TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በትላንትናው ዕለት ከሲዳማ የክልልነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ በሀዋሳ ከተማ በተፈጠረ #ግጭት በትንሹ 3 ሰዎች #መሞታቸውን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘግቧል።
.
.
(#Reuters) - At least three people have died in Ethiopia's southern city of Hawassa, hospital authorities said on Friday, amid a showdown between state security forces and some local activists who want to declare a new region for their Sidama ethnic group.

የሮይተርስን ዘገባ ያንብቡ👇
https://telegra.ph/HAWSSA-07-19
የሟቾች ቁጥር 67 ደርሷል!

#Reuters

ሮይተርስ የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ነገሩኝ ብሎ ባወጣው ዘገባ መሰረት ባለፉት ሁለት ቀናት በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ከተሞች በነበረው ተቃውሞ የ67 ሰዎች ህይወት መጥፋቱን ዘግቧል። ከሟቾቹ ውስጥ 5ቱ የፖሊስ አባላት ናቸው። 13 ሰዎች ደግሞ በጥይት ተመተው የተገደሉ ሲሆን የተቀሩት በድንጋይ ተደብድበው እንደተገደሉ ነው የተገለፀው።

https://telegra.ph/ETH-10-25-3

http://www.dailystar.com.lb/News/World/2019/Oct-25/494338-67-people-killed-in-protests-in-ethiopias-oromiya-region-police.ashx#.XbNI_WnU9lV.facebook

Via #DailyStar
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጂቡቲ በሀገሯ የመጀመሪያው ኮሮና ቫይረስ ተጠቂ ግለሰብ መገኘቱን ሪፖርት አድርጋለች። በቫይረሱ የተያዘው ግለሰብ ከአራት ቀን በፊት ጂቡቲ የደረሰ የስፔን ልዩ ሀይል አባል ነው።

#Reuters
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#TurkishAirlines

የቱርክ አየር መንገድ በኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] ወረርሽኝ ምክንያት ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ5 አገሮች በስተቀር ዓለም አቀፍ በረራዎችን እ.ኤ.አ ከመጋቢት 27 ቀን 2020 ጀምሮ እንደሚያቆም አስታውቋል። አየር መንገዱ ወደ ሆንግ ኮንግ፣ ሞስኮ፣ አዲስ አበባ፣ ኒው ዮርክና ዋሽንግተን የሚያደርገው በረራ እንደማይቋረጥ የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት ቢላል ኢክሲ ማስታወቃቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

#Reuters #etv
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አጫጭር መረጃዎች፦

- የእንግሊዙ ዘውድ ወራሽ የሆኑት ልዑል ቻርልስ በኮሮና ቫይረስ መያዛቸውንና መጠነኛ ምልክት እንደታየባቸው ከቤተ መንግሥቱ የወጣው መረጃ ያስረዳል። ባለቤታቸውም ምርመራ የተደረገላቸው ቢሆንም ከቫይረሱ ነፃ ሆነው ተገኝተዋል።

- በስፔን በኮሮና ቫይረስ ምክንያት የሞቱ ሰዎች ቁጥር ከቻይና መብለጡ ተነግሯል። የስፔን ጤና ጥበቃ ሚንስቴር ባወጣው አሃዝ መሠረት የሞቱ ሰዎች ቁጥር 3434 ደርሷል።

- በሩዋንዳ መንግሥት የተጣለውን የእንቅስቃሴ ገደብ ጥሶ በመውጣት አሳ ለማስገር የሄደው ግለሰብ በአዞ መበላቱ ተሰማ።

- በሁቤይ ግዛት ውሃን የሚገኘው ኤርፖርት ከ APRIL 8 ጀምሮ ዳግም አገልግሎት መስጠት ይጀምራል። ለጊዜው አለም አቀፍ በረራዎችን እንዲሁም ከውሃን ወደ/ከ ቤጂንግ የሚደረጉ በረራዎችን አያስተናግድም።

- ሞስኮ የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን ለመግታት ተጨማሪ እርምጃ ወስዳለች የከተማይቱ ከንቲባ ፦ ማንኛውም አይነት ህዝባዊ ዝግጅት ሞስኮ ውስጥ እንዳይደረግ አግደዋል።

#BBC #REUTERS #XInhua
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፊሊፒንስ ውስጥ 9 ዶክተሮች በኮሮና ቫይረስ ተጠቅተው መሞታቸው ተሰምቷል። የሰዎችን ህይወት ለማትረፍ ከፍተኛ ትግል እያደረጉ ያሉት የፊሊፒንስ የጤና ባለሞያዎች በቂ መከላከያ እያገኙ አይደለም ተብሏል። #StayHomeSaveLives @tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ተጨማሪ ከፊሊፒንስ በDW ፦

