TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#BenishangulGumuz : ኢሰመኮ በመተከልና ካማሺ ዞኖች የዜጎችን ደኅንነት ለማረጋገጥ እየተወሰዱ ያሉ እርምጃዎች ሊፋጠኑ እንደሚገባ አሳስቧል።

* የኢሰመኮ መግለጫ ከላይ ተያይዟል፤ ያንብቡ!

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#NewsAlert የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ አሻድሊ ሀሰን ጨምሮ የክልሉ የብልጽግና ፓርቲ የሰራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት ወደ ግንባር ለመዝመት ውሳኔ አሳለፉ። " በግንባር ተገኝቼ ጦሩን እመራለሁ " ብለው ወደ ግንባር ያቀኑት የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዚዳንት ዶ/ር አብይ አህመድ ባቀረቡት ጥሪ መሰረት የክልሉ ርዕሰ-መስተዳድር አቶ አሻድሊ ሀሰንን ጨምሮ የክልሉ የብልጽግና ፓርቲ የሰራ አስፈጻሚ…
#BenishangulGumuz

የኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ወደ ግንባር ዘምተው ጦሩን እንደሚመሩ በይፋ ካሳወቁ በኃላ " እኛም ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ወደ ጦር ግንባር እንዘምታለን " ያሉት ከፍተኛ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለስልጣናት መሰረታዊ የውትድርና ስልጠና እየወሰዱ እንደሚገኙ ታውቋል።

ከትላንት አርብ አንስቶ የክልሉ ከፍተኛ ባለስልጠናት መሠረታዊ የውትድርና ስልጠና እየወሰዱ ሲሆን ስልጠናው ዛሬ ተጠናክሮ መቀጠሉን ነው የክልሉ መንግስት ያስታወቀው።

ባለስልጣናቱ ዛሬ አካላዊ የስፓርት እንቅስቃሴ ጨምሮ ፣ መሠረታዊ የቦታ አያያዝ፣ ዒላማና የተኩስ ልምምድ ማድረጋቸው ተገልጿል።

በስልጠናው ላይ እየተሳተፉ የሚገኙት ባለስልጣናት ፥ " ከስልጠናው በኋላ ህወሓትና ተላላኪዎቹ አገራችን ለማፍረስ የከፈቱትን ጦርነት ለመቀልበስ በግንባር ተገኝተን ፊት ለፊት ጦርነቱን ለመምራት ቁርጠኛ ነን " ሲሉ ተናግረዋል።

ለ ክልሉ ከፍተኛ ባለስልጣናት እየተሰጠ የሚገኘው መሠረታዊ የውትድርና ስልጠና ለቀጣዮቹ 5 ቀናት እንደሚቀጥልም ከክልሉ ኮሚኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#BenishangulGumuz

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሁለት ዞኖች በፀጥታ ችግር ምክንያት ከ2 ዓመት በላይ ምንም አይነት የመብራት አገልግሎት አላገኙም።

የክልሉ መንግስት ኮሙዩኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ መለሰ በየነ ለአሐዱ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ፥ ባለፉት ዓመታት በመተከል እና ካማሽ ዞኖች በታጣቂዎች የተስተጓጎለው የመብራት አገልግሎት መፍትሔ ሳያገኝ እስካሁን ድረስ ዘልቋል ብለዋል፡፡

በዚህም ህብረተሰቡ ለከፍተኛ እንግልት ተዳርጓል ፤ በተለይም በከተሞች አካባቢ በመብራት ኃይል ብቻ ስራቸውን የሚሰሩ ዜጎችን ለስራ አጥነት ተጋላጭ አድርጓቸዋል ሲሉ ገልፀዋል።

ችግሩ መቼ ይፈተል በሚል ከቴሌቪዥን ጣቢያው ለቀረበላቸው ጥያቄ ፥ " በቀጣይ የክልሉ የፀጥታ ሁኔታ ሲስተካከል እግር በግር በመከተል ተቋርጦ የነበረውን የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመመለስ ይሰራል " ሲሉ መልሰዋል።

