዳ አስተዳዳሪ ተገደሉ። በወረዳው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎች የወረዳውን አስተዳዳሪ አቶ አልብስ አደፍራሽን ትለንትና በምሽት በመግባት እንደገደሏቸው ተሰምቷል። ወረዳው ባወጣው የሀዘን መግለጫው ፥ " አቶ አልብስ ለዓመታት በቀውስ ነጋዴዎች ለችግር ተጋልጦ የሴራ ፖለቲካ መሸቀጫ የተደረገውን የጀውሃና አካባቢው ማህበረሰብ ቀርቦ በማወያየት መተማመን ፈጥሮና አደራጅቶ ወደ ቀደመ…
#AmharaRegion

ወ/ሮ ሚሊሹ በቀለ ተገደሉ።

የቀወት ወረዳ አስተዳደር ፅ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሚሊሹ በቀለ ከተማ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ በተተኮሰባቸው ጥይት ተገደሉ።

ወ/ሮ ሚሊሹ በዛሬው እለት ነው የተገደሉት።

እንደ ወረዳው መረጃ ፥ የመንግስታዊ አገልግሎት ላይ ውለው ከተማ ውስጥ በመንቀሳቀስ ላይ እያሉ ነው ጥቃት ተሰንዝሮባቸው የተገደሉት።

ግድያ የተፈጸመባቸው አመራሯ በእናትነት ላይ ነፍሰ ጡርነትን ይዘው እንደነበር ተገልጿል።

የወረዳው አስተዳደር ዛሬ ምሽት ባወጣው መግለጫ " ግድያው የተፈጸመው በጽንፈኛ አካላት #በተተኮሰ ጥይት ነው "  ብሏል።

ከቀናት በፊት የኤፍራታ ግድም ወረዳ አስተዳዳሪው አቶ አልብስ አደፍራሽ #በታጣቂዎች_መገደላቸው ይታወሳል።

በሌላ በኩል ከሰሞኑን በወልዲያ ከተማ የመንግስት ባለስልጣናት እና ተቋምን ዒላማ ያደረጉ #የቦምብ ጥቃቶች ተፈጽመው እንደነበር ነዋሪዎች ለቢቢሲ አማርኛ ክፍል ተናግረዋል።

ጥቃቶቹ በዞኑ አስተዳደር ጽህፈት ቤትና በመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች መኖሪያ ቤት ላይ እንደተፈጸሙ ነው የተሰማው።

ጥቃቱ አነጣጥሮባቸው ነበር ከተባሉት ውስጥ፦

➡️ የሰሜን ወሎ ዞን ብልጽግና ጽ/ቤት ኃላፊ

➡️ የወልዲያ ከተማ ማዘጋጃ ቤት ምክትል ኃላፊ ይገኙበታል።

መኖሪያ ቤታቸው ላይ ነበር ጥቃት የተፈጸመው።

ከዚህም ባለፈ የዞኑ አስተዳደር ጽህፈት ቤት ቅጥር ግቢም የጥቃት ኢላማ እንደነበር ነዋሪዎች ተናግረዋል።

" #ባልታወቁ_አካላት " ተፈጽሟል በተባሉት ጥቃቶች በባለስልጣናቱ ላይ ሳይሆን በሌሎች ሰዎች ላይ ቀላል ጉዳት መድረሱ እንዲሁም ንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ ተሰምቷል።

በቅርቡ የጉባ ላፍቶ ወረዳ አስተዳደር ጽህፈት ቤት እና በፖሊስ ጣቢያ ላይ ተመሳሳይ ጥቃቶች ተፈጽመው እንደነበር ተነግሯል።

ባለፈው #ሚያዚያ ወር የላስታ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ጌታቸው መልሴ እና የወረዳው የጤና ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሚሊዮን አፈወርቅ ከስብሰባ ሲመለሱ በተፈጸመባቸው ጥቃት መገደላቸው አይዘነጋም።

#TikvahEthiopia
#BBCAmharic

@tikvahethiopia
#Amhara

" እስኪበቃን ተገዳድለናል ፤ እስኪበቃን ተዋጋን አሁን ይብቃን !! መፍትሔው ንግግር ነው፣ መነጋገር ነው፣ መከባበር ነው " - አቶ አገኘሁ ተሻገር

በአማራ ክልል ያለው የትጥቅ ግጭት በውይይት እና በድርድር እንዲቋጭ መንግስት በድጋሚ ጥሪ አቀረበ።

ጥሪውን ያቀረበው በባህር ዳር ከተማ በተካሄደው የሰላም ኮንፈረንስ ነው።

የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አቶ አገኘሁ ተሻገር ምን አሉ ?

