TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
' ቤቲንግ ' ሊታገድ ነው ?

ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያዎች ላይ " ቤቲንግ " ሊታገድ መሆኑን የሚገልፁ በትክክል ምንጫቸው ያልተገለፁ ፅሁፎች ሲሰራጩ ተስተውሏል።

ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ግን እየተሰራጩ ያሉት መልዕክቶች ፍፁም ስህተት ናቸው ብሏል በማህበራዊ ትስስር ገፁ ዛሬ ባወጣው ማሳሰቢያ።

" ' አንዳንድ ግለሰቦች በማህበራዊ ሚዲያ ቤቲንግ ሊዘጋ ነው ' በማለት የሚያሰራጩት መልእክት ፍጹም ስህተት መሆኑን እንገልፃለን " ያለው አስተዳደሩ " የስፖርት ውርርድ ጨዋታዎችም ሆነ  ሎተሪን   በተመለከተ ማንኛውም መረጃ ከብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ብቻ ማግኘት እንደሚገባ አመልክቷል።

ከዚህ ቀደም ከ ' ቤቲንግ / ስፖርታዊ ውርርድ / ' ጋር በተያያዘ ፤ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር #እንዲታገድ እየሰራ መሆኑን አሳውቆ እንደነበር ይታወሳል።

ሚኒስቴር መ/ቤቱ  ፤ ከታዲጊዎች እና ወጣቶች ስብዕና ግንባታ እንዲሁም በተለያየ መንገድ ከሚያስከትላቸው ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ቀውሶች አንጻር ነው ዘርፉ #ሊታገድ ይገባል በሚል እየሰራ እንደሆነ አሳውቆ የነበረው።

የስፖርት ውርርድ ' ቁማር ነው ' ብሎ የሚያምነው ይኸው የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት ፤ በተለያየ ጊዜ ሰርቻቸዋለሁ ባላቸው የዳሰሳ ጥናቶች ቤቲንግ ለወጣቱና ለታዳጊው ዘርፈ ብዙ አደጋ የደቀነ መሆኑን አመላካች መሆኑን ፤ ቁማር ታዳጊዎችን ይሁን አዋቂ ሰዎችን ወዳልተፈለገ መንገድ ሊወስድ የሚችል ማህበራዊ ቀውስ እንደሆነና ማንኛውም ሰው ሰርቶ የመለወጥ እሳቤውን የሚያቀጭጭ፣ ቤተሰብን ጭምር ወደ መበተን ሊያደርስ የሚችል ጉዳይ መሆኑን አስገንዝቦ ነበር።

ወጣቶች እና ታዲጊዎች ለቤቲንግ ውርርድ ሲሉ ያላቸውን ነገር በሙሉ እስከማውጣት ይደርሳሉ ፤ ወጣቶች ስራን ከመስራት ይልቅ በአቋራጭ መክበር እንዲያስቡ በማድረግ ምርት እና ምርታማነትን የሚቀንስ ተግባር ነው የሚልው መ/ቤቱ ቤቲንግ እንዲታገድ ፍቃድ ለሚሰጡት የንግድ ሚኒስቴር እና የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ተቋማት አስፈላጊውን የግንዛቤ እና የማሳወቅ ስራ ቢሰራም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ባለማድረጋቸው ለውሳኔው መዘግየት ዋነኛ ምክንያት መሆኑን ገልጾ ነበር።

የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ቤቲንግ እንዲታገድ ብርቱ እንቅስቃሴ ማድረግ መጀመሩን ካሳወቀ ወራት ቢቆጠርም እስካሁን በጉዳዩ ላይ አዲስ ነገር የለም።

የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ግን በ ' ቤቲንግ ' ኮሚሽን (15%) በሚሊዮን የሚቆጠር ብር ያስገኛል (ለሀገር) ፣ በርካታ ሰው በተለይ ሴቶችን ቀጥሯል ፣ ለማህበራዊ ጉዳይ ከገቢው ያውላል ፣ ቤት ይከራያል ፣ ገንዘብ ኢኮኖሚ ውስጥ እንዲንቀሳቀስ ያደርጋል ... ይህ ሁሉ ጥቅሞቹ ናቸው ብሎ ያምናል።