ምንጭ ፦ አሐዱ ቴሌቭዥን

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በአንደኛው ዙር በፀጥታ ችግር የ12ኛ ክፍል ፈተና መውሰድ ያልቻሉ ተማሪዎች ዛሬ ፈተናቸውን ጀምረዋል። መልካም ፈተና! @tikvahethiopia
#Update

የመጀመሪያው ቀን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ሲሰጥ ውሏል።

ፈተናው በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ አፋር እና ቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ተሰጥቷል።

#Amahra

በአማራ ክልል ከ37 ሺ በላይ ለሆኑ ተማሪዎች ዛሬ ፈተና ሲሰጥ ውሏል። ፈተናው በደቡብና ሰሜን ወሎ፣ ዋግኸምራ፣ ኦሮሞ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞኖችና በደሴ ከተማ ፣ የሰሜን ሸዋ ዞን 3 ወረዳዎች፣ በሰሜን ጎንደር ዞን በ1 የፈተና ጣቢያ ፈተናው ነው የተሰጠው።

በሌላ በኩል ከኦሮሚያ ክልል ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ ዞኖች ተፈናቅለው ለመጡ 220 ተማሪዎችም በልዩ ሁኔታ በቡሬ በተቋቋመ የመፈተኛ ጣቢያ ተፈትነዋል።

#OromiaRegion

በኦሮሚያ ክልል በቄለም ወለጋ ዞን በ12 ወረዳዎች በ42 የፈተና ጣቢያዎች 14,228 ተማሪዎች ለፈተና መቀመጣቸው ፤ ፈተናውን እንደሚወስዱ ከተጠበቁት 16,608 ተማሪዎች መካከል 1, 243 በተለያዩ ምክንያቶች ፈተና ላይ አለመቀመጣቸው ተገልጿል።

በምዕራብ ወለጋ የቤጊ እና ቆንደላ ወረዳዎች 1,137 ተማሪዎች በአራት የፈተና ጣቢያ ፈተናው ላይ የተቀመጡ ሲሆን በተለያዩ ምክንያቶች 931 ተማሪዎች ፈተናው ላይ እንዳልተቀመጡ ተገልጿል።

#Afar

በአፋር ክልል ፈተናውን ይወስዳሉ ተብለው ከተጠበቁት 257 ተማሪዎች 154 ተማሪዎች ፈተናውን መውሰድ ጀምረዋል።

#BenishangulGumuz

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ካማሺ ዞን አንፃራዊ ሠላም ተመዝግቦባቸዋል በተባሉ አካባቢዎች የ12ኛ ክፍል የዩኒቨርስቲ መግቢያ ፈተና ሲሰጥ ውሏል።

• የሁለተኛው ቀን ፈተና ይቀጥላል።

መረጃ ፦ ኢብኮ፣ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ትምህርት ቢሮ፣ የአማራክ ክልል ትምህርት ቢሮ

ፎቶ ፦ የደሴ፣ ኮምቦልቻ፣ የወልዲያ ከተማ ፣ የጅሌ ጥሙጋ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ቢሮዎች ፣ የቤ/ጉ ክልል ትምህርት ቢሮ

@tikvahethiopia
#BenishangulGumuz , #Kamashi📍

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የካማሺ ዞን አስተዳደር በአገር ሽማግሌዎችና በሃይማኖት አባቶች በኩል፣ በዞኑ ከሚገኙ ታጣቂዎች ጋር እየተነጋገረ መሆኑ ተገልጿል።

በዞኑ አስተዳደርና በታጣቂዎች መካካል የሚደረገው ንግግር " ጥሩ ደረጃ " ላይ እንደሚገኝ የተገለጸ ሲሆን፣ ታጣቂዎቹ ያሏቸውን ጥያቄዎች በሽማግሌዎች በኩል በደብዳቤ አቅርበው ሁለቱም አካላት በተነሱ አጀንዳዎች ላይ መስማማታቸው ታውቋል፡፡

በቅርቡ አዳዲስ አመራሮች የተሾሙለት ካማሺ ዞን፣ አዲሶቹ አመራሮች ያዋቀሯቸው የአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች ወደ የሚገኙበት ያሶ ወረዳ ሄደው ታጣቂዎቹን ማነጋገራቸው ተገልጿል፡፡