- የፊሊፒንስ ሕክምና ማህበር የ9ኙ ሐኪሞቹ ህልፈት የጤና ባለሞያዎች የቫይረሱን መከላከያ ቁሳቁስ እንደማይቀርብላቸው ማሳያ ነው ሲል ወቀሳውን አቅርቧል።

- በዋና ከተማዋ ማኒላ የሚገኙ ሶስት ትልልቅ ሆስፒታሎች በመሙላታቸው በቫይረሱ ታመው የሚመጡ ሰዎችን መቀበል አቁመዋል።

- በመቶዎች የሚቆጠሩ ሐኪሞች ለቫይረሱ ተጋላጭ በመሆናቸው እና በቫይረሱ ሊያዙ ይችላሉ በሚል ጥርጣሬ ለ14 ቀናት መለየታቸውንም ተነግሯል። ይህ ደግሞ ለደሃዋ ፊሊፒንስ በእንቅርት ላይ እንዳይሆንባት አስግቷል።

- በማኒላ ከሆስፒታሎች አቅም በላይ የሆኑትን ታማሚዎች ወደ ሌሎች ሆስፒታሎች ማድረስ ካልተቻለ የሃገሪቱ የሕክምና ስረዓት ውድቀት ሊያጋጥመው ይችላል ተብሏል።

#DW #REUTERS
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የጆ ባይደን እና የአል ሲ ሲ የስልክ ውይይት :

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ጆ ባይደንና የግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱል ፋታህ አልሲሲ ትናንት ሰኞ በታላቁ የህዳሴ ግድብ ጉዳይ ዙሪያ መወያየታቸውን ከሁለቱም ወገን የወጣ መግለጫ አመልክቷል።

ሁለቱ መሪዎቹ በውይይታቸው ግብጽ ከ #ኢትዮጵያ ጋር አለመግባባት ውስጥ ስለገባችበት ስለታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አንስተው መወያየታቸውን ከፕሬዝዳንት ባይደን ጽህፈት ቤት የወጣው መግለጫ አመልክቷል።

ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን እና አልሲሲ ከሕዳሴው ግድብ ጉዳይ በተጨማሪ ባለፈው ሳምንት ጋዛ ውስጥ ተከስቶ የነበረውን ግጭት ለማስቆም በግብጽ አሸማጋይነት ስለተደረሰው ተኩስ አቁምም ተወያይተዋል ተብሏል።

ከዋይት ሐውስ የወጣው መግለጫ እንዳስታወቀው በስልክ በተደረገው ውይይት ላይ "ፕሬዝዳንት ባይደን የአባይን ውሃ በተመለከተ ግብጽ ያላትን ስጋት እንደሚረዱ ገልጸዋል" ብሏል።

በተጨማሪ ፕሬዝዳንት ባይደን በጉዳዩ ዙሪያ "የግብጽን፣ የሱዳንን እና የኢትዮጵያን ሕጋዊ ፍላጎቶችን የሚያሟላ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሔ እንዲገኝ የአሜሪካ ፍላጎት መሆኑን ገልልፀዋል ተብሏል።

በሁለቱ መሪዎች መካከል ስለተደረገው ውይይት የግብጽ ፕሬዝዳንት ጽህፈት ቤት ፥ ባይደን እና አልሲሲ "የሁሉንም ወገኖች የውሃ እና የልማት መብቶችን የሚያስከብር ስምምነት ላይ እንዲደረስ የሚያስችል የተጠናከረ ዲፕሎማሲያዊ ጥረት ለማድረግ ተስማምተዋል" ብሏል።

#BBC #Reuters

@tikvahethiopia
የተመድ ፀጥታው ምክር ቤት ፦

- የተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች
- አልባኒያ፣
- ብራዚል፣
- ጋቦን እና ጋና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ፀጥታ ምክር ቤት በተለዋጭ አባልነት ዛሬ ተመርጠዋል፡፡

ሀገራቱ ኤስቶኒያ፣ ኒጀር፣ ቱኒዚያ ፣ ቬትናም እንዲሁም ሴንት ቪንሴንት ኤንድ ዘ ግሬናዲንስን የተኩ ናቸው።

በፀጥታው ምክር ቤት አሜሪካ ፣ ሩሲያ ፣ ቻይና ፣ ብሪታንያ እና ፈረንሣይ ቋሚ አባላት ሲሆን 10 ቋሚ ያልሆኑ አባላትን አሉት። በአጠቀላይ ምክር ቤቱ 15 አባላት ነው ያሉት።

#Reuters

@tikvahethiopia
"...ከአንድ ቤተሰብ 5 እና 6 ሰዎች የሞቱ አሉ" የጭና ነዋሪዶች

በአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን በዳባት ወረዳ "ጭና" ተብሎ በሚጠራ ቦታ የህወሓት ታጣቂዎች ከአንድ መቶ በላይ ንፁሃንን መግደላቸውን ነዋሪዎች አሳውቀዋል።

ግድያው የተፈጸመው አካባቢው በህወሓት ታጣቂዎች ቁጥጥር ስር በቆዩባቸው ቀናት ውስጥ ሲሆን ሽማግሌዎች፣ ሴቶችና ህጻናት በተፈጸመባቸው ጥቃት ተገድለዋል።

አንድ የጭና አጎራባች ቀበሌ አብጥራ፣ ነዋሪ የሆኑ አስማረ ታፈረ የተባሉ ግለሰብ ለቢቢሲ በሱጡህ ቃል ፥ ነሐሴ 12 ከቀኑ 9፡00 ጀምሮ በአካባቢው የህወሓት ታጣቂዎች በመግባት ተኩስ መክፈታቸውንና ውጊያ መካሄዱን ጠቁመዋል።

ጦርነቱ እስከ ነሐሴ 29 ድረስ መካሄዱን የገለፁ ሲሆን፥ እስካሁን ድረስ ተገድለው የተገኙ 119 ሰዎች በጦርነቱ ያልተሳተፉ የአካባቢው ነዋሪዎች ናቸው ብለዋል።

"ይህ ቁጥር መሞታቸው ታውቆ ለቅሶ እየተለቀሰ ያለ ነው" በማለት ይህ ቁጥር ከዚህ በላይ ሊጨምር እንደሚችል ተናግረዋል።

እንደነዋሪው ገለፃ፥ ከአንድ ቤተሰብ 5 እና 6 ሰዎች ሞተዋል።

ዛሬ ደግሞ ሌሎች የአይን እማኝ ነን ያሉ ነዋሪዎች በጭና ተክለሃይማኖት ቀበሌ የተገደሉ ንፁሃ ከ200 በላይ መሆናቸውን አመልክተዋል። 193 የሚሆኑት በጭና ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን መቀበራቸውን አመልክተዋል።

ከ20 በላይ የሚሆኑት በዲያ ጊዮርጊስ መቀበራቸውን አሳውቀዋል።

አሁንም ተጨማሪ አስከሬን እየተገኘ መሆኑ የተመላከተ ሲሆን የደረሱበት ያልታወቀ እንዳሉም ነው የአካባቢው ነዋሪዎች ገልፀዋል።

More : https://telegra.ph/CHEENA-09-08

Source : #Reuters #BBC #FBC

@tikvahethiopia
#TOYOTA

ቶዮታ / Toyota ዓለም አቀፍ የመኪና አምራች ኩባንያ በዓለም ገበያ በዋነኝነት #በአሜሪካ የተሸጡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎቹን  ከገበያ ላይ እንዲሰበሰቡ አዟል።

ቶዮታ እንዲሰብሰቡ ያዘዘው ከ2020 እስከ 2022 ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ የተመረቱ ተሽከርካሪዎችን ሲሆን ተሽከርካሪዎቹ የ " ኤርባግ " ደህንነት ችግር አለባቸው ተብሏል።

ከ2020 እስከ 2022 ወደ ገበያ የቀረቡ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎች (በዋነኝነት #አሜሪካ) ከ " ኤርባግ " ጋር በተያያዘ ችግር እንዳለባቸው ተደርሶበታል።

ችግሩ በፊት ለፊት ተሳፋሪ መቀመጫ በኩል በስህተት ከተሰራ የ " ኤርባግ ሴንሰር " ጋር የሚያያዝ ሲሆን ምናልባትም በአደጋ ጊዜ " ኤርባጉ " አገልግሎት ላይሰጥ ይችላል። ይህ አደጋ በሚፈጠር ጊዜ ኩዳቱ እንዲጨምር ያደርጋል።

ቶዮታ የትኞቹ ሞዴሎች ይሰብሰቡ አለ ?

#ቶዮታ

ኮሮላ (2020 - 2021)
ራቭ4 ፣ ራቭ4 ሃይብሪድ (2020 - 2021)
ሃይላንደር፣ ሃይላንደር ሃብሪድ (2020 - 2021)
አቫሎን ፣  አቫሎን ሃይብሪድ (2020 - 2021)
ካምሪ፣ ካምሪ ሃብሪድ (2020 - 2021)
ሴና ሀይብሪድ (2021)

#ሌክሰስ

ES250 (2021)
ES300H (2020-2022)
ES350 (2020-2021)
RX350 (2020-2021)
RX450H (2020-2021) የተሰኙ ከ2020 እስከ 2022 ላይ የተመረቱት የ " ኤርባግ " ችግር ስላለባቸው ይሰብሰቡ ብሏል።

ከላይ የተጠቀሱት ተሽከርካሪዎች ያላቸው ሰዎች ኤርባጋቸውን #እንዲያረጋግጡ እና ችግር ካጋጠማቸው እስከ ቀጣዩ የካቲት ወር ድረስ እንዲመልሱለት ቶዮታ ጥሪ አቅርቧል።

የቶዮታ ተሽከርካሪዎች ችግር እንዳለባቸው የታወቀው የጃፓን ትራንስፖርት ሚኒስቴር በሀገሪቱ ተሽከርካሪ እምራች ኩባንያዎች ላይ ባደረገው #ምርመራ ላይ እንደሆነ ተገልጿል።

ይህን ተከትሎ የቶዮታ ኩባንያ አክስዮን ዋጋ ቅናሽ አሳይቷል።

ምርመራው ከቶዮታ ተሽከርካሪዎች በተጨማሪ ዳይሀትሱ በተሰኘው ኩባንያ ላይም ተመሳሳይ ችግር መታየቱን ገልጿል።

ከ87 ዓመት በፊት ኪቺሮ ቶዮታ በተባለ ግለሰብ የተመሰረተው ቶዮታ የተሽከርካሪ አምራች ኩባንያ አሁን ላይ በዓመት 10 ሚሊዮን ተሽከርካሪዎችን በማምረት ላይ ይገኛል።

ከ360 ሺህ በላይ ሰራተኞች ያሉት ቶዮታ ኩባንያ 300 ቢሊዮን ዶላር የተጣራ ሀብት እንዳለው የኩባንያው ዓመታዊ ሪፖርት ያስረዳል።

#ጥቆማ ፦ ከደህንነት ጋር በተያይዘ በተለይም በአሜሪካ እንዲሰበሰቡ የታዘዙ ተሽከርካሪዎችን ቼክ ለማድረግ https://www.nhtsa.gov/recalls በዚህ አድራሻ መጠቀም ይቻላል። የመኪናውን መለያ ቁጥር (VIN) በማስገባት ማወቅ ይቻላል።

Credit - #AlAiN / #Reuters / #Toyota_News_Room

@tikvahethiopia
#Yemen

በአብዛኞቹ #ኢትዮጵያውያን የሆኑ ስደተኞችን አሳፍራ ስትጓዝ የነበረች ጀልባ ከየመን የባሕር ዳርቻ አቅራቢያ ተገልብጣ 39 ሰዎች ሞቱ።

እንደ IOM እና ከአደጋው ከተረፉ ሰዎች በተገኘ መረጃ ጀልባዋ 260 የሚጠጉ ሰዎችን አሳፍራ የነበር።

በካባድ ነፋስ ምክንያት መገልበጧ ተጠቁሟል።

መሞታቸው ከታወቀው 39 ሰዎች ውጪ ሌሎች 150 ሰዎች የደረሱበት አልታወቀም። እነሱን ለማግኘት ፍለጋ እየተደረገ ነው።

71 ሰዎች ከአደጋው ተርፈዋል።

የሩደም አካባቢ ባለሥልጣናት ጀልባዋ ላይ ተሳፈረው ከነበሩት 260 ስደተኞች በአብዛኞቹ #ኢትዮጵያውያን ስደተኞች እንደነበሩ አመልክተዋል።

#Reuters #IOMYemen #IOMspokesperson

@tikvahethiopia
#Sudan

" በ2 ሳምንት ውስጥ ለቃችሁ ውጡ " - የሱዳን ጸጥታ ኃይሎች

የሱዳን የጸጥታ ኃይሎች የውጪ ዜጎች ከዋና ከተማዋ ካርቱም እና በዙሪያ ካሉ አካባቢዎች እንዲወጡ ትዕዛዝ ሰጡ።

ፖሊስ ባወጣው ማሳሰቢያ ፥ የውጪ ዜጎች ከተባሉት የሱዳን አካባቢዎች ለመውጣት የ2 ሳምንት ጊዜ ብቻ ነው የተሰጣቸው።

የሱዳን በመንግሥት ወታደሮች እና የፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ ከገቡ በርካታ ወራት አልፈዋል።

ውጊያ አሁን ድረስ ተጠናክሮ በመቀጠሉ የውጪ ዜጎች ለራሳቸው ደህንነት ሲሉ አካባቢውን ለቀው መውጣት እንዳለባቸው ነው ፖሊስ ያሳሰበው።

በሌላ በኩል ፥ ' በፈጥኖ ደራሹ ኃይል ውስጥ የሌላ ሀገር ቅጥር ነፍሰ ገዳዮች አሉ ' በሚል በመገናኛ ብዙሃን መዘገቡን ተከትሎ በተለይ ከሌሎች የአፍሪቃ ሃገራት በመጡ የውጪ ዜጎች ላይ ጥላቻ ይስተዋላል።

ከቀናት በፊት ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸው ከ150 በላይ የውጪ ዜጎች መታሰራቸውን ሮይተርስ ዘግቧል።

#DW
#Reuters
#SudanMilitary
#RSF

@tikvahethiopia