" ቤቲንግ " አትራፊ እንደሆነ የሚገልጸው አስተዳደሩ " ጨዋታ " እንጂ " ቁማር " አይደለም ብሎ ያምናል። በስርዓት እንዲመራም መመሪያዎችን አውጥቶ እየሰራ እንደሆነና " እኛ ጨዋታውን አቅርበናል ፤ ተጫዋቹ ደግሞ በኃላፊነት መጫወት አለበት " ባይ ነው።

ማህበራዊ ቀውስ ያመጣ እንደሆነ ኃላፊነት ያለባቸው አካላት አጥንተው ከጉዳቱ ጥቅሙ ያመዝናል በሚል ከሚታገድ በህግ እንዲመራና የማይገባቸው ሰዎች እንዳይጫወቱ ክትትል  ቢደረግ የተሻለ መሆኑ ታምኖበት እየተሰራ እንደሆነ በከወራት በፊት ገልጿል።

ከሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ ላይ " ከጥር 3 ጀምሮ ቤቲንግ ይታገዳል " የሚሉ ምንጫቸው ያልተረጋገጠ መረጃዎች በስፋት ሲሰራጩ የነበረ ሲሆን የብሔራዊ ሎተሪ አስተዳደር ይህ ፍፁም የተሳሳተ ነው ፤ ማንኛውም ቤቲንግ / የስፖርት ውርርድ ነክ መረጃ የሚገኘው ከኔው ነው እንጂ ከሌላ አይደለም ሲል አስገንዝቧል።

#ቲክቫህኢትዮጵያ

@tikvahethiopia
ቀላል የመክፈያ ዘዴ ከቴሌብር !

በቴሌብር ሱፐርአፕ ወይም *127# ግብይት ሲፈፅሙ ከአገልግሎት አቅራቢዎች/ነጋዴዎች በሚደርስዎ የክፍያ መጠየቂያ መልዕክት መሠረት የተጠየቁትን የክፍያ መጠን እና የጠያቂውን ማንነት አረጋግጠው የሚስጥር ቁጥርዎን ብቻ በማስገባት ክፍያዎን መፈጸም ይችላሉ፡፡

ቴሌብር - ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!

#Ethiotelecom #telebirr #RealizingDigitalEthiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ጊዳሚ በምዕራብ ኦሮሚያ ቄለም ወለጋ ዞን ጊዳሚ ወረዳ ጊዳሚ ከተማ ውስጥ በሚገኘው የመካነ ኢየሱስ ቤተ-ክርስቲያን ጸሎት ላይ የነበሩ ዘጠኝ ሰዎች ተወስደው ተገድለዋል። ድርጊቱ የተፈፀመው አርብ ኅዳር 14/2016 ዓ.ም. ሌሊት 8 ሰዓት አካባቢ ነው። የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የወንጌል እና ቲዎሎጂ ክፍል ኃላፊ የሆኑት ዶ/ር ለሊሳ ዳንዴል ምን አሉ ? (ለቢቢሲ አፋን ኦሮሞ…
" ቤተክርስቲያን ለፍትህ ድምጿን  ስታሰማ ብትቆይም ምላሽ የተሰጠበት አንድም ጊዜ አልነበረም " - መካነ ኢየሱስ

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ፤ በኦሮሚያ ክልል ቄሌም ወለጋ ዞን፤ በጊዳሚ ወረዳ በአባላቶቿ ላይ የደረሰውን ግድያ አስመልከቶ  ዛሬ መግለጫ አውጥታለች።