" ከጎንደር ወደ አዲስ አበባ መሄድ ቅንጦት ሆኗል፣ ከአዲስ አበባ ባሕር ዳር መምጣት ቅንጦት ሆኗል ያላቸው በአውሮፕላን ነው የሚሄዱ፣ የእኔና የእናንተ ቤተሰቦች በአውሮፕላን መሄድ አይችሉም።

ተማሪዎች ትምህርታቸውን መማር አልቻሉም ፣ በርካታ ተማሪዎች ለክልላዊ እና ለአገራዊ ፈተናዎች መቀመጥ አልቻሉም ፣ እየተማሩ ያሉ ተማሪዎች ተገቢ የሆነ ውጤት ለማምጣት እየተቸገሩ ነው፣ በርካታ ተማሪዎችም ትምህርታቸውን እያቋረጡ ነው።

መንግስት የልማት ስራዎችን መስራት አልቻልም።

በኢኮኖሚውም ዘርፍ የአማራ ክልል 35 ከመቶ እና ከዚያ በላይ የሚሆነውን የአገሪቱን የሰብል ምርት የሚሸፍን ሆኖ ሳለ ፣ ዛሬ ማምረት እንኳ አልቻለም ፣ ማዳበሪያ ማሰራጨት አልቻለም ፣ ምርጥ ዘር ማሰራጨት አልቻልም ፣ የአበዳሪ ተቋማት ብድር መሰብሰብ አልቻሉም ፣ ባንኮች አገልግሎት መስጠት አልቻሉም ፣ ነጋዴው ሰርቶ ፣ ነግዶ ራሱን ማሻሻል አልቻለም፡፡

ህዝባችን የከፋ ችግር ውስጥ ነው ያለው አይናገርም ቢናገር ችግር ይደርስበታል።

መገዳደሉና ፣ በጠላትነት መፈላለጉ ከበቂ በላይ ነው። ይሄን መገዳደል ካላስቆምን በስተቀር ክልላችን ወደፊት መራመድ / ፈቀቅ እንኳን ማለት አይችልም።

በቃ !! እስኪበቃን ተገዳድለናል፣ እስኪበቃን ተዋጋን ስለዚህ አሁን ይብቃን፣ መፍትሔው ንግግር ነው፣ መነጋገር ነው፣ መከባበር ነው።

ሌለው አካል ብቻ  ችግር ያለበት አድርጌ እኔ እራሴን ከችግር እያወጣው አይደለም፣ እኔ ችግር የለብኝም እያልሁም አይደለም፣ እኔም ሁላችንም የችግሩ አካል ነን፣ ስለዚህ ይብቃን፣ ህዝባችን ከችግር እናውጣው።

አሁንም መንግስታችን እና ፓርቲያችን የሰላም ጥሪ ያቀርባል፣ ለመነጋገር ፣ ለመወያየት ለመደራደር ፣ ለመመካከር የክልሉም ሆነ የፌደራሉ መንግስት ዝግጁ ነው። "

#Ethiopia
#AmharaRegion

@tikvahethiopia
#Amhara

ከሰሞኑን በአማራ ክልል፣ በባህርዳር ከተማ የተለያዩ የመንግሥት አካላት ፣ የሃይማኖት አባቶች ፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበት ከተካሄደ የሰላም ኮንፈረንስ በኃሏ ተቋቁሟል የተባለው ' አመቻች የሰላም ምክር ቤት ' በአማራ ክልል እየተደረገ ያለው የእርስ በእርስ ጦርነት ነው ብሏል።

ምክር ቤቱ በዚህ ጦርነት ፥ " ወንድም ከወንድሙ፣ ልጅም ከአባቱ ጋር ነው እየተገዳደለ ያለው " ሲል ገልጿል።

ለፌዴራል መንግሥት / ለአማራ ክልላዊ መንግሥት እና ለፋኖ ኃይሎች ሲል በስም ጠርቶ ባቀረበው የሰላም ጥሪ " የወገናችሁን ስቃይ ተረድታችሁ ምንም መሸናነፍ በማትችሉት ጦርነት ከመቆየት ሁለታችሁም ማሸነፍ ወደምትችሉት ንግግር እና ድርድር እንድትመጡ እንጠይቃለን " ብሏል።

