TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
" የባህል ህክምና እንሰጣለን የሚሉ አጭበርባሪ ግለሰቦች እየተበራከቱ ነው " - የአ/አ ባህል መድኃኒት አዋቂዎች ማህበር

የአዲስ አበባ ባህል መድኃኒት አዋቂዎች ማህበር ፤ የባህል ህክምና እንሰጣለን የሚሉ አጭበርባሪ ግለሰቦች እየተበራከቱ ነው ብሏል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እንደ ፌስ ቡክ እና ቴሌግራም ያሉ ማኅበራዊ መገናኛዎችን በመጠቀም " የባህል መድሃኒት አዋቂዎች ነን " የሚሉ እየተበራከቱ መጥተዋል፡፡

እነዚህ መድሃኒት አዋቂ ነን የሚሉ ሰዎች መድሃኒት እናዘጋጅላቸዋለን የሚሏቸው ጉዳዮች ያልተለመዱና " መድሃኒት " ይፈታቸዋል የማይባሉ ዓይነት ናቸው፡፡

ለምሳሌ ፦
- ለገበያ፣
- ለስልጣን፣
- ለግርማ ሞገስ፣
- ትዳር እምቢ ላለው፣
- ወደ ውጭ ለሚጓዝ፣
- ሎተሪ እንዲደርሳችሁ
- ለቤቲንግ
- ለእቁብ
- ለድምፅ ወዘተ.  የሚሉ አጓጊ ቃላትን ይጠቀማሉ ተብሏል።

መድሃኒት አዋቂ ነን ከሚሉት ሰዎች " መርጌታ " የሚል መንፈሳዊ ማዕረግን የሚጠቀሙት ብዙዎቹ ሲሆኑ በመቶ ሽዎች ተከታዮች ባሏቸው የማኅበራዊ መገናኛዎች ላይ ስልክ ቁጥሮቻቸውን ከመለጠፍ ባለፈ የሥራ አድራሻቸውን በግልጽ አያስቀምጡም ተብሏል።

ስልክ ሲደወልላቸው " ምን መድሃኒት ትልጋለህ ? " ብለው ይጠይቁና ለማንኛውም ዓይነት ችግር መፍትሔ እንዳላቸው ይናገራሉ ፤ ባለጉዳዩ ክፍያ #በባንክ እንዲያስገባ መድሃኒቱንም በመልክተኛ እንደሚልኩ ይገልጻሉ።

በዚህ መልኩ በርካታ ማጭበርበሮች የደረሰባቸው ሰዎች ስለመኖራቸው ተነግሯል።

ይህንን ጉዳይ አስመልክቶ የአዲስ አበባ የባህል መድሃኒት አዋቂዎች ማህበር ፕሬዝዳንት መሪጌታ መንግሥቱ ፤ እንዲህ ያለ ሥራ የሚሠሩ አጭበርባሪዎች መበራከታቸውን ጠቁመዋል፡፡

" በራሴ ሥም መርጌታ መንግስቱ የባህል መድሃኒት አዋቂ " የሚል ገጽ ተከፍቶ ሰዎች እየተጭበረበሩ ነው ብለዋል፡፡

ከመንግስት ጋር እየተነጋገርን እነዚህን አጭበርባሪዎች ለማስታገስ እየሞከርን ነውም ሲሉ ተናግረዋል።

እነዚህ " መድሃኒት " አዋቂ ነን ብለው የሚያስተዋውቁ ሰዎች እንፈውሳቸዋለን የሚሏቸው በግልጽ መድሃኒት እንደሌላቸው የተነገረላቸው በሽታዎች ለምሳሌ ፦ ኤች አይ ቪ. እና ካንሰር ... ወዘተ. እንዲሁም እንደ በሽታ ሊታዩ የማይችሉ ወይም በሽታ ስለመሆናቸው ያልተረጋገጡ ለሆኑ ነገሮች ለምሳሌ ፦
* ራዕይ ለማዬት፣
* ሌሊት ሽንቱ ለሚያመልጠው፣
* ለወር አበባ፣
* ለንቃተ ህሊና፣
* ትምህርት ለማይገባው፣
* ለሥራ ዕድል፣
* ለመስተፋቅር ወዘተ. የሚሉ አሉ፡፡ ህክምና ፈላጊዎች እንዲህ መሰል በሆኑ አጭበርባሪዎች እንዳይታለሉ ሲሉ መሪጌታ መንግሥቱ (የአ/አ የባህል መድሃኒት አዋቂዎች ማህበር ፕሬዝዳንት) ተናግረዋል።