በመግለጫዋ ፤ በኦሮሚያ ክልል፣ በቄለም ወለጋ ዞን፣ ጊዳሚ ወረዳ፤ መነ ሃሞ በመባል በሚታወቀው ቀበሌ " ቶኩማ መነ ሃሞ " በተሰኘ የመካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን ህዳር 14 ቀን 2016 ዓ.ም. ከሌሊቱ 8፡00 ሰዓት ላይ በቤተ ክርስቲያን በጸሎት ላይ  ከነበሩት 17 ሰዎች መካከል ማንነታቸው ተጣርቶ ባልታወቁ ታጣቂዎች 9 የቤተ ክርስቲያኒቱ አባላት ላይ የጅምላ ግድያ መፈጸሙ በሚዲያዎች መግለፁን ጠቁማለች።

ቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳዩን በሚመለከት መረጃዎችን ለማግኘት የሚቻላትን ሁሉ ስታደርግ የነበረ ቢሆንም፤ መንግስትም ባለው ሃላፊነት መሠረት ሁኔታውን አጣርቶ ለህዝብ ይፋ ያደርጋል በሚል ተስፋ እስካሁን ዝምታን መርጣ መቆየቷን ገልጻለች።

ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ የተገደሉት ሰዎች ከፖለቲካ ጋር ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌላቸው ንጹሐን ዜጎች መሆናቸውን የገለፀው ቤተ ክርስቲያኒቱ ድርጊቱን በጽኑ አውህዛ ፤ ኃዘንዋን ገልጻለች።

የዚህ እኩይ ተግባር ሰለባ የሆኑ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባላት፡-

1. ተሊላ ላሜሳ ታሲሳ
2. ቶሊና ላሜሳ ታሲሳ
3. ታምራት ላሜሳ ታሲሳ
4. ቀበና ቡልቻ ጉተማ
5. ጌታቸው ቤከታ ታይሳ
6. ሂካ አያና ያደሳ
7. ጅረኛ ድንገታ ቴሶ
8. ሰለሞን ድንገታ ቴሶ
9. ሲራጅ ደኑ መሆናቸውንና ሁላቸውም በወጣትነት ዕድሜ ክልል ውስጥ የነበሩ እንደሆኑ ገልጻለች።

አምስቱ ከሁለት ቤተሰቦች የሆኑ ወንድማማች ሲሆኑ ከዘጠኙ አራቱ የቤተሰብ ኃላፊዎች ናቸው ብላለች።

ቤተክርስቲያኒቱ በጊዳሚ የተከሰተው ይህ በግፍ መገደል በዓይነቱ የመጀመሪያ እንዳልሆነ ገልጻለች።

ከዚህም በፊት በተለያዩ ቦታዎች፤ ለምሳሌ፦

- ባለፈው ዓመት በምስራቅ ወለጋ በሳሲጋ ወረዳ 15 የቤተ ክርስቲያኒቱ ምዕመናን በዕሁድ የአምልኮ አገልግሎት ላይ እያሉ ማንነታቸው ባልታወቀ ታጣቂዎች በጅምላ ተገድለዋል።

- በምዕራብ ወለጋ ዞን በቦጂ ወረዳ በዕሁድ አምልኮ ላይ የነበሩ ሶስት ወጣቶች በታጣቂዎች ተገድለዋል።

በሌሎች የአገሪቱ አካባቢዎች በምእመናን ላይ ተመሳሳይ ድርጊቶች እየተከሰቱ መሆኑን ጠቅሳለች።

ለነዚህ ሁሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ለፍትህ ድምጽዋን ስታሰማ ብትቆይም ምላሽ የተሰጠበት አንድም ጊዜ አንዳልነበር አስረድታለች።

ቤተ ክርስቲያኒቱ በማንኛውም ደረጃ የሚገኙ የፌደራል መንግስትና የክልል ህግ አውጪ፣ ህግ አስፈጻሚ እና የዳኝነት አካላት ብርቱ ክትትል በማድረግ ህዳር 14/2016 ዓ/ም እና ከዚያም በፊት ላይ የተፈጸመውን በደል እንዲጣራና አጥፊዎቹ ወደ ህግ እንዲቀርቡ ያደርጉ ዘንድ መንግስትን ዳግመኛ አበክራ ጠይቃለች።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#እንድታውቁት የነዳጅ ዋጋ ባለበት ይቀጥላል። ከጥቅምት 28 ቀን 2016 ዓ.ም  ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ቀደም ሲል በስራ ላይ በነበረበት ዋጋ እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል። ቀደም ሲል የነበረው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ስንት ነው ? - ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም - ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም - ኬሮሲን በሊትር…
#እንድታውቁት

