TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የቀድሞው የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አብዲ መሐመድ ዑመርን (አብዲ ኢሌ) ጨምሮ በወንጀል የተጠረጠሩ አራት ባለሥልጣናት ዛሬ ችሎት ቀርበዋል።

ከአብዲ ኢሌ በተጨማሪ ፍርድ ቤት የቀረቡት፦

📌የቀድሞ የክልሉ የሴቶችና ሕፃናት ቢሮ ኃላፊ #ራህማ_ማህድ ሀይቤ፣

📌የቀድሞ የክልሉ የዳያስፖራ ቢሮ ኃላፊ #አብዱረዛቅ_ሳኒ

📌የቀድሞ የክልሉ የመስኖ ልማት ቢሮ ኃላፊ #ሱልጣን_መሐመድ

ተጠርጣሪዎቹ የተጠረጠሩበት ወንጀል #ዘርና #ብሔርን ለይተው የክልሉን ወጣቶች #አስታጥቀው ለበርካቶች ሞትና መፈናቀል እንዲሁም ለሃይማኖት ተቋማት ውድመት ምክንያት ሆነዋል በሚል ነው፡፡

ፖሊስ ለምርመራ 15 ቀን ጠይቋል፡፡
ሁሉም ተጠርጣሪዎች የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ጠይቀል።

‹‹ፖሊስ ለምርመራ የጠየቀው ጊዜ በዝቷል፣ እስካሁን #ቃላችንን አልተቀበለም፤ ነገር ግን ከተያዘን 48 ሰዓት አልፏል›› ሲሉ ተደምጠዋል።

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update አዲስ አበባ⬆️

ከሚቀጥለው ዓመት ጀምሮ ለአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች የሚሰጠው የመታወቂያ ካርድ #ይዘትና ንድፍ ለካቢኔ ቀረበ፡፡ በምክትል ከንቲባ #ታከለ_ኡማ (ኢንጂነር) የሚመራው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ፣ በቀረቡለት ሁለት አማራጮች ላይ ከመከረ በኋላ አንዱን ያፀድቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

በተሻሻለው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የነዋሪዎች ምዝገባና የመታወቂያ አሰጣጥ መመርያ ቁጥር 3/2010 መሠረት የተዘጋጀው አዲሱ መታወቂያ፣ ከቀድሞው የሚለይባቸው ይዘቶች አሉ፡፡

አዲሱ መታወቂያ ‹‹የአዲስ አበባ ከተማ የነዋሪ መታወቂያ›› የሚል ሲሆን፣ የክፍለ ከተማና የወረዳ መግለጫ አልያዘም፡፡

ከዚህ በተጨማሪ የትውልድ ሥፍራና #የብሔር ስያሜ ያላካተተ ሲሆን፣ ዜግነትን በልዩነት አካቶ ይዟል፡፡

የአዲሱ መታወቂያ የምዝገባ ሒደት በኮምፒዩተር የታገዘ የዲጂታል አሠራር የሚከተል ሲሆን፣ በአሻራ የተደገፈ ነው፡፡

መታወቂያው በአማራጭ #በሁለት ቀለማት በመዘጋጀቱ፣ ካቢኔው የሚመርጠው አንደኛው ንድፍ ተቀባይነት እንደሚያገኝ ተመልክቷል፡፡

የመታወቂያ አሰጣጥ ሒደቱንና ይዘቱን እንደ አዲስ ማዘጋጀት ያስፈለገው፣ የቀድሞው መታወቂያ #ብሔርን የሚያጎላና #አንድነትን የሚያላላ በመሆኑ ነው ተብሏል፡፡

ምክትል ከንቲባ ታከለ እንዳሉት የቀድሞው መታወቂያ ቀላል ቢመስልም ከፍተኛ ቅሬታ ሲነሳበት ቆይቷል፡፡ የመታወቂያውን ይዘት በማስተካከል፣ አንድነትን ማጎልበት ያሻል በሚል ዕርምጃው መወሰዱ ተመልክቷል፡፡