ከዞኑ አስተደዳር የተላኩት እነዚህ ልዑካን ከታጣቂዎች ጋር ውይይት ካደረጉ በኋላ፣ በታጣቂዎቹ በኩል የተወከሉ የአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶችን ይዘው ወደ ካማሺ ከተማ መመለሳቸው ተሰምቷል፡፡

በሁለቱም በኩል ያሉ ልዑካን ጥር 21 ቀን 2014 ዓ.ም. ይዘው የመጡትን የውይይት ሪፖርት በተመለከተ፣ ከዞኑ አመራሮች እንዲሁም በዞኑ ከሚገኙና ከክልሉ የፀጥታ አካላት ጋር ውይይት አድርገዋል።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብጅጋ ጻፊዮ ፤ ከውይይቱ በኋላ በሁለቱም ወገን ያሉ ሽማግሌዎች ተመልሰው ወደ ታጣቂዎቹ ዘንድ መሄዳቸውን አስረድተዋል፡፡

በካማሺ በተደረገው ውይይት ላይ ታጣቂዎቹ ለሰላም ፍላጎት እንዳላቸው በሽማግሌዎቹ በኩል መግለጻቸውን የተናገሩት ዋና አስተዳዳሪው፣ ታጣቂዎቹም ሆነ የክልሉ መንግሥት ባሏቸው አጀንዳዎች ላይ መግባባት እንዳለ ገልጸዋል፡፡

የሪፖርተር ጋዜጣ ዘገባን ያንብቡ : https://telegra.ph/Reporter-02-09

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BenishangulGumuz , #Kamashi📍 የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የካማሺ ዞን አስተዳደር በአገር ሽማግሌዎችና በሃይማኖት አባቶች በኩል፣ በዞኑ ከሚገኙ ታጣቂዎች ጋር እየተነጋገረ መሆኑ ተገልጿል። በዞኑ አስተዳደርና በታጣቂዎች መካካል የሚደረገው ንግግር " ጥሩ ደረጃ " ላይ እንደሚገኝ የተገለጸ ሲሆን፣ ታጣቂዎቹ ያሏቸውን ጥያቄዎች በሽማግሌዎች በኩል በደብዳቤ አቅርበው ሁለቱም አካላት በተነሱ አጀንዳዎች…
#BenishangulGumuz , #Kamashi📍

የካማሺ ዞን ታጣቂዎች ያናሷቸው ጥያቄዎች ምንድናቸው ?

የካማሺ ዞን ኮማንድ ፖስት ዋና አስተባባሪ ኮሎኔል ዓለሙ በሽር  ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደተናገሩት ታጣቂዎቹ በእስር ላይ ያሉ አባሎቻቸው እንዲፈቱ ጠይቀዋል።

የዞኑ አስተዳደሮች ይሄ ጥያቄ በዞኑ የሚመለስ እንዳልሆነ አስረድተው፣ በጉዳዩ ላይ ከበላይ አካላት ጋር ንግግር በማድረግ መልስ እንደሚሰጡ አሳውቀዋል።

ሌላው በመተከል ዞን የሚገኙና ከክልሉ ውጪ ያሉ የፀጥታ ኃይሎች እንዲወጡ ታጣቂዎቹ ጠይቀዋል።

ኮሎኔል ዓለሙ በሽር ፥ " የሌሎቹን አላውቅም፤ የፌዴራል ፖሊስ እና መከላከያ ሠራዊትን ግን ማስወጣት አይችሉም፣ ይኼ አይመለስላቸውም እርግጠኛ ነኝ " ብለዋል።