የታህሳስ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ #ባለበት ይቀጥላል ተብሏል።

የሁሉም የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከኅዳር 26 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ ባለበት እንደሚቀጥል የንግድ እና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።

ቀደም ሲል የነበረው የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ስንት ነው ?

- ቤንዚን በሊትር 77 ብር ከ65 ሳንቲም
- ነጭ ናፍጣ በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ኬሮሲን በሊትር 79 ብር ከ75 ሳንቲም
- ቀላል ጥቁር ናፍጣ በሊትር 62 ብር ከ36 ሳንቲም
- ከባድ ጥቁር ናፍጣ በሊትር 61 ብር ከ16 ሳንቲም ነው።

@tikvahethiopia
#ኮሬ #ዳርባማናና

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኮሬ ዞን ዳርባ ማናና ወረዳ 2 ወጣቶች መገደላቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከአከባቢው ነዋሪዎች ለማወቅ ችሏል።

አንድ ስሜ አይጠቀስ ያሉ የቀድሞ አማሮ ልዩ ወረዳ ባለሥልጣን ደግሞ ፤ ወጣቶቹ የተገደሉት ሲጠፉ የነበሩ መከላከያ ሠራዊትን ለማስመለጥ ሞክራችኋል ተብለው እንደሆነ ተናግረዋል።

በመንግስት የፀጥታ ኃይል የተገደለው አንደኛው ወጣት ሳሙኤል ሰለሞን እንደሚባልና ይኸው ወጣት ቀጥታ ሞተር ሳይክል ላይ እንደነበር ተመቶ እንደተገደለ ገልጸዋል።

ሌላኛው አቡለ ጸጋዬ የተባለ ወጣት ጉጂ ቦሬ ወደ ተባለ ካምፕ ከተወሰደ ከቀናት በኃላ ስቃይ ተፈፅሞበት መገደሉን ገልጸዋል።

ቃላቸውን የሰጡ አንድ የአካባቢው ነዋሪ  በበኩላቸው ፦

* ከመከላከያ ሲኮበልሉ የነበሩ አባሎችን ሲፈልጉ የነበሩ የመንግሥት ሠራዊቶች ሁለት በሞተር ሲጓዙ የነበሩ ወጣቶችን ኮሬ ዞን ሸሮ ቀበሌ ሙራ ማንቻ የሚባል ቦታ ምሽት አራት ሰዓት ላይ እንዳገኟቸው ገልጸዋል።

* አንዱ ከጸጥታ ኃይሎቹ በተተኮሰ ጥይት ወዲያው እንደሞተ ፣ ሌላኛውን ደግሞ ለማምለጥ ሲሞክር ይዘውት ወደ ሌላ ቦታ ወስደውት እንደነበር ፤ በኃላም እሁድ 7 ሰዓት ላይ እንደተረሸነ መስማታቸውን ተናግረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተፈጸመ ስለተባለው ግድያ ምን ምላሽ እንዳላቸው የኮሬ ዞን ምክትል ፖሊስ አዛዥ አቶ ሲዳሞ ማደቦን ጠይቋል።

ምክትል ፖሊስ አዛዡ  ፤ " በዚህ ነገር ላይ እኔ መግለጫ መስጠት አልችልም፣ ምክንያቱም ወጣቶች በሆነውም ባልሆነውም ቅሬታ ሊያቀርቡ ይችላሉ። መንግሥት እንደ መንግሥት እርምጃ ሊወስድ ይችላል " ብለዋል።