ይህ መረጃ #ባለቤትነቱ የኤፍ ኤም አዲስ 97.1 ሬድዮ ' እውነትን ፍለጋ ' የተሰኘ ፕሮግራም / ደሳለኝ ስዩም ነው።

@tikvahethiopia
" በብዛት የምንቀጥረው የእኛ ልጆች የሥራ ዕድል እንዲያገኙ ከዩኒቨርስቲ የሚመጡ ግራጁየቶችን ነው " - የአንድ ባንክ ባለስልጣን

" ጉዳዩ የሚታወቅ ነው እኮ " - የኢትዮጵያ  ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋም

የሥራ ቅጥርን በተመለከተ በተለያዩ ተቋማት የሚደረግ ብሔር ተኮር፣ የዘመድ አዝማድና የሙስና ቅጦር ለምሬት እንደዳረጋቸው በርካቶች በተደጋጋሚ እሮሮ ሲያሰሙ ይደመጣሉ።

በተለይ #በባንክ_ቤቶች ይሄው ችግር በሰፊው እንደሚስተዋል መነገር ከጀመረም ሰንበትበት ያለ ቢሆንም ችግሩ መፍትሄ ስላልተቸረው አሁንም እንደቀጠለ ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረዳት ችሏል።

የአንድ ባንክ ባለሥጣን ባንኩ በዚህ ዓመት አዘጋጅቶት በነበረው የባለአክሲዮኖች ስብስባ የሠራተኛን የቅጥር ሁኔታን በተመለከተ በመርሀ ግብሩ ወቅት ከአንድ ባለአክሲዮን ለቀረበላቸው ጥያቄ ባደረጉት ገለጻ፣ " በብዛት የምንቀጥረው የእኛ ልጆች የሥራ ዕድል እንዲያገኙ ከዩኒቨርስቲ የሚመጡ ግራጁየቶችን ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።

ባለስልጣኑ እንዲህ ያሉት በባንኩ ሠራተኞች አገልግሎት አሰጣጥ ክፍተትን በተመለከተ ከአንድ የባንኩ ባለአክሲዮን የቀረበላቸውን ጥያቄን በተመለከተ ማብራሪያ በሰጡበት አውድ ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ፦
* በብሔር ተኮር ፣
* በሙስና የቅጥር አፈጻጸሞች ዙሪያ ከዜጎች የደረሱት ቅሬታዎች እንዳሉ፣ እንደ ተቋምም በዚሁ ረገድ የሕዝብን እንባ ለማበስ ጉዳዩን አይቶት (ተከታትሎት) እንደሆነ፣ የኢትዮጵያ  ሕዝብ ዕንባ ጠባቂ ተቋምን ጠይቋል።

አንድ የተቋሙ ከፍተኛ ባለሥልጣን በሰጡን ቃል፣ " ጉዳዩ የሚታይ እኮ አይደለም፣ የሚታወቅ ስለሆነ " ብለዋል።

ከዚህ በፊትም ከሥራ ቅጥር ጋር በተያያዘ በርካታ አቤቱታዎች ወደ ተቋሙ ይመጡ እንደነበር አስታውሰዋል።

" አቤቱታ በተናጠል ሊመጣ ይችላል " ያሉት የተቋሙ ባለስልጣን " ነገር ግን ማስረጃ ስለማይኖር፣ እከሌ በዘመድ ነው የተቀጠረው፣ ገንዘብ ሰጥቶ ነው የተቀጠረው የሚለውን ነገር ኢቪደንስ ስለማይኖር ሰውም አይመጣም " ብለዋል።