ም/ ቤቱ መንግሥት እና የፋኖ ኃይሎች ወደ ሰላም መድረክ እንዲመጡ ለማመቻቸት እንደሚሰራ አመልክቷል።

" በአማራ ክልል ባለው ጦርነት ንጹሃን ይገደላሉ፣ በጠራራ ጸሃይ ያለ ከልካይ ይዘረፋሉ  " ያለው ምክር ቤቱ ከ12 እስከ 13 ቢሊዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን አመልክቷል።

መንግሥት ጦርነቱን በድርድር ለመቋጨት ፍቃደኛ እንደሆነ ገልጾ " ብዙ መሪ እና አደረጃጀት ያላቸው የፋኖ ታጣቂዎች ለመደራደር ወደ አንድ መምጣት አለባቸው በማለቱ ይህ የሰላምና ድርድር አመቻች ምክር ቤት መቋቋሙ ተነግሯል።

ምክር ቤቱ 15 አባላት ያሉት ነው።

በሌላ በኩል ፥ ከሰሞኑን በርካታ ሰዎች በክልሉ መገደላቸው ተሰምቷል።

በሰሜን ጎንደር ዞን ፤ በዳባት ወረዳ፣ በመንግስት የጸጥታ አካላት እና ፋኖ ኃይሎች መካከል በተደረገ የተኩስ ልውውጥ የፓሊስ አባላት መገደላቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸዋል።

ሁነቱን በቅርበት ሲከታተሉ የነበሩ ነዋሪ ፤ " ከተማው ውስጥ አሁንም ሀዘን/ልቅሶ አለ " ሲሉ ተናግረዋል።

" ሀዘኑ የተፈጠረው በአካባቢው ላይ ከ ‘ ፋኖ ’ ጋር በነበረ ውጊያ በርካታ የአካባቢው የጸጥታ አባላት ስለተገደሉ መሆኑን አረጋግጫለሁ " ብለዋል።

የሟቾች ቁጥር ምን ያህል ነው ? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ " የሟቾች ቁጥር ከ115 በላይ ነው " የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ሟቾቹን በተመለከተም አድማ ብተና ሚሊሻና ፖሊስ እንደሆኑ ገልጸዋል።

ቃላቸውን የሰጡ ሌሎች ነዋሪዎች የሟቾች ቁጥር እስከ 130 እንደሚደርስ ንጹሐን እንደቆሰሉ ገልጸው ሰሞኑን ከተማዋ ከባድ ሀዘን እንዳስተናገደች ተናግረዋል።

ስለግድያው ምላሽ የጠየቅነው የዳባት ወረዳ ከንቲባ ጽ/ቤት፣ ጉዳዩን በጽሞና ከሰማ በኋላ ማብራሪያ ለመስጠት ፍቃደኛ አልሆነም።

በዚሁ ባሳለፍነው ሳምንትም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቃላቸውን ባአዊ ዞን የቲሊሊ ወረዳ ነዋሪዎች ደግሞ የመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች 3 ሰዎችን ከቲሊሊ ሆቴል አውጥተው ገድለዋል ሲሉ ከሰዋል።

ሌሎች 2 ሰዎችም ተገድለዋል። በድምሩ 5 ንጹሐን በቲሊሊ ወረዳ መገደላቸውን ተናግተዋል።

በቦታው የተኩስ ልውውጥ ተደርጎ ነበር እንዴ ? በሚል ለነዋሪዎቹ ለቀረበው ጥያቄ ምንም ተኩስ እንዳልነበር፣ ግማሾቹን መንገድ ላይ በሚጓዙበት፣ ሌሎቹን ደግሞ ከሆቴል አስወጥተው እንደገሏቸው አስረድተዋል።

የመንግስት አካላት ስለሁኔታው እንዲያብራሩልን ብንጠይቅም ፍቃደኛ አልሆኑም።

ከዚህ ባለፈም ፥ በሰሜን ሸዋ ዞን ጣርማ በር ወረዳ ከደብረ ሲና ከተማ ወጣ ብላ በምትገኝ  " ሾላ  ሜዳ " በተባለች አነስተኛ የገጠር ከተማ ሰኔ 19 በመንግሥት ኃይሎች ደርሷል በተባለ ጥቃት ቢያንስ 15 ሰዎች መገደላቸውን እና 4 የሚሆኑ ሰዎች መቁሰላቸውን ነዋሪዎችን ዋቢ በማድረግ ቢቢሲ አማርኛው ዘግቧል።