አክለውም፣ " የምሰጠው ነገር ከሕግ ጋር ሊጋጭ ስለሚችል ተነጋግረን ነው መረጃ የምንሰጠው " ሲሉ አክለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተመሳሳይ ጥያቄ ለዞኑ ፓሊስ አዛዥ ኢንስፔክተር አራርሶ ነጋሽ አቅርቧል።

ሁለት ወጣቶች በጸጥታ ኃይል ለምን እንደተገደሉ ሲጠየቁ ከአሥር ደቂቃ በኋላ እንዲደወል ቀጠሮ ቢሰጡም በቀጠሮው ሰዓት በድጋሚ ሲደወል ስልክ ለማንሳት ፈቃደኛ አልሆኑም።

በተጨማሪ፦ " እባክዎ ስልክዎን ያንሱና ምላሽ በመስጠት ኃላፊነትዎን ይወጡ። የወከሉት ሕዝብ በመንግሥት የጸጥታ ኃይሎች እየተተኮሰበት እየተገደለ እንደሆነ እየገለፀልን ነው ፤ በዚህ ጉዳይም ከ10 ደቂቃ በኋላ ደውሉ ብለው ነበር " ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለተላከላቸው የጽሑፍ መልዕክትም ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም።

ከዚህ ባለፈ ፦

- የኮሬ ዞን ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ብሩክ አየለ ስልክ ባላማንሳታቸው፣

- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ ወገኔ ብዙነህ "ስብሰባ ላይ ነኝ" በማለታቸውና በድጋሚ ሲድልወልም ስልክ ባለማንሳታቸው ምላሻቸውን ለማካተት አልቻልንም።

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) የክልሉ ቅርንጫፍ በበኩሉ፣ ስለሁለቱ ወጣቶች እስካሁን መረጃ ባይደርሰውም በዞኑ ባለው የጸጥታ ችግር ነዋሪዎች እየተደበደቡ መሆኑን ከዚህ በፊትም እንደተከታተለ አስረድቷል።

ዘገባው በአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ ተዘጋጅቶ የቀረበ ነው።

@tikvahethiopia
ፎቶ፦ የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እና የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ እውቅናና ሽልማት ተበረከተላቸው።

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ዛሬ  ፤ ' ቀጣይ ምዕራፍ ለሁለንተናዊ ለውጥ! ' በሚል መሪ ቃል የምስጋናና የሰላም ኮንፈረንስ በሚሊኒየም አዳራሽ አካሂዶ ነበር።

በዚህም ወቅት ፤ " ከለውጡ ወዲህ ለተገኘው ፍትሃዊ አገልግሎት እና ለሙስሊሙ ህብረተሰብ ጥያቄ ለሰጡት ምላሽ " በሚል ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አሕመድ እና ለከንቲባ አዳነች አቤቤ የእውቅና ሽልማት አበርክቷል።

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በስፍራው ተገኝተው ሽልማታቸውን ተረክበዋል።

በምን ጉዳይ ምላሽ ተሰጠ ተባለ ?

በመድረኩ ላይ ፦

- የህዝበ ሙስሊሙ መሪ ተቋም የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ፅ/ቤት ህጋዊ እውቅና ያለው ተቋም ሆኖ እንዲመሰረትና ተቋማዊ አደረጃጀቱ እንዲሻሻል መደረጉ።

- በሸሪያ ህግ የሚመሩ ወለድ አልባ ባንኮች እንዲመሰረቱ መደረጉ።

- በአዲስ አበባ ለህዝበ ሙስሊሙ ለማህበራዊ አገልግሎት የሚውሉ የቦታ ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ በመመለሳቸው የሚሉት ተነስተዋል።

በሌላ በኩል፤ በታላቁ አሊም ሀጅ ሙሃመድ ሳኒ ሀቢብ ስም ማእከል ሊገነባ መሆኑ ተገልጿል።

የማዕከሉ ግንባታ በለሚ ኮራ ክፍለ ከተማ በአራት ሺ ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፍ ይሆናል። ማእከሉን በሃላፊነት እንዲያስገነቡ የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼይኽ ሱልጧን ሀጅ አማን ለኢትዮጵያ  እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼይኽ ሀጅ ኢብራሂም አስረክበዋል።