" ግን አጠቅላይ ስሩአውት ዘከንትሪ ያለው ትሬንድ ወይ ዘመድ ካለህ፣ ወይ ገንዘብ ካለህ ነው የምትቀጠረው በማስረጃ እንዲህ ነው ለማለት ግን ያስቸግራል " ነው ያሉት ባለሥልጣኑ።

የመፍትሄ አቅጣጫው ምን እንደሆነ ሲጠየቁም፣ " ሲቪል ሰርቪስ ወቅታዊ ሁኔታዎች ይዘውት እንጂ አጠቃላይ በዚህ የአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ተከታታይ የሆነ ሥራ እንደሚሰራ፣ እኛም ጠይቀናቸዋል " ብለዋል።

አክለውም፣ " ከዚህ ከአገልግሎቱ አሰጣጥ ጋር፣ ከመልካም አስተዳደር ጉዳይ፣ ከቅጥርም፣ ከእያንዳንዱ የሰው ኃይል ጋር ተያይዞ በቅጡ እየሄደ አይደለም የሚል ሀሳብ አንስተንላቸው እነርሱም ዝግጅት አጠናቀው 'በስድስት ወራት የምንሰራው ሥራ ነው' የሚል ሀሳብ አንስተዋል " ሲሉ አስረድተዋል።

ዘገባውን ያጠናቀረው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Asset Recovery draft proc. Amharic from COM to HPR (1).pdf
#ኢትዮጵያ

የንብረት ማስመለስ ረቂቅ አዋጅ ፤ " ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ስለማስመለስ " ምን ይላል ?

➡️ #ማንኛውም_ሰው በቀጥታ ሆነ #በተዘዋዋሪ ያለው ንብረት ወይም የኑሮ ደረጃው አሁን ላይ ባለበት ወይም አስቀድሞ በነበረበት ስራ ወይም በሌላ መንገድ ከሚያገኘው ወይም ሲያገኝ ከነበረው ህጋዊ ገቢ የማይመጣጠን እንደሆነ እና የንብረቱን ወይም የኑሮ ደረጃውን ምንጭ በተመለከተ ምክንያታዊ የሆነ የወንጀል ጥርጣሬ በኖረ ጊዜ የዚህ አይነቱ የኑሮ ደረጃ ወይም ያለው ንብረት እንዴት ሊኖረው እንደቻለ ለፍርድ ቤት ካላስረዳ በስተቀር ንብረቱ #ይወረሳል

➡️ ህጋዊ ገቢ እንዳለው የሚያስረዳ የተመዘገበበት ስርዓት የሌለው ወይም ገቢው እነስተኛ በመሆኑ #ከግብር_ነጻ የሆነ ሰው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያለው ንብረት ወይም የኑሮ ደረጃው ከሚያገኘው ወይም ሲያገኝ ከነበረው ህጋዊ ገቢ የማይመጣጠን እንደሆነ የዚህ አይነቱ የኑሮ ደረጃ ወይም ያለው ንብረት እንዴት ሊኖረው እንደቻለ ለፍርድ ቤት ካላስረዳ በስተቀር ንብረቱ ይወረሳል፡፡

➡️ " በቀጥታ ወይም በተዘዋዋሪ ያፈራው ንብረት " ማለት ፦

° በራሱ ስም የሚገኝ ንብረት፣

° በራሱ ስም ባይሆንም ለራሱ ጥቅም ሲያዝበት ወይም ሲቆጣጠረው የነበረው ንብረት ፣

° የተጠቀመው ወይም ደግሞ ያስወገደው ንብረት፣

° በሽያጭ ፣ በስጦታ ወይም በማንኛውም ሁኔታ #ያስተላለፈውን ንብረት ይጨምራል፡፡

➡️ ዐቃቤ ሕግ " #ምንጩ_ያልታወቀ_ነው " ብሎ የጠረጠረውን ማንኛውንም ንብረት ዝርዝር እና የተገኘበትን አግባብ የሚያሳይ መግለጫ እንዲያቀርብ በፅሁፍ ጥያቄ የቀረበለት ማንኛውም ሰው ጥያቄው በደረሰው በ1 ወር ጊዜ ውስጥ ለዐቃቤ ህግ ዝርዝር ማስረጃዎችን በማያያዝ በፅሁፍ ማቅረብ ይኖርበታል።

➡️ የንብረቱን ምንጭ እንዲያስረዳ የተጠየቀው ሰው የንብረቱን ምንጭ ለማስረዳት የሚያቀርበው ማስረጃ ሀጋዊ መሆን አለበት።

ተጨማሪ ....

