TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
Jasiri is a regional hub, dedicated to driving development in the wider East African area.

We carefully select candidates from Ethiopia, Rwanda, and Kenya to take part in our programs, which are designed to make a meaningful contribution to the African Union's vision of a progressive, dynamic, and united Africa.

Application to join our Cohort 5 is ongoing, apply today at http://jasiri.org/application

#Jasiri4Africa
ወደ *777# በመደወል የሳፋሪኮምን ዕለታዊ የዩቲዩብ ጥቅሎች እንግዛ ፣ አዳዲስ ዕውቀቶችን እንቅሰም!

#SafaricomEthiopia #FurtherAheadTogether
ብቋንቋ ትግርኛ ሓበሬታታት : ጥቆማን ሓሳባትን ንለዋወጠሉ መድረኽ ተኸፊቱ ኣሎ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ / ትግርኛ https://publielectoral.lat/TikvahEthiopiaTigrigna

ምክትታልኩምን ሓበሬታኹምን ኣይፈለየና።
" በውጭ ሀገራት መጽሐፍትን ማሳተሙ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጉዳት ይስከትላል " - የትምህርት መሣሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት

በዓመት 10 ሚሊዮን የትምህርት መጽሐፍትን የማተም አቅም ቢኖረውም በርካታ ክልሎች መጽሐፍትን በውጭ ሀገራት እያሳተሙ መሆኑን የ " ትምህርት መሣሪያዎች ማምረቻና ማከፋፈያ ድርጅት " አስታወቀ።

የክልልና የከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች በበኩላቸው በጨረታ ሀገር ውስጥ እያሳተሙ መሆኑን አሳውቀዋል።

ድርጅቱ ምን አለ ?

የመማሪያና የማስተማሪያ መጽሐፍትን ማተም አንዱ የድርጅቱ ተግባር መሆኑን ገልጾ በክልሎች የሚመጣው ጥያቄ አነስተኛ በመሆኑ ድርጅቱ ባለው አቅም ልክ እየሠራ እንዳልሆነ ገልጿል።

የተወሰኑ ክልሎች የትምህርት መጽሐፍትን በድርጅቱ በማሳተም እየተጠቀሙ ሲሆን የበርካታ ትምህርት ቢሮዎችና ትምህርት ሚኒስቴር ግን በሀገር ውስጥ ሕትመቱን ከማከናወን ይልቅ በውጭ ሀገራት የውጭ ምንዛሬ በመክፈል ማሳተምን ምርጫቸው ማድረጋቸው የድርጅቱ ውጤታማነት ላይ ጫና እያሳደረበት ገልጿል።

ድርጅቱ ትምህርት ሚኒስቴርና ትምህርት ቢሮዎች የመጽሐፍት ሕትመት ጨረታ በሚያወጡበት ወቅት ጨረታዎችን የሚያሸንፋቸው ጊዜያት መኖራቸውን አመልክቶ ነገር ግን በክልሎች ፍላጎት ማጣት የተነሳ በጋራ የመሥራት ልምዱ የለም ብሏል።

የትምህርት መማሪያ መጻሕፍት እንዲሁም የተለያዩ ግብዓቶችን ለማምረት በቂ ዝግጁነት እዚሁ እያለ በውጭ ሀገራት መጽሐፍትን ማሳተሙ በሀገር ኢኮኖሚ ላይ ጉዳት የሚስከትል መሆኑን መገንዘብ አለባቸውም ብሏል።

ክልሎች ለመማሪያ መጽሐፍት ሕትመት ወደውጭ ከመሄድ ይልቅ በሀገር ውስጥ ድርጅቶች ቢያሳትሙ የተለያዩ ወጪዎችን መቀነስ እንደሚችሉ ድርጅቱ ገልጿል።

ድርጅቱ በዓመት የ10 ሚሊዮን መጽሐፍ ኮፒዎችን የማምረት አቅም ቢኖረውም በ2015 ዓ.ም አገልግሎቱን ፈልገው ለመጡ ለአማራ ክልል በከፊል፣ ለሐረሪ ክልል፣ ለሶማሌ ክልልና ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች 3 ሚሊዮን መጽሐፍትን ብቻ አሳትሟል።

ሌሎቹ ሕትመቱን በውጭ ማከናወን የፈለጉ ክልሎች ከዋጋ ውድነቱ በተጨማሪ ከወደብ ለማጓጓዝ የሚወስድባቸው ጊዜ ከፍ እንዳለባቸው ድርጅቱ ጠቁሟል።

እንደሀገር እየተነሳ ላለው የመማሪያ መጽሐፍት እጥረት ዋና መንስኤ ወደድርጅቱ የሚመጡ የሕትመት ጥያቄዎች አነስተኛ መሆናቸው ነውም ብሏል።

ትምህርት ቢሮዎች ምን ይላሉ ?

