TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#አብን

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) ዶ/ር በለጠ ሞላን በድጋሚ የፓርቲው ሊቀመንበር አድርጎ መረጠ።

አቶ መልካሙ ሹምዬ ደግሞ የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር ሆነው ተመርጠዋል።

የአብን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጣሂር መሐመድ ፤ ፓርቲው ለ3 ቀናት የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባውን ሲያካሂድ እንደቆየና የሥራ አስፈፃሚ አባላቱን በአዲስ በማደራጀት ማጠናቀቁን ገልጸዋል።

በዚህም መሠረት፦

👉 ዶ/ር በለጠ ሞላ - ሊቀመንበር
👉 አቶ መልካሙ ሹምዬ - ምክትል ሊቀመንበር
👉 ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ - የውጭ ግንኙነት ኃላፊ
👉 አቶ ዩሱፍ ኢብራሒም - የሕግ ጉዳዮች ኃላፊ
👉 አቶ ክርስቲያን ታደለ - የፖሊሲ እና ስትራቴጂ ክፍል ኃላፊ
👉 አቶ ጋሻው መርሻ - የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ
👉 አቶ ጣሂር መሐመድ - የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ
👉 ዶ/ር ቴዎድሮስ ኃ/ማርያም - የአብን ጽ/ቤት ኃላፊ
👉 አቶ ሐሳቡ ተስፋየ - አደረጃጀት ጉዳዮች ኃላፊ አድርጎ የሥራ አስፈፃሚውን በአዲስ አደራጅቷል።

ከተመረጡት የፓርቲው የሥራ አስፈፃሚዎች መካከል ሦስቱ አዲስ መሆናቸው ተገልጿል።

ፓርቲው ዛሬ 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤውን በአማራ ክልል መዲና ባህር ዳር ማካሄድ መጀመሩን #ኢብኮ / #አሚኮ ዘግቧል።

@tikvahethiopia
" ትውልዱ የፊቼ ጨምበላላን ትርጓሜና እሴቶቹን መገንዘብ ያስፈልገዋል " - ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የሲዳማ ዘመን መለወጫ በዓል ለሆነው ለፊቼ ጨምበላላ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላልፈዋል።

ዶ/ር ዐቢይ በሲዳምኛ ቋንቋ /Sidaamu Afoo/ ባስተላለፉት መልእክት ፤ በዚህ ዘመን ያለው ትውልድ የፊቼ ጨምበላላን ትርጓሜና እሴቶቹ ሰላም ፤ ፍቅር እና አንድነት መሆኑን ትምህርት መውሰድ ወይንም መገንዘብ እንደሚያስፈልገው አሳስበዋል።

#ኢብኮ

@tikvahethiopia
" ቤቲንግ እንዲታገድ እየሰራሁ ነው " - የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር

የስፖርት ውርርድ / ቤቲንግ እንዲታገድ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የሴቶች እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ከታዲጊዎች እና ወጣቶች ስብዕና ግንባታ እንዲሁም በተለያየ መንገድ ከሚያስከትላቸው ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ቀውሶች አንጻር ዘርፉ ሊታገድ ይገባል በሚል በትኩረት እየተሰራ እንደሚገኝ ሚኒስቴሩ ገልጿል።

በተለያየ ጊዜ የተዘጋጁ የዳሰሳ ጥናቶች የስፖርት ውርርድ ለወጣቱና ለታዳጊው ዘርፈ ብዙ አደጋ የደቀነ መሆኑን ያመላከቱ ናቸው የተባለ ሲሆን ዘርፉ በተጨባጭ ችግር የሚፈጥር መሆኑን ተገምግሟል።

ሚኒስቴሩ የስፖርት ውርርድ ' ቁማር ነው ' ብሎ እንቅስቃሴ መጀመሩን እና ቁማር የሚባለው ነገር ደግሞ በራሱ ዘርፈ ብዙ ችግሮች የሚያስከትል ጉዳይ መሆኑን ገልጿል።