☑️ አንድ ሕጋዊ ንግድ ፍቃድ አውጥቶ የሚሰራ ነጋዴ ወይም ድርጅት ሕጋዊ ገቢው ተብሎ የሚገመተው ለተገቢው ባለስልጣን በወሩ ወይም በአመቱ ከንግዱ ያገኘሁት ብሎ ያሳወቀው የገቢ መጠን ሲሆን ወይም ተገቢው ታክስ የተከፈለባቸው ገቢዎች ሆነው ሲገኙና የታክስ ደረሰኝ ሲቀርብ ሲሆን ከዚህ ውጪ ህጋዊ ታክስ ያልተከፈለባቸው ገቢዎች ከህጋዊ ገቢ ውጪ ያፈራው ምንጩ ያልታወቀ ሀብት ተብሎ ሊወሰን ይችላል።

☑️ ምንጩን ሲያስረዳ " ከውጪ የተላከለኝ ገንዘብ ነው " የሚል ማንኛውም ግለሰብ ገንዘቡ በሕጋዊ መንገድ #በባንክ_ሥርዓት ውስጥ ያለፉ ግብይቶች ወይም ክፍያዎች ስለመሆናቸው በተገቢው የባንክ ደረሰኝ አስደግፎ ማቅረብ የሚገባው ሲሆን ከዚህ ውጪ ያለው ግን እንደ ምንጩ ያልታወቀ ገቢ ተደርጎ ይቆጠራል።

በረቂቅ አዋጁ ላይ #ምንጩ_ያልታወቀ_ንብረት ክስ የሚቀርብበት ጊዜ እና የገንዘብ መጠን ተደንግጓል፡፡

በዚህም አዋጁ ወደኋላ 10 ዓመታት ተመልሶ የሚሠራ ሲሆን ይህንንም ለመክሰስ የ5 ሚሊዮን የገንዘብ ገደብ ተቀምጧል፡፡

ይህ የገንዘብ ገደብ የተቀመጠበት ዋነኛው ምክንያት በአሁኑ ወቅት ላይ በሀገሪቱ ያለውን የሰው ሃይል ፣ የመክሰስ አቅም እና የፋይናንስ አቅም ከግምት ውስጥ በማስገባት አነስተኛ የሃብት መጠን ያላቸውን ግለሰቦች በመተው ከፍተኛ ንብረት ያላቸውን ተጠያቂ ለማድረግ እንደሆነ ተብራርቷል።

ከዚህ በተጨማሪ ሕጉ ወደኋላ (10 ዓመታት) ተመልሶ እንደመስራቱ በሀገሪቱ #ኢኮኖሚ#ማሕበራዊ እና #የፋይናንስ_ሥርዓት ላይ ከፍተኛ የሆነ ተጽዕኖ ያደርሳሉ ተብሎ የሚገመቱትን ግለሰቦችና ሕጋዊ ሰውነት ያላቸው ድርጅቶችን ተጠያቂ ማድረግ የተሻለ አማራጭ ሆኖ በመገኘቱ እንደሆነ ተብራርቷል።

አዋጁ ሥራ ላይ ከዋለ በኋላ ምንጩ ያልታወቀ ንብረት ተጠያቂነት ያለምንም የገንዘብ መጠን ተፈጻሚ ይደረጋል።

ስለ ረቂቅ አዋጁ አጭር ማብራሪያ ⬇️
https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/88313

ረቂቅ አዋጁ⬇️
https://publielectoral.lat/tikvahethiopia/88314

@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM