TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#DrYaredAgidew

ዶክተር ያሬድ አግደው ወደ ኢትዮጵያ መምጣታቸውና የኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ህክምና በሚሰጥበት ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ስራ መጀመራቸውን አሳውቀዋል። ዶክተሩ ለሁሉም መልካም ዕድል ተመኝተዋል!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#EkaKotebeHospital የኮሮና ቫይረስን በማከም ስራ ላይ ለተሰማሩ ሃኪሞችና ባለሙያዎች ከከፋ ዞን የአገር ሽማግሌዎች የማርና በግ ስጦታ ተበረከተላቸው። የከፋ ዞን አስተዳደርና የአገር ሽማግሌዎች በአዲስ አበባ ኤካ ኮተቤ አጠቃላይ ሆስፒታል ተገኝተው የኮሮናቫይረስን በማከም ስራ ለተጠመዱ ባለሙያዎች ግምቱ ከ100 ሺህ ብር በላይ የሆነ የማርና በግ ስጦታ ዛሬ አበርክተዋል። የከፋ ዞን የአገር…
#DrDerejeDuguma #DrYaredAgidew

የኤካ ኮተቤ አጠቃላይ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ዶክተር ያሬድ አግደው ከከፋ ዞን አባቶች፣ ወጣቶችና የዞኑ አስተዳደር ስለቀረበላቸው ስጦታና መልካም ምኞት ምስጋና አቅርበዋል።

"እኛም ለእናንተ መልዕክት አለን" ያሉት ዶክተር ያሬድ፤ ''ለእኛ ያላችሁን ፍቅርና አክብሮት ራሳችሁን ከወረርሽኙ በመጠበቅ ልታሳዩን ይገባል'' ብለዋል።

የጤና ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ድጉማ በበኩላቸው ''የከፋ ዞን የአገር ሽማግሌዎች ወረርሽኙን ለመከላከል ያደረጉት ድጋፍ ለሌሎችም አካባቢዎች አርዓያ የሚሆን ነው'' ብለዋል።

ከእነዚህ የከፋ ዞን ደግ አድራጊዎች በመማር በሌሎች ዞኖችና ወረዳዎች ያሉትም ወረርሽኙን ለመከላከል የሚያስችል የቁሳቁስ ድጋፍ እንዲያደርጉ ጠይቀዋል።

ኅብረተሰቡ የህክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ከማድረግም ባለፈ ራሱን ከአካላዊ ንክኪ በመጠበቅ የቫይረሱን ስርጭት ለመግታት የሚደረገውን ጥረት እንዲያግዝ ጥሪ አቅርበዋል።

#ENA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#DrYaredAgidew

ትላንት ምሽት ማህበራዊ ሚዲያ ላይ አንዲት እናት በኮሮና ቫይረስ (ኮቪድ-19) ምክንያት ህይወታቸው ማለፉ ከጤና ሚኒስቴር እና ከኤካ ኮተቤ ሆስፒታል እውቅና ውጭ ሲሰራጭ ነበር።

በፌስቡክ እንዲሁም በየተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የተሰራጨውን መረጃ ተከትሎ የኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ስራ አስኪያጅ ዶክተር ያሬድ አግደው ተከታዩን መልዕክት አስተላልፈዋል ፦

በትናንትናው ዕለት በሞት የተለየችንን እናት ለማትረፍ ባለሞያዎቻችን የሚቻላቸውን አድርገዋል ፤ ነገር ግን ህይወቷን ማትረፍ አልቻልንም። ሁላችንም ለቤተሰብ መፅናናትን እንመኛለን።
.
የዝችን እናት ሞት ተከትሎ ለሁሉም ቤተሰብ መርዶ #ባልተነገረበት ሁኔታ መረጃውን የማህበራዊ ሚዲያ ላይ የለጠፉ ገፆች መኖራቸው በጣም ያሳዘነን ክስተት ነው።
.
ይህን የታካሚዎቻችንን ሚስጥራው መረጃ ቤተሰብ ላይ የሚያደርሰውን ጫና ባላገናዘበ መልኩ ለጋዜጠኞች የሚያቀብሉ ባለሞያዎች ካሉ ለወደፊቱ እርማት እንደሚወስዱ እንጠብቃለን።
.
ጋዜጠኞች ባህላችንን አገናዝበን የደረሰንን መረጃዎች በጥንቃቄ እና ሀላፊነት በተሞላበት መልኩ እድናስተላልፍ በትህትና እጠይቃለው።

(ዶክተር ያሬድ አግደው - ኤካ ኮተቤ ሆስፒታል)

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#ALERT🚨

በኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ስርጭት እየተባባሰ ይገኛል።

በወረርሽኙ ሳቢያ የኮቪድ-19 ህክምና መዕከሎች እየሞሉ መሆኑንም የጤና ባለሞያዎች እየጠቆሙ ናቸው።

የፅኑ ህሙማን ክፍሎችም ሞልተው ታካሚዎች የሚስተናገዱት በወረፋ ነው።

#DrYaredAgidew

@tikvahethiopia