ቁማር ታዳጊዎችን ይሁን አዋቂ ሰዎችን ወዳልተፈለገ መንገድ ሊወስድ የሚችል ማህበራዊ ቀውስ እንደሆነና ማንኛውም ሰው ሰርቶ የመለወጥ እሳቤውን የሚያቀጭጭ፣ ቤተሰብን ጭምር ወደ መበተን ሊያደርስ የሚችል ጉዳይ መሆኑን አስገንዝቧል።

ወጣቶች እና ታዲጊዎች ለቤቲንግ ውርርድ ሲሉ ያላቸውን ነገር በሙሉ እስከማውጣት እንደሚደርሱ የተጠቀሰ ሲሆን ወጣቶች ስራን ከመስራት ይልቅ በአቋራጭ መክበር እንዲያስቡ በማድረግ ምርት እና ምርታማነትን የሚቀንስ ተግባር ነው ብሏል።

ሚኒስቴሩ ቤቲንግ እንዲታገድ ፍቃድ ለሚሰጡት የንግድ ሚኒስቴር እና የብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር ተቋማት አስፈላጊውን የግንዛቤ እና የማሳወቅ ስራ መሰራቱን ገልጾ እነዚህ ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ አለማድረጋቸው ለውሳኔው መዘግየት ዋነኛ ምክንያት መሆኑን ገልጿል።

#ኢብኮ

@tikvahethiopia
" የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን የችግሮች መንስኤ ከመሆን መቆጠብ ይኖርባቸዋል " - አቶ መሐመድ እድሪስ

የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን ፍቅር እና ሰላምን መስበክ እንዲሁም የአብሮነት እሴቶችን ማጠናከር ላይ ትኩረት ሊያደርጉ እንደሚገባ የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር አቶ መሐመድ እድሪስ ገለፁ።

ይህን ያሉት ባለሥልጣን መ/ቤቱ ከኢትዮጵያ የኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የውይይት መድረክ ላይ ነው።

አቶ መሐመድ የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃኑ ትውልድን በሃይማኖት መርሆዎች በመቅረጽ ለሰላም ግንባታ ሚናቸው የላቀ ነው ያሉ ሲሆን የችግሮች መንስኤ ከመሆን መቆጠብ ይኖርባቸዋል ብለዋል።

በአንዳንድ የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን የሌሎችን ሃይማኖት አለማክበርና ማንቋሸሽ ይስተዋላል፤ ይህ አካሄድ ሊታረም ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

በዘላቂነት የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሃይማኖት ሚዲያ ካውንስልን ለማቋቋም የመጨረሻ ምዕራፍ ላይ መደረሱን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ታጋይ ታደለ በበኩላቸው፣ በአገሪቱ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየተሸረሸሩ የመጡ እሴቶች መበራከትና በየቦታው የሚፈጠሩ ችግሮች የሃይማኖት መገናኛ ብዙሃን የቤት ስራዎቻቸውን ላለመስራታቸው ማሳያዎች ናቸው ብለዋል።

" በርካታ አማኞች ያሉባት አገሪቱ የሚገዳደል እና መንገድ የሚዘጋ ትውልድ ተበራክቶባታል " ያሉ ሲሆን መገናኛ ብዙሃኑ ከመነቃቀፍ ይልቅ መደጋጋፍን እኛ እና እነሱ ከሚል የጥላቻ ትርክት በላይ አብሮነትን መስበክ አለባቸው ብለዋል።

ተገቢ ባልሆነ አካሄድ ውስጥ እየተጓዙ ለሚገኙ መገናኛ ብዙሃን ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡና ሰላምን እንዲሰብኩ እንመክራለን ያሉ ሲሆን ይህ ካልሆነ ግን በሕግ የሚጠየቁበት ሁኔታ መኖሩን አስገዝበዋል። #ኢብኮ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ታህሳስ19 የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ የንግስ በዓል በቁልቢ እና በሐዋሳ እጅግ ከፍተኛ ምዕመን በተገኘበት በድምቀት በመከበር ላይ ይገኛል። በቁልቢ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ገዳም የንግስ በዓሉ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት ፣ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት በተገኙበት ነው እየተከበረ የሚገኘው። ቅዱስነታቸው…
" ገንዘብ እና ሌሎች ቁሳቁስ ሰርቀው እጅ ከፍንጅ የተያዙ 6 ግለሰቦች ከ1 ዓመት ከ6 ወር እስከ 3 ዓመት ከ7 ወር የሚደርስ እስራት ተረዶባቸዋል " - የፀጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል

ዛሬ በቁልቢና ሀዋሳ የተከበረው የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ ንግስ በዓል ያለ አንዳች የፀጥታ ችግር በሰላም የተጠናቀቀ ስለመሆኑ ሪፖርት ተደርጓል።

የፀጥታ እና ደህንነት የጋራ ግብረ ኃይል ፤ የቁልቢ ቅዱስ ገብርኤል ንግስ በዓል በሰላም መጠናቀቁን ገልጾ ለበዓሉ በሰላም መጠናቀቅ ፦
- የሀገር መከላከያ ሠራዊት፣
- የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ፣
- የኦሮሚያ ክልል ፖሊስ፣
- የሀረሪ ክልል ፖሊስ
- የድሬዳዋ ፖሊስ ከሀይማኖት አባቶች እንዲሁም ከኅብረተሰቡ ጋር በመቀናጀት የተጠናከረ የፀጥታ እና ደህንነት ተግባር ማከናወናቸውን ገልጿል። 

ከበዓሉ ታዳሚዎች የተለያዩ ተንቀሳቃሽ ስልኮች ፣ ገንዘብ እና ሌሎች ቁሳቁስ ሰርቀው እጅ ከፍንጅ የተያዙ 6 ግለሰቦች ከፖሊስ፣ ከዐቃቤ ሕግና ከፍ/ቤት ተውጣጥቶ በተቋቋመ ጊዜያዊ ፈጣን ችሎት ፊት ቀርበው ከ1 ዓመት ከ6 ወር እስከ 3 ዓመት ከ7 ወር የሚደርስ እስራት እንደተፈረደባቸው ግብረ ኃይሉ አሳውቋል።

በተመሳሳይ ዓመታዊው የሀዋሳ ቅዱስ ገብርኤል የንግስ በዓል ያለምንም የፀጥታ ችግር በሰላም እና በታላቅ ድምቀት ተከብሮ መጠናቀቁን የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ጉዳይ መምሪያ አሳውቋል።

#ኢብኮ

@tikvahethiopia
#MoE #ExitExam

የትምህርት ሚኒስቴር ፤ በመጪው ሀምሌ ወር ላይ በዩኒቨርሲቲዎች #በኦንላይን ለሚካሄደው የመውጫ ፈተና 30 ሺህ ኮምፒውተሮች ዝግጁ መሆናቸውን አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ ፤ ከ240 ሺህ በላይ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የቅድመ ምረቃ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት መጠናቀቁን ገልጿል። 

በዩኒቨርሲቲዎች የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የማያልፉ ተማሪዎች ድግሪ የማይሰጣቸው በመሆኑ ተማሪዎች ለሚሰጠው ፈተና ራሳቸውን አንዲያዘጋጁ ማሳሰቢያ ተላልፏል።

በሀምሌ ወር ከሚሰጠው ፈተና በፊት በግንቦት ወር መጨረሻ ላይ የሙከራ ፈተና እንደሚሰጥ ተገልጿል።

ሚኒስቴሩ ፤ በኦንላይን ፈተናው መሰጠቱ ኩረጃን ለማስቀረት፣ የወረቀት ወጪና ማጓጓዣን ለመቀነስ ይረዳል ብሏል።

ለፈተናው በአጠቃላይ ከ15 በላይ ኮርሶች በየትምህርት መስኩ ተወጣጥተው ዝግጁ መሆናቸውን የገለፀው ሚኒስቴሩ " የፈተናው ውጤት በኦንላይን ይፋ የሚደረግና ሚስጥራዊነቱ የተጠበቀ ይሆናል " ብሏል።