በጥቃቱት ከአያቶቹ ጋር የሚኖር የ14 ዓመት ታዳጊ መገደሉን ፥ አንድ የአይን እማኝ ደግሞ አንድ ሻይ ቤት 11 ሰዎች መገደላቸውን በ20ዎቹ እድሜ የሚገኝ ወንድማቸው ተገድሎ ሜዳ ላይ እንዳገኙት ተናግረዋል።

ሌላ የአይን እማኝ የ11ዱ ሟቾችን ስም ዝርዝር መሰብሰብ እንደቻሉ ሰኔ 20 ቀን/2016 ዓ/ም 4 ተጨማሪ አስከሬን እንደተገኘ ገልጸዋል።

የጸጥታ ኃይሎቹ በአካባቢው ለለቅሶ መጥተዋል የተባሉ 3 የፋኖ ታጣቂዎችን ተከትለው ሳይመጡ እንዳልቀረና ስለ ታጣቂዎቹ መረጃ በመፈለግ ግድያውን እንደተፈጸመ አክለዋል።

በተመሳሳይ በሰሜን ጎጃም ዞን ፤ በይልማና ዴንሳ ወረዳ አዴት ከተማ ሰኞ ሰኔ 17 ቀን 11 ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ቃላቸውን የሰጡ ነዋሪዎች ፥ በእለቱ የፋኖ ታጣቂዎች እና የመንግሥት ኃይሎች ለሰዓታት የዘለቀ ከባድ ውጊያ ማድረጋቸውን ጠቁመዋል።

ይህን ተከትሎ ጥቃቱ መፈጸሙን አንድ ሴትና 10 ወንዶች እንደተገደሉ ገልጸዋል።

ግድያው የ ' ፋኖ ታጣቂዎች ' ከተማይቱን ለቀው መውጣታቸውን ተከትሎ 02 ቀበሌ እርሻ ሰብል በተባለ ሰፈር መንገድ ላይ እና ቤት ለቤት መፈጸሙን ገልጸዋል።

" ለፋኖ መረጃ ትሰጣላችሁ " በሚል ግድያው ተፈጽሟል ሲሉ ከሰዋል።

ፋኖ በከተማው ተቆጣጥሮ ውሎ በወጣበት ሰዓት የመንግስት ጸጥታ ኃይል ተመቶ እንደነበር ነዋሪዎች ተናግረዋል።

በተፈጠረው ክስተት ከተማዋ በከባድ ሀዘን ውስጥ መውደቋን ገልጸዋል።

በአማራ ክልል ፤ ያለው ጦርነት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን በተለያየ ጊዜ በተለያየ ቦታ እየተፈጠረ ባለው ግጭት የሰዎች ህይወት እየጠፋ ነው።

ከሰሞኑን የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ህዝቡ በሰላም እጦት የከፋ ችግር ላይ ወድቆ እንደሚገኝ ተናግረው ፥ መገዳደሉና ፣ በጠላትነት መፈላለጉ እንዲያበቃ ጥሪ አቅርበዋል።

አቶ አገኘሁ ተሻገር፥ " በቃ! እስኪበቃን ተገዳድለናል ፣ እስኪበቃን ተዋጋን ስለዚህ አሁን ላይ ይብቃን ፣ መፍትሔው ንግግር ነው ፣ መነጋገር ነው ፣ መከባበር ነው " ሲሉ ነበር የተናገሩት።

#Ethiopia
#AmharaRegion

@tikvahethiopia
#AmahraRegion

አቶ አህመድ አሊ ዛሬ በታጣቂዎች በተተኮሰባቸው ጥይት መገደላቸው ተሰማ።

በአማራ ክልላዊ መንግሥት ፣ የኦሮሞ ብሔረሰብ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ አህመድ አሊ ዛሬ በከሚሴ ከተማ ከሚገኝ መስጅድ ጁምአ ሶላት ሰግደው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ በታጣቂዎች በተተኮሰባቸው ጥይት መገደላቸው ተነግሯል።