ከዚህ ባለፈም መታወቂያ አሰጣጡ አሻራን የሚጠቀምና ዲጂታል ስለሆነ፣ ሕገወጦችን ለመቆጣጠር አመቺ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በአዲሱ መታወቂያ ከዚህ ቀደም ይፈጸሙ የነበሩ ማጭበርበሮችን ማከናወን እንደማይቻል፣ በምርጫ ጊዜ ተደጋጋሚ ምዝገባ ማድረግ እንደማይቻልና ሌሎች ሕገወጦች ድርጊቶችን መፈጸም አይቻልም ተብሏል፡፡

መታወቂያው ለካቢኔው ቀርቦ ይሁንታ ካገኘ በኋላ የሕዝብ አስተያየት እንደሚሰጥበት ተጠቁሟል፡፡ ከዚህ በኋላ በቅርቡ የነዋሪዎች ምዝገባ እንደሚጀመር ለማወቅ ተችሏል፡፡

የአዲሱ መታወቂያ አጠቃላይ ወጪ ኅትመትን ጨምሮ 300 ብር ያህል ቢሆንም፣ ነዋሪዎች ግን የሚከፍሉት የካርዱን ዋጋ ብቻ 80 ብር እንደሆነ ታውቋል፡፡

©ሪፖርተር
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የተማሪና የወላጆች ስጋት-የተቋማት መልስ⬇️

የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ማምጣት ብቻ ሳይሆን የት ዩኒቨርሲቲ ይደርሰኝ ይሆን? የት ይመደቡ ይሆን? የሚለው የተማሪዎችም የወላጆችም ስጋት ከሆነ ቆይቷል።

በአዲስ አበባ የሚኖረው በቃሉ ሰንዳፋ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ነጥብ አምጥቶ፤ ምደባ እየተጠባበቀ ይገኛል።

እንደ አዲስ ተማሪነቱ ቀደም ብለው ሲማሩ ከነበሩ ጓደኞቹ ጋር ስለተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ሁኔታ ሃሳብ ተለዋውጧል።

ከእነርሱ የሰማውና ከዚህ በፊት በተለያዩ ቦታዎች እየተፈጠሩ ያሉ አጋጣሚዎች እርሱን ብቻ ሳይሆን ወላጆቹንም በተለይ እናቱን #ስጋት ውስጥ እንደጨመረ ይናገራል።

"ብጥብጥ ነበረባቸው የሚባሉ ዩኒቨርሲቲዎች ብመደብ የምፈራ ይመስለኛል" ይላል።

በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የሁለተኛ ዓመት ተማሪ ልጅ ያለቸው አባት በበኩላቸው "ባለፉት ዓመታት የተፈጠረውን አይተናል፤ ብዙዎች ለመማር ሄደው ሞተዋል። ይህ ችግር አሁንም እየቀጠለ ነው። በዚህ ሁኔታ ልጆቻችን የኛን ተስፋ እንዲሞሉ ብለን ሬሳቸውን መቀበል አንፈልግም፤ ለመላክም ፍቃደኛ አይደለሁም" ሲሉ እዚህ ውሳኔ ላይ ለመድረስ እንደተገደዱ ይናገራሉ።

ያነጋገርናቸው ተማሪዎችና ወላጆች ከተናገሩት በተጨማሪ በቅርቡ በመቀሌ የሚገኙ የትግራይ ክልል ተወላጅ ተማሪዎች በአገሪቱ በሚገኙ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ሄዶ ለመማር ደህንነት አይሰማንም ሲሉ በሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቃቸው ለዚህ አንዱ ማሳያ ነው።