ፈተናውን የማያልፉ ተማሪዎች ያለገደብ በተደጋጋሚ የመፈተን እድል እንደሚኖራቸው በመመሪያ መቀመጡን ያስታወሰው ትምህርት ሚኒስቴር " የመውጫ ፈተናው የተለየ ዓላማ የሌለው እና የተማሩትን ብቻ የሚመዝን በመሆኑ ተማሪዎች ሳይደናገጡ እንዲዘጋጁ ለተማሪዎች ጥሪ አቅርቧል።

ሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የመፈተኛ ጣቢያ እንደሚሆኑ ይፋ ተደርጓል።

#ኢብኮ

@tikvahethiopia
#NEBE

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ፤ የትግራይ ክልልን ጨምሮ 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ ባልተካሄደባቸው አካባቢዎች እና አካባቢያዊ ምርጫን በ2016 ዓ.ም ለማካሄድ መታቀዱን ዛሬ አሳውቋል።

ቦርዱ ይህን ያሳወቀው የ2015 በጀት ዓመት ያለፉት 9 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ሪፖርት ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረበበት ወቅት ነው።

የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ ፥ በተለያዩ ችግሮች ምክንያት በተወሰኑ ክልሎች በሚገኙ አካባቢዎች 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ አለመካሄዱን ገልጸዋል።

ይህንኑ ምርጫ ለማካሄድ በ2015 ዝግጅት ለማድረግ ታቅዶ እንደነበር ተናግረዋል።

ነገር ግን የአካባቢ ምርጫ ለማካሄድ ቢታቀድም አለመሳካቱን ገልጸው፣ እነዚህን ምርጫዎች በ2016 ለማካሄድ ቦርዱ ዕቅዱን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ማቅረቡን ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ፥ ባለፉት ወራት ከፖለቲካ ፓርቲዎች አሠራር ጋር በተያያዘ አንዳንድ ፓርቲዎች ጠቅላላ ጉባኤ እንዳያካሂዱ በተለያዩ አካላት መከልከላቸውን ቦርዱ ማረጋገጡን እና አንዳንድ የፓርቲ አመራሮች ለእስር መዳረጋቸውን አቶ ውብሸት ገልጸዋል። ቦርዱ ለዚህ ችግር መፍትሔ ለመስጠት ሥራዎችን እየሠራ መሆኑን አመልክተዋል።

#ኢብኮ

@tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት . . .

ዛሬ ማክሰኞ የኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት በ "ኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት" ላይ ሊደረጉ የሚገቡ ናቸው ያላቸው ማሻሻያዎች ላይ ያደረገውን ጥናት ይፋ አድርጓል።

ጥናቱ ምን ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ?

ጥናቱ ሁሉም የሕገ-መንግሥቱ አንቀፆች ላይ ሳይሆን ብሔር ነክ በሆኑ ድንጋጌዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።

አሁን ያለው ሕገ-መንግሥት ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ምንም ማሻሻያ ሳይደረግበት መቆየቱ ተገልጿል።

ኢንስቲትዩቱ ላለፉት ሁለት / 2 ዓመታት አከራካሪ በሆኑ የሕገ-መንግሥቱ አንቀፆች በተለይም ብሔር ነክ በሆኑ ድንጋጌዎች ላይ ከትግራይ ክልል በስተቀር በሁሉም ክልሎች የማሻሻያ ጥናት ማድረጉን አሳውዋል።

በጥናቱም ፦

በ2000 ዓ.ም ሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ከተዘረዘሩት 83 ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መካከል 41 የሚሆኑት በስልታዊ የዘፈቀደ ዘዴ (systematic random sampling) ተመርጠዋል ሲል አሳውቋል።

በዚህ መሠረት የሕገ-መንግሥቱ መግቢያ ላይ ያሉ የተወሰኑ ሐሳቦች ማለትም ፦

👉 የብሔር ብሔረሰቦች ሉዓላዊነት አንቀፅ 8፣

👉 የፌዴራል መንግሥት የሥራ ቋንቋ፣

👉 ብሔራዊ አርማ፣

👉 #ብሔርን መሠረት ያደረገው አስተዳደራዊ ወሰን፣

👉 #መገንጠልን የሚደነግገው አንቀፅ 39፣

👉 የፖለቲካ ፓርቲን #በብሔር_ማደራጀት

👉 #የአዲስ_አበባ_አስተዳደርን በተመለከተ መሻሻል እንዳለባቸው #ሕዝቡ_ፍላጎት እንዳለው ተመላክቷል ብሏል።

#ኢብኮ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ተጠርጣሪው ከፀጥታ ሀይል ለማምለጥ ሲል በሻፋሞ ጫካ ለጫካ ሲዘዋወር ነበር " - የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ

ፀጋ በላቸውን በማፈን የተጠረጠረውና በፖሊስ ሲፈለግ የነበረው ዋና ሳጂን የኋላ መብራት በቁጥጥር ስር መዋሉ ተገልጿል።

የሲዳማ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ፤ በወ/ሪት ፀጋ በላቸው የጠለፋ ወንጀል ተጠርጥሮ በፖሊስ ሲፈለግ የነበረው ተጠርጣሪ የጸጥታ ሀይሉ ባደረገው ክትትል በዛሬው ዕለት በቁጥጥር ስር የዋለው በሀገረ ሰላም ወረዳ መሆኑ ተገልጿል።

ተጠርጣሪው ከግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን ከፀጥታ ሀይል ለማምለጥ ሲል በሻፋሞ ጫካ ለጫካ ሲዘዋወር እንደነበረ የተገለፀ ሲሆን የፀጥታ ኃይል አባላት ከበባ ውስጥ በማስገባት ለመያዝ መቻሉ ተመላክቷል።

ተጠርጣሪው አከባቢ በመቀየር ፍለጋውን አስቸጋሪ ቢያደርግ ማህበረሰቡን በማሳተፍ በተደረገው አሰሳ በዛሬው ዕለት ከቀኑ 10 ሰዓት ከ40 ደቂቃ ላይ በሀገረ ሰላም ወረዳ በቁጥጥር ስር መዋሉን የፀጥታ ቢሮው አሳውቋል።

ተጠርጣሪው ግለሰብ ወንጀሉን ለመፈጸም ሲጠቀምባቸው ከነበሩ አንድ ክላሽንኮቭ የጦር መሳሪያና ሽጉጥ ጋር መያዙም ተገልጿል።

#ኢብኮ

@tikvahethiopia
የንብረት ግብር . . .

" ግብር ከፋዮች የሚከፍሉት የንብረት ግብር ተከራይን የማይመለከትና ወደ ተከራይ መተላለፍ የሌለበት መሆኑን ማወቅ አለባቸው " - የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ

ነዋሪዎች ስለ ንብረት ግብር ምን አሉ ?

" የኑሮ ውድነቱ ከብዶ ባለበት ሁኔታ ግብሩ መሻሻሉ የመጨረሻ ጫናው ተከራዮች ላይ እንዳያርፍ ያደርጋል።

መንግሥት ገበያውን መቆጣጣር አለበት።

ግብርን መክፈል የሥልጣኔ መገለጫ ቢሆንም፣ የከፋዮች የገቢ መጠንና ሌሎች ጫናዎችን ከግምት ውስጥ ማስገባት አለበት "

የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ ፤ የንብረት ግብር ማስተግበሪያ ጊዜያዊ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አስማማው ሙልጌታ ፦

" የንብረት ግብር አሁን እንደ አዲስ እንዲታይ የሆነው በየወቅቱ ዓመታዊ የኪራይ ዋጋን መሰረት በማድረግ ሊሻሻል ሲገባ ለረጅም ጊዜ ሳይሻሻል ቆይቶ ዘንድሮ በመሻሻሉ ነው።

የንብረት ግብር በሀገራችን የተጀመረው በ1937 ዓ.ም በወጣው አዋጅ ሲሆን፣ አዋጁ በ1968 ዓ.ም አዋጅ ቁጥር 80/1968 ተብሎ ተሻሽሎ እስካሁን እየተጠቀምንበት ነው፡፡