በተጨማሪም ታጣቂዎቹ " በክልሉ ውስጥ ድርሻ ይኑረን " የሚል ጥያቄም አንስተዋል።

የካማሺ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ብጅጋ ጻፊዮ ፤ ታጣቂዎቹ ያቀረቧቸውን ጥያቄዎች በተመለከተ በካማሺ ዞን ደረጃ ሚስተናገዱትን እንደሚመለሱ በክልል ወይም በፌዴራል ደረጃ የሚመለሰውን ደግሞ የዞኑ አስተዳደር ለበላይ አካላት እንደሚያስታውቅ ስምምነት ላይ መደረሱን ለጋዜጣው አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BenishangulGumuz , #Kamashi📍 የካማሺ ዞን ታጣቂዎች ያናሷቸው ጥያቄዎች ምንድናቸው ? የካማሺ ዞን ኮማንድ ፖስት ዋና አስተባባሪ ኮሎኔል ዓለሙ በሽር  ለሪፖርተር ጋዜጣ እንደተናገሩት ታጣቂዎቹ በእስር ላይ ያሉ አባሎቻቸው እንዲፈቱ ጠይቀዋል። የዞኑ አስተዳደሮች ይሄ ጥያቄ በዞኑ የሚመለስ እንዳልሆነ አስረድተው፣ በጉዳዩ ላይ ከበላይ አካላት ጋር ንግግር በማድረግ መልስ እንደሚሰጡ አሳውቀዋል።…
#Update

#BenishangulGumuz , #Kamashi📍

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በጫካ ያሉ ታጣቂዎች ፤ ትጥቃቸውን በሚፈቱበት አካሄድ ላይ ከተወካዮቻቸው ጋር ውይይት ሊደረግ መሆኑ ታውቋል።

የክልሉ መንግስት የተሃድሶ ስልጠና ሃሳቡን ያቀረበው፤ ከጉሙዝ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ጉህዴን) ታጣቂዎች ጋር ትላንት ቅዳሜ መጋቢት 10 ቀን 2014 በይፋ ዕርቅ መፈጸሙን ተከትሎ መሆኑ ተገልጿል።

በጉሙዝ ባህል መሰረት የተከናወነው የዕርቅ ስነ ስርዓት የተካሄደው በካማሺ ዞን፤ ካማሺ ከተማ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽና በካማሺ ወንዝ ዳርቻ ነው።

በዕርቅ ስነ ስርዓቱ ላይ የምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ጌታሁን አብዲሳ፣ የክልሉ ም/ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወይዘሮ አለምነሽ ይባስ እና የጉህዴን ሊቀመንበር አቶ ግራኝ ጉደታ ተገኝተው ነበር።

በካማሺ ከተማ የስብሰባ አዳራሽ በተከናወነው ዕርቅ ለአራት ሰዓታት የዘለቀ ነበር።

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት እና በጉህዴን አመራሮች መካከል ዕርቅ መውረድ ተከትሎ፤ በጫካ የነበሩ አማጽያን ከእነ ትጥቃቸው ወደ ካማሺ ከተማ ሲገቡ መመልከታቸውን አንድ የከተማውን ነዋሪዎች ዋቢ አድርጎ ድረገፁ አስነብቧል።

የታጣቂዎቹን ወደ ከተማ መግባት የካማሺ ዞን ኮሚዩኒኬሽን ኃላፊ አቶ ቦካ አቦሴም አረጋግጠዋል።

ታጣቂዎቹ ለጊዜው የካማሺ ዞን ባዘጋጀላቸው ማረፊያ እንደሚቆዩ የኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ኃላፊው ገልፀው ፤ በየትኛው የከተማው አካባቢ እንደሚቆዩ ግን ከመግለጽ ተቆጥበዋል።

ያንብቡ ፦ telegra.ph/Ethiopia-Insider-03-20

Credit - Ethiopia Insder

@tikvahethiopia
#BenishangulGumuz📍

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በአለም አቀፍ የስደተኞች ተቋም / IOM / እና አክሽን ፎር ዘ ኒዲ ኢን ኢትዮጵያ በተባሉ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ድጋፍ የሚካሄድ ፕሮጀክት ይፋ ሆነ።

ይህ ፕሮጀክት ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ በጀት እንደተመደበለት የተገለፀ ሲሆን በክልሉ ላሉ ተፈናቃዮች የጊዜያዊ መጠለያ ግንባታ ይከናወናል ተብሏል።

ፕሮጀክቱ በመተከል እና ካማሺ ዞኖች እንዲሁም ማኦ ኮሞ ልዩ ወረዳዎች እንደሚካሄድ  ታውቋል።

ተፈናቃይ ወገኖችን ለማቋቋም የተደረገው ጥረት የሚበረታታ ቢሆንም ከተፈናቃዮች ቁጥር አንጻር  ችግሩን መፍታት እንዲቻል መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ድጋፋቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጠይቋል።

መንግስት ከባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ ከማቀድ ጀምሮ  ለተፈናቃዮች የእለት ደራሽ ድጋፍ እያቀረበ መሆኑን የገለፀው የክልሉ መንግስት ጊዜያዊ መጠለያ ለመስራት የተጀመረው ፕሮጀክትም የዚሁ ማሳያ ነው ማለቱን ኢዜአ ዘግቧል።

ከክልሉ አደጋ ስጋት እና ስራ አመራር ኮሚሽን በተገኘው መረጃ በክልሉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ተፈናቃዮች በጊዜያዊ መጠለያ እና በግለሰቦች ቤት ተጠግተው ይኖራል።

@tikvahethiopia
#BenishangulGumuz📍

በኢትዮጵያ በተለያየ አቅጣጫ በጦርነት እና በግጭት ምክንያት እጅግ በርካታ ወገኖቻችን ተፈናቅለው ይገኛሉ።

በርካታ ተፈናቃይ ወገኖቻችን ከሚገኙባቸው አካባቢዎች አንዱ የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ነው።

በክልሉ በተለያየ ጊዜ በተከሰተ የፀጥታ ችግር ከሞቀው ቄያቸው ተፈናቅለው እርዳታ የሚጠባበቁ ወገኖቻችን ቁጥር እየጨመረ ሲሆን ከክልሉ የአደጋ ስራ አመራር ኮሚሽን እንደተገኘው መረጃ አሁን በክልሉ ከ400 ሺህ በላይ ተፈናቅይ ይገኛል።

ከመኖሪያቸው ከተፈናቀሉ ጀምሮ በርካታ ችግር እየደረሰባቸው እንደሆነ የሚናገሩት ተፈናቃይ ወገኖቻችን ዝናብ እና ፀሃይ እየተፈራረቀባቸው መሆኑን እና የሚደረግላቸው ድጋፍ በቂ እንዳልሆነ አስረድተዋል።

ከተፈናቃዮቹ ብዛት ያላቸው ሴቶች፣ ህፃናት ፣ ተማሪዎች የሚገኙ ሲሆን በእድሜ የገፉ አረጋዊያን በመጦሪያ እድሜያቸው ተፈናቅለው እየተንገላቱ ናቸው።

እርዳታ እየተደረገላቸው እንደሆነ የሚገልፁት ተፈናቃዮች ግን በቂ እንዳልሆነ ምግብ፣ የህክምና፣ አልባሳት ድጋፍ እንደሚያስፈልጋቸው ገልፀዋል።

ክልሉን የሚያስተዳድሩት አቶ አሻድሊ ሀሰን ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ በሰጡት ቃል፤ በክልሉ ከደረሰው ጉዳት እና ካለው ተፈናቃይ ቁጥር አንፃር የሚደረገው ድጋፍ ተጠናክሮ ሊቀጥል እንደሚገባ ገልፀው ለመንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ፣ አጋር አካላት ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ጠይቀዋል።

እየቀረበ ካለው ጥሪ ጋር በተያያዘ ፤ Action for Social Development and Environmental Protection Organization (ASDEPO) የተባለ ድርጅት ከ100 ሺህ በላይ ሰዎችን ለመድረስ 40 ሚሊዮን ብር በጀት የተያዘለት ፕሮጀክት ይፋ ማድረጉን ከብሄራዊ ቴሌቪዥን ጣቢያ ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahethiopia
#Amhara #BenishangulGumuz

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን እና በአማራ ክልል ወረዳዎች እንደቀድሞው ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲኖር መግባባት ላይ መደረሱ ተገለፀ።

አራት ዓመታትን ያስቆጠረው የመተከል ዞን የሰላም መደፍረስ ወደ ፍፁም ሰላም እንዲመለስ በመተከል እና በአማራ ክልል አጎራባች ወረዳዎች በትናንትናው ዕለት የምክክር መድረክ ተካሂዷል ።

የጓንጓ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ መኮንን ለኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ሬድዮ በሰጡት ቃል የትላንቱን የምክክር መድረክ " ከሁሉም የመተከል ዞን ወረዳዎች እና የአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር ወረዳዎች የተውጣጡ የእምነት አባቶች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ የፖለቲካ አመራሮች እና በአጠቃላይ ከ500 በላይ እንግዶች ተሳትፈውበታል " ብለዋል።

ኃላፊው ፥ ወረዳዎቹ ከዚህ በፊት ብዙ ተፈናቃዮችን ያስተናግዱ እንደነበር እና በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የችግሩ ገፈጥ ቀማሽ እንደነበሩ ገልፀው ፤ አሁን ላይ የነበረውን ግጭት ወደ ጎን ትተው #ለእርቅ መስማማታቸውን ገልፀዋል።

ከሁለቱም ወገን እንደቀድሞው ሰላማዊ እንቅስቃሴ እንዲኖር መግባባት ላይ መደረሱ የተነገረ ሲሆን በቦታው ያሉ ልዩ ሀይሎች፣ መከላከያን ጨምሮ እንዲሁም ጥምር የፌዴራል ፖሊስ ሃይል ሀላፊነት እንዳለባቸው ተነስቷል።

ከዚህ በፊት ሸፍተው በጫካ የነበሩ የጉሙዝ ብሔረሰብ ተወላጆች እጃቸውን በመስጠት ትጥቅ ፈትተው፤ በባህላቸው መሠረት ዕርቅ ፈፅመው ከማህበረሰቡ ጋር መቀላቀላቸውን የጓንጓ ወረዳ መንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ብርሃኑ መኮንን ለሬድዮ ጣቢያው ተናግረዋል።

Credit : Ethio FM 107.8

@tikvahethiopia
#BenishangulGumuz

• “ የውሃ አቅርቦት ተቋርጦ ችግር ላይ ወድቀናል ” - ነዋሪዎች

• “ የመብራት ችግር ነው ” - የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ

• “ የተቋረጠው የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቀጠል እየተከታተልን ነው ” - የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት
 

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማን ጨምሮ ሌሎች አካባቢዎች የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ባለመኖሩ መቸገራቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ ገለጹ።

“ የውሃ አቅርቦት ተቋርጦ ችግር ላይ ወድቀናል። ውሃ ካለበት ቦታ በጀሪካ እስከ 30 ብር ለመግዛት ተገደናል ” ሲሉ አማረዋል።

በወንበራ፣ በአሶሳ ከተማና ሌሎችም ቦታዎች የውሃ መብራት ችግር እንዳለ ገልጸው፣ የሚመለከተው አካል መፍትሄ እንዲሰጣቸው በአንክሮ ጠይቀዋል።

ቲክባህ ኢትዮጵያም ምን ተፈጥሮ ነው አገልግሎቱ የተቋረጠው ? ሲል የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮን ጠይቋል።

የቢሮው ኃላፊ አቶ አድማሱ ሞርካ “ የመብራት ችግር ነው። ያለ መብራት አይደለም የሚሰራው ውሃው። ቅሬታቸው ትክክል ነው ” ብለዋል።

“ መንዲ የሚባል አካባቢ ላይ ኤሌክትሪክ ተበላሽቶ ተስካክሎ ነበር። በድጋሚ ተበላሽቶ ነው። በዚህ ምክንያት የከተማው ውሃ የተቋረጠበት ሁኔታ አለ ” ሲሉ አክለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያም፣ አሶሳ ከተማ ላይ የኤሌክትሪክ ችግር ከመከሰቱ ቀድሞም የውሃ አቅርቦት ችግር እንደነበር ተመላክቷል፤ ችግሩን ለመቅረፍ ቢሮው ምን እየሰራ ነው ? ሲል ተጨማሪ ጥያቄ አቅርቧል።

ኃላፊው በምላሻቸው፣ “ ችግሩን ለመቅረፍ ያቀድነው ጉድጓዶችን መጨመር ነው። 4 ነበር ያቀድነው 3ቱ ተቆፍረው ለአገልግሎት ዝግጁ ሆነዋል ” ብለዋል።

“ ሁለተኛ አማራጭ ደግሞ ታንከሮች ናቸው። ከዚህ በፊት ለ500 ሺህ ህዝብ ነው ታንከር የተሰራው። ይሄም በቂ ባለመሆኑ 3 ታንከር ለመጨመር አቅደን አሁን ዝግጁ ሆነዋል ” ሲሉ ተናግረዋል።