ፎቶ ፦ የአዲስ አበባ ኮሚኒኬሽን ቢሮ

@tikvahethiopia
#Tigray

አቶ ጌታቸው ረዳ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ሳይመለሱ ሪፈረንደም አይታሰብም አሉ።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ፦

- የትግራይ ግዛቶችን በወረራ የያዙ ኃይሎች ሳይወጡ፤

- ተፈናቃዮች ወደ ቀደመው ቄያቸው ሳይመለሱ ሪፈረንደም የሚባል ነገር #አይታሰብም ሲሉ ተናግረዋል።

አቶ ጌታቸው ይህንን ያሉት በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ሚስተር ኤርቪን ጆዜ ማሲንጋ ከተመራ የልኡክ ቡድን ጋር ውይይት ባደረጉበት ወቅት ነው።

በውይይቱ ላይ የአሜሪካ መንግስትና ህዝብ የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እንዲፈረም ላደረጉት አስተዋፅኦ ምስጋና አቅርበዋል።

አቶ ጌታቸው ፤ ከልኡካን ቡድኑ ጋር አህጉርና ዓለም አቀፍ እንዲሁም አከባቢያዊ የፀጥታ ጉዳዮችና በክልሉ ስላጋጠመው ድርቅ አንስተው መወያየታቸው ታውቋል።

የትግራይ ግዛታዊ አንድነት በህገ መንግስቱ መሰረተ ከጦርነቱ በፊት ወደ ነበረበት መመለስ አለበትም ብለዋል። 

" የኤርትራ እና የአማራ ሃይሎች በወረራ ከያዙት የትግራይ ግዛት ሳይወጡ፤ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው መመለስ ለሌላ ስቃይ መዳረግ ነው " ያሉት አቶ ጌታቸው " የሪፈረንደም ጉዳይ መነሳት ካለበት በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሰረት በሃይል የተያዘው መሬት ተለቆ ተፈናቃዮች ወደ ቄያቸው ተመልሰው በምርጫ ህጋዊ መንግስት ከተቋቋመ በኃላ ነው " ብለዋል።   

ከቄየው የተፈናቀለው ህዝብ በቂ የእርዳታ አቅርቦት የማያገኝ በተለይ በአሁኑ ሰዓት በክልሉ የተከሰተው ድርቅ ተጨምሮበት ኑሮው እጅግ አስከፊና ውስብስብ አድርጎታል በማለት የገለፁት አቶ ጌታቸው የአሜሪካ ህዝብና መንግስት የጉዳዩ አሳሳቢነት በመገንዘብ ድጋፉን እንዲያጠናክር ጠይቀዋል። 

አምባሳደር ኤርቪን ጆዜ ማሲንጋ ምን አሉ ?

- የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በጥብቅ እንደሚከታተሉት ገልጸዋል።
- መንግስታቸው ለስምምነቱ ተግባራዊነትና የትግራይ መልሶ ማልማትን እንደሚደግፍና እንደሚሰራ ቃል ገብተዋል።

መረጃውን የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕረዚደንት ፅህፈት ቤት መግለጫን ዋቢ በማድረግ የላከው የመቐለ የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
" የባህል ህክምና እንሰጣለን የሚሉ አጭበርባሪ ግለሰቦች እየተበራከቱ ነው " - የአ/አ ባህል መድኃኒት አዋቂዎች ማህበር

የአዲስ አበባ ባህል መድኃኒት አዋቂዎች ማህበር ፤ የባህል ህክምና እንሰጣለን የሚሉ አጭበርባሪ ግለሰቦች እየተበራከቱ ነው ብሏል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እንደ ፌስ ቡክ እና ቴሌግራም ያሉ ማኅበራዊ መገናኛዎችን በመጠቀም " የባህል መድሃኒት አዋቂዎች ነን " የሚሉ እየተበራከቱ መጥተዋል፡፡