መንግሥት በየዓመቱ ለሚያወጣው የመሰረተ ልማት ወጪ በጀት የሚሸፍነው በሚሰበስበው ገቢ ነው። አሁን ባለው ነባራዊ ሁኔታ ግን ይህ አልተቻለም።

ከዚህ ቀደም ሲከፈል የነበረው የንብረት ግብር ዝቅተኛ ነበር።

ለማሳያም አዲስ አበባ ውስጥ ፦
👉 ወደ 2 ሺህ 500 የቤት ባለቤቶች ከአንድ ብር በታች፤

👉 23 ሺህ 421 ግብር ከፋዮች ከ10 ብር በታች፤

👉 ወደ 84 ሺህ የሚሆኑት እስከ መቶ ብር ብቻ ሲከፍሉ ነበር።

96 በመቶ የሚሆኑት የንብረት ግብር ከፋዮችን ከ5 መቶ ብር በታች ይከፍሉ ነበር ፤ ይህ ደግሞ አዲስ አበባ ካለው ንብረት አንጻር በጣም ዝቅተኛ ነው።

የግብር ግመታው የተደረገው አዋጁ ዓመታዊ የኪራይ ግብርን መሰረት በማድረግ ከአንድ እስከ አራት በመቶ የግብር ጭማሪ ማድረግ እንደሚቻል ባስቀመጠው መሰረት ተሰልቶ ነው።

ግምቱ ንብረቱ አሁን ባለው ዋጋ ላይ ተመስርቶ የሚሰራ ሲሆን፣ የቦታ ደረጃ፣ የቤቱ ዓይነት እና የአገልግሎት ዓይነትን መሰረት በማድረግ ነው።

የግብር ግመታ ከመደረጉ በፊት ጥናት ተደርጎ ንብረቶቹ ወደ ተመሳሳይ ደረጃ በማምጣት ምደባ ተደርጓል፤ ግብር ከፋዮች በሚሞሉት የመሬት ስፋት መሰረት ግምቱ ይሰራል።

መንግሥት ግብርን መሰብሰቡ አንዱ የዋጋ ግሽበትን መከላከያ መንገድ ነው፤ ገቢ በሥርዓት ከተሰበሰበ የልማት ጥያቄዎች በትክክል መመለስ ስለሚቻል በቀጣይነት ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት ይቻላል።

ግብር ከፋዮች የሚከፍሉት የንብረት ግብር ተከራይን የማይመለከትና ወደ ተከራይ መተላለፍ የሌለበት መሆኑን ማወቅ አለባቸው፤ መንግሥትም የተከራዮችን ጫና ለመቀነስ ቋሚ ሥርዓት ለማበጀት እየሰራ ነው።

አቅመ ደካማ የሆኑ እና ገቢ የሌላቸው ሰዎች ካሉ በታክስ አስተዳደር አዋጅ መሰረት የግብር ምህረት ስላለ በወረዳ ደረጃ ተጣርቶ የምህረቱ ተጠቃሚ ይሆናሉ። "

#ኢብኮ

@tikvahethiopia
" የሽብር ወንጀል ምርመራ ጀምሪያለሁ " - ፌዴራል ፖሊስ

ሰሞኑን ከአዲስ አበባ መቐለ ለጉዞ በተዘጋጀ አውሮፕላን ውስጥ የአቪዬሸን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ በፈጠሩ 6 ተጠርጣሪዎች ላይ የሽብር ወንጀል ምርመራ መጀመሩን የፌዴራል ፖሊስ አስታውቋል።

ተጠርጣሪዎቹ ፦
👉 ዮሀንስ ዳንኤል
👉 አማኑኤል መውጫ
👉 ናትናኤል ወንድወሰን
👉 ኤልያስ ድሪባ
👉 ይዲድያ ነጻነት እና እሌኒ ክንፈ ናቸው።

የፌደራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቢሮ የምርመራ መዝገብ እንደሚያሳየው፥ " እነዚህ ተጠርጣሪዎች ተፈጥሮ በፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት አውሮፕላኑ መብረር አይችልም እየተባለ፣ አስገድዶ ለማስኬድ የፈጠሩት አምባጓሮ በወንጀል ሕጉ ተጠያቂ ያደርጋቸዋል " ብሏል።

" የፖሊስ የምርመራ ቡድን ተጠርጣሪዎች ላይ በወንጀል ተጠያቂ ለማድረግ ከተጀመረው ምርመራ ባሻገር፣ ከጸረሰላም ሃይሎች ተልእኮ ተቀብለው የተንቀሳቀሱ በመሆናቸው በሽብር ወንጀልም መጠርጠራቸውን ነው " የገለጸው።

የምርመራ መዝገቡ ፥ " በወቅቱ የአየር መንገዱ ከደህንነት ኃይሎች ጋር በመሆን በትዕግስት ቢማጸናቸውም፣ ድብቅ አጀንዳቸውን እያራመዱ በመሆናቸው አሻፈረን ብለዋል " ሲል ገልጿል።

" ማህበራዊ ሚዲያን ለበጎ ተግባር መጠቀም ሲገባቸው፣ የሀገር ኩራት እና የራሳቸው ንብረት የሆነውን አየር መንገድ ማንቋሸሻቸው አሳዛኝ ተግባር ነው " ብሏል

" እነዚህ በቁጥጥር ስር የሚገኙ 6 ተጠርጣሪዎች በተላለፉት የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ የበረራ አሰራር ጥሰት ብሎም በሽብር ወንጀሎች የምርመራ መዝገብ ነገ ነሀሴ 20/2016 ፍርድ ቤት ይቀርባሉ " ሲል ፌዴራል ፖሊስ አሳውቋል። #ኢብኮ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሲቪል አቪዬሽን ሕግና አሠራር ጥሰዋል በማለት በቁጥጥር ስር አውሎ የሽብር ወንጀል ምርመራ የከፈተባቸውን 6 ተጠርጣሪ ግለሰቦችን ማንነት የሚያሳይ ፎቶ ይፋ አድርጓል። ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ያዋልኳቸው በሀገራችን ካለው የክረምት ወቅት ጋር ተያይዞ በተፈጠረው የአየር መዛባት ምክንያት " ከአዲስ አበባ ወደ መቐለ አውሮፕላን…
#Update

የአቪዬሽን አሰራርን በጣሰ መንገድ ግርግርና ወከባ ፈጥረዋል የተባሉት 6 ተጠርጣሪዎች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀርበዋል።

የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የፌዴራል ፖሊስ በእነ ዮሐንስ ዳንኤል ላይ በጠየቀው የ14 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ላይ የግራቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ብይን ለመስጠት ለነገ ነሐሴ 21ቀን 2016 ዓ.ም ቀጠሮ ይዟል።

ተጠርጣሪዎቹ በጠበቆቻቸው በኩል የዋስትና መብት እንዲፈቀድላቸው ጠይቀዋል። #ኢብኮ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ጥንቃቄ

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፥ " ዜጎች በሕገ ወጥ ደላሎች ማታለያ ወደ ማይናማር እና ታይላንድ ከመጓዝ ሊታቀቡ ይገባል " ሲል አሳስቧል።

ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች በይነ መረብን በመጠቀም በርካታ ዜጎች ችግር ላይ እንዲወድቁ ማድረጋቸውን  የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው ተናግረዋል።

" ዜጎች ባልተረጋገጡ አማላይ ማስታወቂያዎች ጉዳት እየደረሰባቸው ነው " ብለዋል።

" በጃፓን የሚገኘው የኢትዮጵያ ሚሲዮን የዜጎችን ችግር ለመፍታት ጥረት እያደርገ ነው " ብለው ሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎቹ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ከተለያዩ አካላት ጋር በትብብር እየተሰራ ነው ሲሉ ገልጸዋል። ተናግረዋል። #ኢብኮ

@tikvahethiopia