የመብራት ችግሩን በተመለከተ ጥያቄ ያቀረብንላቸው የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ካሳሁን ከበደ፣ “ አሶሳ አካባቢ ተቋርጦ ነው ያለው። ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋረጠ መስመር አለ ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“ ባለቤትነቱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ቡድን የነቀምት ቢሮ ነው። ከእነርሱ እየገዛን ነው ኤሌክትሪክ ለማህበረሰቡ የምንሸጠው። የተቋረጠው ኤሌክትሪክ እንዲቀጠል እየተከታተልን ነው። ድጋፍ እያደረግንም ነው ” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BenishangulGumuz • “ የውሃ አቅርቦት ተቋርጦ ችግር ላይ ወድቀናል ” - ነዋሪዎች • “ የመብራት ችግር ነው ” - የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ውሃና ኢነርጂ ቢሮ • “ የተቋረጠው የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቀጠል እየተከታተልን ነው ” - የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት  በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል አሶሳ ከተማን ጨምሮ ሌሎች አካባቢዎች የመጠጥ ውሃ አቅርቦት ባለመኖሩ መቸገራቸውን ነዋሪዎች ለቲክቫህ…
#BenishangulGumuz

° “ ኤሌክትሪክ ከተቋረጠ 3 ወር ሆነው። ጨለማ ውስጥ እየኖርን ነው” - የወምበራ ወረዳ ነዋሪዎች

° “ ከወረዳው መንግስት ጋር እየተየጋገርን ነው፤ በቅርቡ እንሰራዋለን ” - የደብረ ዘይት ማዕከል

በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ ወምበራ ወረዳ ደብረ ዘይት ከተማ ኤሌክትሪክ በመቋረጡ ጨለማ ውስጥ ለመኖር መገደዳቸውን ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

“ ኤሌክትሪክ ከተቋረጠ 3 ወር ሆነው። ጨለማ ውስጥ እየኖርን ነው። የፋሲካ በዓል አካባቢ ሁለት ቀን በርቷል ከዚያ በኋላ ምንም የለም ” ብለዋል።

ችግሩ ፦
-  በኑሯቸው ላይ ፈተና እንደሆነባቸው፣
- ተማሪዎች ለመማር፣ ፕሮጀክቶችን ለመስራት እንደተቸገሩ፣ 
- ለስልክ ቻርጅ በጀኔሬተር 20 ብር እንደሚከፍሉ፣ 
- በመስሪያ ቤታቸው ጀነሬተር፣ በቤታቸው Solar Energy ስላላቸው ባለስልጣናቱ ለጉዳዩ ቸልተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል።

“ ግብር እየከፈልን መሰረታዊ የሆኑ አገልግሎት ፍትሃዊ በሆነ መንገድ አለመጠቀም ግን አግባብነት የሌለው ቅሬታን የሚያስነሳ ጉዳይ ነው ” ብለዋል።

በወረዳው የታላቁ ህዳሴ ግድቡ በቅርበት ቢገኝም ተጠቃሚ ባለመሆናቸው የሚመለከተው አካል ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።

አቶ የኔሰው የኤሌክትሪክ አገልግሎት የደብረ ዘይት ማዕከል ኃላፊ አገልግሎቱ ለምን እንደተቋረጠ ጠይቀናቸው በሰጡት ምላሽ፣ ቡለን ላይ ኤሌክትሪክ ስለተቋረጠ መሆኑን አስረድተዋል።

"እንደ ወንበራ ደብረ ዘይት ቅድሚያ የቡለን ማዕከል ራሱን የቻለ አለ። እሱ ከበራ በኋላ ነው እኛ ማብራት የምንችለው። ቡለን ከበራ ይበራል" ብለዋል።

ችግሩን ለመቅረፍ ምን እየተሰራ ነው? ተብሎ ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ "ከወረዳው መንግስት ጋር እየተየጋገርን ነው፤ በቅርቡ እንሰራዋለን" የሚል ምላሽ ተሰጥተዋል።