እነዚህ መድሃኒት አዋቂ ነን የሚሉ ሰዎች መድሃኒት እናዘጋጅላቸዋለን የሚሏቸው ጉዳዮች ያልተለመዱና " መድሃኒት " ይፈታቸዋል የማይባሉ ዓይነት ናቸው፡፡

ለምሳሌ ፦
- ለገበያ፣
- ለስልጣን፣
- ለግርማ ሞገስ፣
- ትዳር እምቢ ላለው፣
- ወደ ውጭ ለሚጓዝ፣
- ሎተሪ እንዲደርሳችሁ
- ለቤቲንግ
- ለእቁብ
- ለድምፅ ወዘተ.  የሚሉ አጓጊ ቃላትን ይጠቀማሉ ተብሏል።

መድሃኒት አዋቂ ነን ከሚሉት ሰዎች " መርጌታ " የሚል መንፈሳዊ ማዕረግን የሚጠቀሙት ብዙዎቹ ሲሆኑ በመቶ ሽዎች ተከታዮች ባሏቸው የማኅበራዊ መገናኛዎች ላይ ስልክ ቁጥሮቻቸውን ከመለጠፍ ባለፈ የሥራ አድራሻቸውን በግልጽ አያስቀምጡም ተብሏል።

ስልክ ሲደወልላቸው " ምን መድሃኒት ትልጋለህ ? " ብለው ይጠይቁና ለማንኛውም ዓይነት ችግር መፍትሔ እንዳላቸው ይናገራሉ ፤ ባለጉዳዩ ክፍያ #በባንክ እንዲያስገባ መድሃኒቱንም በመልክተኛ እንደሚልኩ ይገልጻሉ።

በዚህ መልኩ በርካታ ማጭበርበሮች የደረሰባቸው ሰዎች ስለመኖራቸው ተነግሯል።

ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ የአዲስ አበባ የባህል መድሃኒት አዋቂዎች ማህበር ፕሬዝዳንት መሪጌታ መንግሥቱ ፤ እንዲህ ያለ ሥራ የሚሠሩ አጭበርባሪዎች መበራከታቸውን ጠቁመዋል፡፡

" በራሴ ሥም መርጌታ መንግስቱ የባህል መድሃኒት አዋቂ " የሚል ገጽ ተከፍቶ ሰዎች እየተጭበረበሩ ነው ብለዋል፡፡

ከመንግስት ጋር እየተነጋገርን እነዚህን አጭበርባሪዎች ለማስታገስ እየሞከርን ነውም ሲሉ ተናግረዋል።

እነዚህ " መድሃኒት " አዋቂ ነን ብለው የሚያስተዋውቁ ሰዎች እንፈውሳቸዋለን የሚሏቸው በግልጽ መድሃኒት እንደሌላቸው የተነገረላቸው በሽታዎች ለምሳሌ ፦ ኤች አይ ቪ. እና ካንሰር ... ወዘተ. እንዲሁም እንደ በሽታ ሊታዩ የማይችሉ ወይም በሽታ ስለመሆናቸው ያልተረጋገጡ ለሆኑ ነገሮች ለምሳሌ ፦
* ራዕይ ለማዬት፣
* ሌሊት ሽንቱ ለሚያመልጠው፣
* ለወር አበባ፣
* ለንቃተ ህሊና፣
* ትምህርት ለማይገባው፣
* ለሥራ ዕድል፣
* ለመስተፋቅር ወዘተ. የሚሉ አሉ፡፡ ህክምና ፈላጊዎች እንዲህ መሰል በሆኑ አጭበርባሪዎች እንዳይታለሉ ሲሉ መሪጌታ መንግሥቱ (የአ/አ የባህል መድሃኒት አዋቂዎች ማህበር ፕሬዝዳንት) ተናግረዋል።

ይህ መረጃ #ባለቤትነቱ የኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬድዮ ' እውነትን ፍለጋ ' የተሰኘ ፕሮግራም / ደሳለኝ ስዩም ነው።

@tikvahethiopia