TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Amhara

በአማራ ክልል ፤ በሰሜን ጎንደር ዞን በአድርቃይ ወረዳ በተፈጸመ ጥቃት 15 የሚሆኑ ሰዎች መገደላቸውን እና በርካታ ቤቶች መቃጠላቸውን ነዋሪዎች እና የአካባቢው አስተዳደር አሳውቀዋል።

ይህ አካባቢ የትግራይ እና አማራ ክልሎች አዋሳኝ ነው።

ነዋሪዎች ምን አሉ ?

- ባለፈው ማክሰኞ ግንቦት 27 ከንጋቱ በ11፡00 ሰዓት አሊጣራ ቀበሌ አንካቶ በተባለ ጎጥ የቡድን መሳሪያ #ከትግራይ_በኩል በመጡ የታጠቁ ኃይሎች ከባድ ጥቃት ተከፍቶ ነበር።

- ጥቃቱ ከንጋቱ 11፡00 ጀምሮ እስከ ጠዋት 2፡30 ገደማ ነበር የዘለቀው።

- አንድ የአካባቢው ነዋሪ ፥ " #በአንድ_ቤት 5 ነበርን፣ ከአምስታችን እኔ ነኝ በአጋጣሚ የተረፍኩት፤ ሌሎቹ ሞቱ። አሰልፈው ነው የተኮሱብን።...እኔንም ሞቷል ብለው ነው ትተውኝ የሄዱት። በፈጣሪ ፈቃድ ነው የተረፍኩት ፤ ጀርባዬን በጥይት ተመትቼ ሆስፒታል ነው ያለሁት " ብለዋል።

- ሌላ ነዋሪ ፤ " በጥቃቱ 15 ሠዎች መገደላቸውን በዐይኔ ተመልክቻለሁ። ሁለት የ16 እና የ19 ዓመት የእህት ልጆቼም ተገድለዋል። " ሲሉ ተናግረዋል።

- ሌላኛው ነዋሪ ፥ " በእሳት እና በጥይት 3 ታዳጊዎችን ጨምሮ የበርካታ ሰዎች ሕይወት አልፏል። ህጻናትን ጨምሮ 15 ሠዎች መገደላቸውን አይቻለሁ " ብለዋል።

- የአካባቢው #የሚሊሻ አባል ፤ " ከጥቃት ፈጻሚዎች ጋር የተኩስ ልውውጥ ነበር። አብሮኝ የነበረው ታናሽ ወንድሜ በጥቃቱ ተገድሏል። ቦምብ ጉዳት አድርሷል፤ ጥይቱ፤ መሳሪያውም ብዙ ስለሆነ፤ ድሽቃ፣ ስናይፐር፣ ብሬን አላቸው። በእርቀት እየተኮሱ ነው ጉዳት ያደረሱት " ብለዋል።

-  ታጣቂዎቹ አካባቢውን ለቀው ሲወጡ 3 ሰዎችን ወስደዋል። 500 ከብቶችን ዘርፈወል። ቤቶችም ተቃጥለዋል።

ወረዳው ምን አለ ?

ዋና አስታዳዳሪ አቶ ሚሊዮን ታደሰ ጥቃቱን የፈጸሙት በዋልድባ ገዳም በኩል አድርገው የገቡ የትግራይ ኃይሎች ናቸው ብለዋል።

ቀብራቸው መፈጸሙን #ማረጋገጥ የቻሉት የስምንት ሰዎች መሆናቸውን ተናግረዋል።

ከ8ቱ ሟቾች መካከል 6ቱ #ንጹሃን_ነዋሪዎች እንደሆኑ 2ቱ የአካባቢው ሚሊሻ አባላት እንደነበሩ ገልጸዋል።

ጥቃተ የፈጸሙት የትግራይ ኃይሎች ስለመሆናቸው በምን እንዳወቁ ተጠይቀው ፥ ነዋሪዎች በሚናገሩት ቋንቋ እንደለይዋቸውና በተለያዩ ጊዜያትም ትንኮሳዎችን ይፈጽሙ እንደነበር ገልጸዋል።

" የትግራይ ታጣቂዎች ናቸው። ከእነሱ ውጪ የሚመጣብን ሌላ እንደሌለ ነው የተረዳነው " ብለዋል።

" ቡድኑን የሚመራውን ግለሰብ ጭምር እናውቃለን ፤ የህወሓት ታጣቂዎች ናቸው " ሲሉ ተናግረዋል።

ቦታው ይገባኛል የሚነሳባቸውን አካባቢዎችን ለመያዝ " ስልታዊ " መሆኑን ተንተርሶ ጥቃቱ ሳይፈጸም አልቀረም ብለዋል።

" የማንነት ጉዳይ ሚነሳባቸውን አካባቢዎች በቁጥጥራቸው ስር ለማድረግ የግድ የእኛን አካባቢ ማጥቃት አለባቸው። በ2013ም የተመለከትነው ይህን ነው። ስለዚህ ይህን አካባቢ የመቁረጥ፤ ቆርጦ መሀል ላይ ያለን የመንግሥትን መዋቅር የማጥቃት ፍላጎት አለ " ሲሉ ተናግረዋል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምን ምላሽ ሰጠ ?

የትግራይ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ባልደረባ አቶ አማረ ኃይሌ ፤ የትግራይ ኃይሎች ጥቃት አልፈጸሙም ብለዋል።

" እስካሁን ድረስ ወደዚያ አካባቢ ያደረግነው ምንም እንቅስቃሴ የለም " ብለዋል።

" እኛ ያለንበት ቦታና አሁን እየተባለ ባለው ቦታ በጣም ሰፊ ርቀት ነው ያለው። በቀጥታ የሚዋሰን ቦታም አይደለም " በማለት ጥቃቱን እንዳላደረሱ ገልጸዋል።

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር " ያሉ ችግሮችን ግጭት አልባ በሆነ መንገድ ለመፍታት ነው የሚያስበው ወደ ግጭት የመግባት ሁኔታ የለንም " ብለዋል።

Credit - BBC AMHARIC

@tikvahethiopia