የክልሉ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ካሳሁን ከበደ ሰሞኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል፣ "የተቋረጠው ኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቀጠል እየተከታተልን ነው" ብለው ነበር።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BenishangulGumuz ° “ ኤሌክትሪክ ከተቋረጠ 3 ወር ሆነው። ጨለማ ውስጥ እየኖርን ነው” - የወምበራ ወረዳ ነዋሪዎች ° “ ከወረዳው መንግስት ጋር እየተየጋገርን ነው፤ በቅርቡ እንሰራዋለን ” - የደብረ ዘይት ማዕከል በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል፤ ወምበራ ወረዳ ደብረ ዘይት ከተማ ኤሌክትሪክ በመቋረጡ ጨለማ ውስጥ ለመኖር መገደዳቸውን ነዋሪዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ። “ ኤሌክትሪክ ከተቋረጠ…
#BenishangulGumuz

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ፤ አሶሳ ከተማ የኤሌክትሪክ ኃይል ከተቋረጠ 2 ሳምንት አልፏል።

የአሶሳ አጠቃላይ ሆስፒታል ሁኔታው በዚህ ከቀጠለ አገልግሎት ሊቆም እንደሚችል አሳውቋል።

ሆስፒታሉ በየቀኑ ከ400 እስከ 500 ከዞን ፣ ከወረዳ፣ ከአጎራባቹ ኦሮሚያ ክልል ታካሚዎችን ያስተናግዳል።

ሆስፒታሉ ከሚሰጠው አገልግሎት አንጻር 24 ሰዓት ሙሉ የማይቋረጥ ኃይል ማግኘት ያለበር ቢሆንም ባለፉት ሳምንታት የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጡ በተቋሙ ላይ ከፍተኛ ጫና አሳድሯል።

ኃይል ከተቋረጠበት ቀን አንስቶ ለጄኔሬተር በየቀኑ ከ180 እስከ 200 ሊትር ነዳጅ እየተጠቀመ ነው።

ሁለት ጄኔሬተሮች ያሉ ቢሆንም ሙሉ ሆስፒታሉን ኃይል እንዲያገኝ የሚያስችሉ አይደሉም።

ያለ ጊዜያቸው የሚወለዱ ጨቅላ ሕጻናትን ለማቆየት የሚሆኑ ማሽኖችን ማስነሳትም ከባድ ሆኗል።

በዚህ ማሽን ውስጥ የሚቆዩ ሕጻናት ያልተቋረጠ ኦክስጅን ማግኘት ስላለባቸው ኃይል መቋረጥ ካጋጠመ በሕጻናቱ ላይ ሞት ሊያስከትል ይችላል።

ሆስፒታሉ የተወሰኑ የሥራ ክፍሎችን የኃይል አቅርቦት እያጠፋ ነው ጄኔሬተሩ ሲነሳ የኤሌክትሪክ ኃይሉን ወደ ጨቅላ ሕጻናት ማቆያ ማሽኑ የሚቀይረው። ሌሎች የሥራ ዘርፎች ላይ ኃይሉ ሲፈለግ ደግሞ ማሽኑን ለማቋረጥ ይገደዳል።

ቀድሞም የበጀት እጥረት የሚፈተነው ሆስፒታሉ ለጄኔሬተሩ የሚውለው ነዳጅ ወጪ ከአቅም በላይ እንደሆነ የነዳጅ ማከማቻም አለመኖር ፈተና እንደሆነ ገልጿል።

ሆስፒታሉ ነዳጅ ከተለያዩ መ/ቤቶች እና ባለሃብቶች በልመና ነው ማታ ማታ እየዞረ የሚያመጣው።

ሁኔታው በዚህ ሁኔታ ከቀጠለ የድንገተኛ ህክምና አገልግሎት ጭምር ሊቋረጥ የሚችልበት አዝማሚያ እንዳለ አሳውቋል።

የአሶሳ ዞን ፥ በአሶሳ ከተማ እና በአካባቢው የኃይል መቋረጥ የተከሰተው በአጎራባች የኦሮሚያ ክልል፣ ምዕራብ ወለጋ ዞን በሚገኝ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ላይ " በታጣቂዎች " በደረሰ ጉዳት እንደሆነ አሳውቋል።

#BBCAMHARIC

@tikvahethiopia