የኦሮሞ ብሔረሰብ አስተዳደር ዞን ባወጣው የሀዘን መግለጫ " ግድያው የተፈጸመው በጽንፈኛው የሸኔ ታጣቂ ቡድን ነው " ብሏል።

አቶ አህመድ ከዋና አስተዳዳሪነታቸው በተጨማሪ የአማራ ክልል የብልጽግና ፓርቲ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባል በመሆን ማገልገላቸው ተገልጿል።

#AmharaRegion
#OromooZone

@tikvahethiopia
" ህዝቡ በጣም ተቸግሮ ነው ያለ ዛሬ ፣ ሰው ውሎ የማይገባበት ፤ ያሰበበት ደርሶ የማይመለስበት ነው " - ወንድማቸው የተገደለባቸው ነዋሪ

በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን መተማ ወረዳና አካባቢው ተባብሷል በተባለ የታጣቂ ኃይሎች እገታና ግድያ ነዋሪዎች ከፍተኛ ችግር ላይ መውደቃቸውን ለቪኦኤ ሬድዮ በሰጡት ቃል አመልክተዋል።

አቶ አወቀ ሰጠኝ የተቡ የህዝብ ማመላለሽ ሚኒባስ አሽከርካሪ የሆነው ወንድማቸው ባለፈው ሳምንት ረቡዕ ሰኔ 26 በስራ ላይ እያለ በታጣቂዎች ጥቃት መገደሉን አመልክተዋል።

በዕለቱ 18 ሰዎች አሳፍሮ ከጎንደር ተነስቶ መተማ እየተጓዘ ነበር።

' መቃ ' በተባለው ቦታ ላይ ነው ታጣቂዎች ጥይት ተኩሰው እሱን ጨምሮ 3 ሰዎች ሲገደሉ 14 ሰዎች ታግተው ወደ ጫካ ተወስደዋል።

ረዳቱ ሩጦ ማምለጡን አቶ አወቀ አስረድተዋል።

ሌላ ከኋላ የመጣ አንድ መኪናም ሰው ባይገደልም አስወርደው እንደሄዱ ጠቁመዋል።

" ሁል ጊዜ ግድያ፣ ሁል ጊዜ እገታ፣ ሞት በቃ በጣም የሚያሳዝን ነው ፤ ገላጋይ የሌለበት ሀገር ሆነናል " ሲሉ በሀዘም ስሜት ሆነው ተናግረዋል።

" ህዝቡ ተቸግሮ ነው ያለ ዛሬ ሰው ውሎ የማይገባበት ፤ ያሰበበት ደርሶ የማይመለስበት ፣ የሰው ህይወት የሚጨፈጨፍበት ሰዓትና ጊዜ ላይ ነው ያለን። ምንም የሚያድነን አላገኘንም፣ መንግስትም ሊያድነን አልቻለም " ብለዋል።

መተማ አጠቃላይ ሆስፒታል አስክሬን ክፍል ውስጥ ሰራተኛ የሆኑት  አቅልለው ገነቱ፥ ባለፈው ሳምንት በታጣቂዎች ተወስደው ከነበሩት መካከል እንደሆነ የተጠቆመ ማንነቱ ያልታወቀ ግለሰብ ቤተሰቡ ባለመቅረቡ ቀብሩ በማዘጋጃ ቤት መፈጸሙን ተናግረዋል።

አንድ ስሜ አይገለጽብኝ ያሉ የመተማ ወረዳ ነዋሪ ፥ በአካባቢው ግድያ እና እገታ ተባብሶ በመቀጠሉ ስራ ውሎ ወደ ቤት መግባት ፈታኝ እንደሆነ ገልጿል።

" እገታ ብቻ መበራከቱ ሳይሆን ሰዎችም ይገደላሉ " ያለው ይኸው ነዋሪ " የታገተ ሰው ብር የጠየቃል መክፈል የማይል አይመለስም " ሲል ተናግረዋል።

ከሰሞኑም ከመተማ ሆስፒታል አንድ አምፑላንስ ከነሹፌሩ መታገቱን ገልጿል። ለማስለቀቂያ 300 ሺህ መጠየቁን ተከትሎ በየመስሪያ ቤቱ እየተለመነ ነው ብሏል።

እገታ በመስፋፋቱ ነዋሪው፣ ሰራተኛው መንቀሳቀስ እንደቸገረው ጠቁሟል።

" በቃ ከቤት መስሪያ ቤት ከዛ ቤት እንጂ ከቤት መውጣት ከባድ ነው " ብሏል።

አንድ ከጎንደር መተማ የሚሰራ ሹፌር ደግሞ ፤ " ማንኛውም ሰው ወጥቶ ለመግባት ፣ ተንቀሳቅሶ ለመስራት ለመነገድም ሌላም የቀን ተቀን ስራ ለማከናወን በጣም ተቸግሯል። አስፈሪ ሁኔታ ነው ያለው። መንገዱ በጣም አስጊ ነው " ሲል ለሬድዮ ጣቢያው ተናግሯል።

#AmharaRegion
#VOAAmh.
#Metema

@tikvahethiopia
#Amhara #Bahirdar

በአማራ ክልል መዲና ባሕር ዳር ክልከላ ተጣለ።

ክልከላው የተጣለው በከተማው የጸጥታ ምክር ቤት ነው።

ከክልከላዎቹ ምንድናቸው ?

-  የቤት መኪና ፣ ታክሲ ፣ የመንግሥት መኪና ፣ ማንኛውም የጭነት መኪና ተሽከርካሪ ከምሽቱ 3 ሰዓት በኃላ እንዳይንቀሳቀሱ ክልከላ ተጥሏል። ከተፈቀደው ሰዓት እላፊ ሲያሽከረክሩ መገኘት በሕግ ያስቀጣል።

- ከምሽቱ 3 ሰዓት በኃላ ማንኛውም የሰው እንቅስቃሴ ተከልክሏል።

- ማንኛውም ተሽከርካሪ ታርጋ ሳይኖረው ወይም ሳያስር መንቀሣቀሥ አይችልም።

- ከተፈቀደላቸው ተሽከርካሪዎች ውጭ ስቲከር መለጠፍ ተከልክሏል።

-  ከዛሬ ጀምሮ ማንኛውም ባጃጅ መጋረጃ እና የግራ ጎን ሸራን ሳያነሱ ማሽከርከር ተከልክሏል።

- የባጃጅ ተሽከርካሪ ማኀበራት ከተሰጣችው የሥምሪት ቦታ ውጭ ማሽከርከር አይችሉም።

- በማኀበራት ተደራጅተው ስምሪት ከተሰጣቸው ባጃጆች ውጭ ማሽከርከር ተከልክሏል።

- የባጃጅ ተሸከርካሪዎች የባሕር ዳር አስተዳደር ትራንስፖርት ጽ/ቤት በአዲስ የሚሰጠውን መለያ ወይም ባር ኮድ ግልጽ እና በሚታይ መንገድ የመለጠፍ ግዴታ አለባችው።

- የባጃጅ ባለ ንብረቶች ለቀን ገቢ ወይም ለተለያዩ የጊዜ ገደብ ለሚያከራዮቸው ግለሰቦች የውል ስምምነት በመያዝ ለፓሊስ እና ትራንስፖርት ጽሕፈት ቤት ማሳወቅ አለባቸው።

- ባጃጆች ከምሽቱ 12 ሰዓት በኋላ እስከ ንጋቱ 12 ሰዓት ማሽከርከር ተከልክሏል።

- ባለ 2 እግር ሞተር ተሽከርካሪ ላልተወሰነ ጊዜ ማሽከርከር ተከልክሏል።

ክልከላው የማይመለከታቸው እነማንን ነው ?

ክልከላ የማይመለከታቸው ተሽከርካሪዎች ፦
° በጸጥታ ሥምሪት ላይ የሚገኙ፣
° አንቡላሶች፣
° የእሳት አደጋ መኪናዎች ናቸው። ነገር ግን በማንኛውም ሰዓት በአንቡላንስም ኾነ በሌሎች ተሽከርካሪዎች ላይ ፍተሻ ይደረጋል ተብሏል።

በሌላ በኩል ፤ ከጸጥታ መዋቅሩ አባላት እና ለጸጥታ ሥራ ተሰማርተው የመንቀሣቀሻ ፈቃድ ከተሰጣቸው ሰዎች ውጭ የጦር መሣሪያ ይዞ መንቀሣቀሥ ተከልክሏል።

ማንኛውም የጸጥታ አባል ከተሰጠው ስምሪት ውጭ በሚሆንበት ጊዜ ሲቪል ለብሶ የጦር መሣሪያ ይዞ መንሳቀስ እንዳይችል ክልከላ ተጥሏል።

#AmharaRegion

@tikvahethiopia