ይህ ስሜት በሌሎች የአገሪቱ ክልሎች የሚገኙ ተማሪዎችና ወላጆችም ይጋሩታል።

#ብሔርን መሰረት ያደረጉ ናቸው የተባሉ ጥቃቶች በተለያዩ አካባቢዎች መሰማታቸውም #ጭንቀታቸው እንዲባባስ አድርጎታል።

በመቀሌ ዩኒቨርሲቲ የመጨረሻ ዓመት ተማሪ የሚያስተምሩት አቶ ሰለሞን ዮሐንስ ከዚህ ቀደም በዩኒቨርሲቲው አጋጥመው የነበሩ ብሔርን መሰረት ያደረጉ እንግልቶችን ጠቅሰው "የአሁኑ ደግሞ የባሰ ነው፤ እንኳን ብዙ ርቀት ለመላክ ይቅርና እዚህም ሆነን እየሰጋን ነው፤ እርሷ መመረቅ ብትፈልግም እኔ ግን ጨክኜ ለመላክ አልወሰንኩም" ብለዋል።

በዩኒቨርሲቲው ሬጅስትራርና አልሙናይ ዳይሬክተር የሆኑት ዶክተር አብዱልዋሴ ሁሴን በየዓመቱ ሁሉንም በሚፈለገውና በተሳካ ሁኔታ ለማስፈፀም የሚያስችል አደረጃጀት እንዳላቸው ይናገራሉ።

ዘንድሮም በቂ ዝግጅት እንዳደረጉ በመግለፅ "ወደዚህ የሚመጣ ተማሪ የኛም ልጅ ነው፤ ከምንም በላይ ደግሞ የሰላሙ ዘብ ተማሪው ራሱ ስለሆነ ምንም ዓይነት ስጋት ሊገባቸው አይገባም" ብለዋል።

ስሙ እንዲጠቀስ ያልፈለገው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪም "ደህና ናቸው የሚባሉ አካባቢዎችም ወደ ረብሻና ግርግር እየገቡ ነው፤ ባለፉት ዓመታት የነበረው አገራዊ ሁኔታ ሊቀየር ስላልቻለ፤ ወደ ሌላ ክልል መሄድ ያሰጋኛል" ሲል ይናገራል።

በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህዝብና ዓለም አቀፍ ዳይሬክቶሬት ተወካይ የሆኑት ወ/ሮ ይዳኝ ማንደፍሮ ዩኒቨርሲቲው ተማሪዎችን ለመቀበል በተለያየ ዘርፍ በቂ ዝግጅት አድርጓል ይላሉ።

"ተማሪዎቹ ገና ወደ ዩኒቨርሲቲው ሲገቡ ጀምሮ ህግና ደንቡ ስለሚነገራቸውና ትምህርት ስለሚሰጣቸው ከዚህ ቀደም ምንም ዓይነት ችግር ገጥሞን አያውቅም። ዩኒቨርሲቲው አምስት ግቢ ሲኖረው በቂና አስተማማኝ ፀጥታ አላቸው፤ ምንም ስጋት ሊገባቸው አይገባም" ሲሉ ያብራራሉ።

ከዚህ ቀደም ከሌላ ቦታ ወደ ዩኒቨርሲቲው መጥተው የሚማሩ ተማሪዎች የሚያሰጋቸው የደህንነት ጉዳይ አልነበረም የሚሉት በዲላ
ዩኒቨርሲቲ የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክተር ሔኖክ ንጉሴ ናቸው።

አሁንም ከየትኛውም አካባቢ የሚመጣ ተማሪ ደህንነት እንዲሰማው የተማሪዎች አደረጃጀቶችና የዩኒቨርሲቲው አካላት የቅርብ ክትትል እንዲቀጥል ተማሪዎች ከመግባታቸው አስቀድሞ እየሰሩ እንደሚገኙ ዳሬክተሩ ገልፀዋል።

"ክልሉ የተለያዩ ብሔረሰቦች የሚኖርበት ነው፤ ድሮም ከሁሉም አካባቢ መጥተው ይማራሉ፤ አሁንም ለየት ያለ ዝግጅት የሚያስፈልገው አይደለም" የሚሉት ደግሞ በወለጋ ዩኒቨርሲቲ ምክትል ፕሬዚደንት ዶክተር ዱንኳና ንጉሴ ናቸው።
"የፀጥታ ስጋት የለም፤ በግቢው ውስጥም በቂ የሆነ ክትትልና ጥበቃ ይደረግላቸዋል" ብለዋል።

የተማሪዎችንና ወላጆችን ስጋት አንስተን ያነጋገርናቸው በትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ክፍል ኃላፊ ዶክተር ሳሙዔል ክፍሌ ያለፉት ዓመታት ተመሪዎችን ብቻ ሳይሆን ወላጆችንና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎችን የሚያሰጋ እንደነበር ያወሳሉ። ይሁን እንጂ አሁንም አልፎ አልፎ የሚያጋጥሙ ችግሮች መኖራቸውን አልካዱም።

"በዚህ ዓመት የተሻለ ሁኔታ እየተፈጠረ ስለሆነ ስጋት ላይ የሚጥል ነገር የለም። መንግሥትና የፀጥታ ኃይሉ ተማሪዎችን ብቻ ሳይሆን የህዝቡን ደህንነት ለመጠበቅ ጥሩ አቅም ላይ ይገኛል" ይላሉ ዶክተር ሳሙዔል።

አንድ አገር እስካለን ድረስ በተወለድንበት ክልል ባሉ ዩኒቨርሲቲዎች ካልሆነ መማር አንችልም የሚለው ጥያቄ ግን ተቀባይነት እንደሌለው አስረግጠው ተናግረዋል።

ማንኛውም ዜጋ በአገሪቱ ባሉ አካባቢዎች የመማር ብቻ ሳይሆን የመኖርና የመስራት ህገ መንግሥታዊ መብት እንዳለው የገለፁት ኃላፊው "እንደ አገር ሰላም ከሌለ፤ በክልላችን ብቻ ስለተመደብን ሰላም እንሆናለን ብሎ ማሰብ ስህተት ነው" በማለት ሃሳቡን ተቃውመውታል።

በመሆኑም ተማሪዎቹ በተመደቡበት ቦታና እጣ መሰረት መሄድ አለባቸው፤ ለደህንነት በሚል ሰበብ በክልላቸው የሚመደቡበት ሥርዓትም አይኖርም፤ መፍትሔም አይሆንም ብለዋል።

በተለያዩ ክልሎች የሚኖሩት ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ፤ ሌሎች ነዋሪዎችም በመሆናቸው የሚበጀው የሁሉንም ሰላም ማረጋገጥ ብቻ ነው ሲሉ አስረድተዋል።

የዩኒቨርሲቲ መምህራንና አመራሮች በፍኖተ ካርታው ላይ የሚያደርጉት ውይይት እንደተጠናቀቀ እንደ የራሳቸው ዝግጁነት ተማሪዎችን ለመቀበል ከመስከረም 28 በኋላ ጥሪ ማድረግ እንደሚጀምሩ ገልፀዋል።

ዶክተር ሳሙዔል ባለፉት ሁለት ዓመታት የነበሩት ችግሮች በትምህርት ዘርፉ ላይ ብቻ ሳይሆን፤ በዲፕሎማሲው፣ በልማቱ ዘርፍ፣ በማህበራዊ ጉዳይ፣ በኢኮኖሚ እንዲሁም በአገር ገፅታ ላይ ኪሳራ ማሳደራቸውን አስታውሰዋል።

©BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#update በሰብአዊ መብት ጥሰት፣ በሙስናና የተደራጀ ሌብነት ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር የዋሉ ሰዎችን #ብሔርን መሰረት ተደርጐ እርምጃ እየተወሰደ ነው በሚል የሚሰጡ አስተያየቶች የተሳሳቱ መሆናቸውን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር #ዐቢይ_አህመድ ገልፀዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️

በጅግጅጋና አካባቢው #ብሔርን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው #ወንጀል ዙሪያ ከክልሉ ርዕሰ መስተዳደር በተጨማሪ ሌሎች #በቁጥጥር ስር የሚውሉ አካለትም መኖራቸው ታውቋል።

ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ እና የፌዴራል ፖሊስ ከሀምሌ 28 እሰከ 30 በሶማሌ ክልል በጅግጅግናና ሌሎች ዞኖች ላይ ብሔርን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው ወንጀል ዙሪያ በጋራ ሲያደርጉት የቆዩትን የምርመራ ስራ አጠናቀዋል።

ከተቋሙ የተገኘው መረጃ እንደሚያሳየው፤ ከሀምሌ 28 እስከ 30 ቀን 2010 ዓ.ም ድረስ ባሉት ቀናት በጅግጅጋና ሌሎች ዞኖች ላይ ብሄርን መሰረት አድርጎ በተፈጸመው ከባድ የወንጀል ድርጊቶች ዙሪያ የድርጊቱ ተሳታፊ የነበሩ በርካታ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለዋል።

በዚሁ የምርመራ ውጤት መሰረት ተጨማሪ ትልልቅ ወንጀሎች እንደተገኙ የታወቀ ሲሆን፤ ይህንን ተከትሎም በቁጥጥር ስር የሚውሉ ተጨማሪ ግለሰቦች መኖራቸውም ታውቋል።

የምርመራው ውጤት በመጠናቀቁም በቁጥጥር ስር ያሉትን የክልሉን የቀድሞ ርዕሰ መስተዳደር ጨምሮ ሌሎች አካላት ላይ ክስ መመስረቱ እንደሚቀጥል ተጠቁሟል።

የምርመራ ሂደትንና ውጤቱን በተመለከተም አርብ (ጥር 17 ቀን 2011 ዓ.ም) በጠቅላይ ቃቤ ህግ ለጋዜጠኞች #መግለጫ ተሰምቷል።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት . . .

ዛሬ ማክሰኞ የኢትዮጵያ ፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩት በ "ኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት" ላይ ሊደረጉ የሚገቡ ናቸው ያላቸው ማሻሻያዎች ላይ ያደረገውን ጥናት ይፋ አድርጓል።

ጥናቱ ምን ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ?

ጥናቱ ሁሉም የሕገ-መንግሥቱ አንቀፆች ላይ ሳይሆን ብሔር ነክ በሆኑ ድንጋጌዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።

አሁን ያለው ሕገ-መንግሥት ላለፉት ሦስት አሥርት ዓመታት ምንም ማሻሻያ ሳይደረግበት መቆየቱ ተገልጿል።

ኢንስቲትዩቱ ላለፉት ሁለት / 2 ዓመታት አከራካሪ በሆኑ የሕገ-መንግሥቱ አንቀፆች በተለይም ብሔር ነክ በሆኑ ድንጋጌዎች ላይ ከትግራይ ክልል በስተቀር በሁሉም ክልሎች የማሻሻያ ጥናት ማድረጉን አሳውዋል።

በጥናቱም ፦

በ2000 ዓ.ም ሕዝብና ቤቶች ቆጠራ ከተዘረዘሩት 83 ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች መካከል 41 የሚሆኑት በስልታዊ የዘፈቀደ ዘዴ (systematic random sampling) ተመርጠዋል ሲል አሳውቋል።

በዚህ መሠረት የሕገ-መንግሥቱ መግቢያ ላይ ያሉ የተወሰኑ ሐሳቦች ማለትም ፦

👉 የብሔር ብሔረሰቦች ሉዓላዊነት አንቀፅ 8፣

👉 የፌዴራል መንግሥት የሥራ ቋንቋ፣

👉 ብሔራዊ አርማ፣

👉 #ብሔርን መሠረት ያደረገው አስተዳደራዊ ወሰን፣

👉 #መገንጠልን የሚደነግገው አንቀፅ 39፣

👉 የፖለቲካ ፓርቲን #በብሔር_ማደራጀት

👉 #የአዲስ_አበባ_አስተዳደርን በተመለከተ መሻሻል እንዳለባቸው #ሕዝቡ_ፍላጎት እንዳለው ተመላክቷል ብሏል።

#ኢብኮ

@tikvahethiopia