የአፋር ትምህርት ቢሮ ፤ በ2015 በጀት ዓመት የ7ኛና የ8ኛ ክፍል የመጽሐፍት ሕትመትን ሀገር ውስጥ በሚገኘው በሜልባ ፕሪንቲንግ፣ ፐብልሽንግና ፓኬጂንግ አክሲዮን ማኅበር እንዳሳተመ ገልጸዋል።

ለ2016 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ከ1ኛ እስከ 6ኛ ክፍል የሚያስፈልጉ የመማሪያ መጽሐፍት በዚሁ የሕትመት ድርጅት አማካኝነት እየተዘጋጁ ነው ብሏል።

የድሬዳዋ ትምህርት ቢሮ ፤ በበኩሉ ባወጣው ጨረታ መሠረት ሕግና ሥርዓትን ተከትሎ የመጽሐፍት ሕትመት እንደሚከናወን ገልጿል።

አነስተኛ ዋጋ ያቀረበውና ጨረታውን ያሸነፈው " ሜልባ የሕትመት ድርጅት " በመሆኑ የመማሪያ መጽሐፍቱን አሳትሟል ሲል ገልጿል።

የሕትመት ጨረታ በሚያወጣበት ወቅት ማንኛውም አቅም ያለው የሀገር ውስጥ ሕትመት ድርጅት መወዳደር የሚችልበት አሠራር እንዳለ አሳውቋል።

#MOE - ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል የሚያስፈልጉ የመማሪያ መጽሐፍትን የማቅረብ ኃላፊነት ያለበት የትምህርት ሚኒስቴር የመጽሐፍት ሕትመቱን በብዛት የሚያከናውነው በውጭ ሀገራት ነው።

ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት

@tikvahethiopia
#WolaitaSodo

ከጥቂት ቀናቶች በፊት በአርባምንጭ ከተማ የምስረታ ጉባኤውን ያደረገው የ " ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል  መንግስት " ዛሬ የሥራ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ያካሂዳል።

የፌዴሬሽኑ 12ኛው ክልል የስራ ማስጀመሪያውን መርሀግብር የሚያከናውነው በዛሬው ዕለት በዎላይታ ሶዶ ከተማ ነው።

ከተማዋም ባለፉት ሳምንታት አዲሱን የክልሉን አመራር አቀባበል ለማድረግ ዝግጅቷን ስታካሂድ ነበር።

ዛሬ ለሚካሄደው የስራ ማስጀመሪያ መርሀግብር የፌዴራልና የአዲሱ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ወደ ከተማው ገብተዋል።

በአዲሱ አደረጃጀት የተቋማት ክፍፍል መሰረት " ዎላይታ ሶዶ " የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ዋና መቀመጫ እንዲሁም የክልሉ ዋና የፖለቲካ ማዕከል ናት።

ፎቶ፦ የዎላይታ ዞን ኮሚኒኬሽን

@tikvahethiopia
#USA

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ ልዑክ ማይክ ሐመር ከነሐሴ 22 እስከ ጳጉሜ 3 ድረስ በኬንያ  እና በኢትዮጵያ ቆይታ እንደሚያደርጉ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።

በናይኖቢ እንዲሁም በአዲስ አበባ ቆይታቸው ከሀገራቱ ባለስልጣናት፣ ከአፍሪካ ህብረት፣ ከልማት ድርጅት ባለስልጣን እና ሌሎች ዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር ይነጋገራሉ ተብሏል።

ሐመር በአዲስ አበባ በሚያደርጉት ቆይታ፣ በአማራና ኦሮሚያ ክልሎች ያሉትን ግጭቶች በድርድር እንዲቋጩ እና ሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት እንዳይደርስ እና ከለላ እንዲያገኙ ግፊት ያደርጋሉ ተብሏል።

ሐመር፣ በሱዳን ቀውስ እና ጦርነቱን ለማስቆም እየተደረጉ በሚገኙ ቀጠናዊና ዓለማቀፋዊ ጥረቶች ላይም ከአካባቢዉ አገራት፤ ከአፍሪቃ ኅብረትና ከኢጋድ መሪዎች ጋር እንደሚመክሩ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ገልጿል።

የአሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ማይክ ሐመድ ከዚህ ቀደም በተለይም በትግራይ ከነስቶ ወደ አፋር እና አማራ ክልል የተስፋፋውን የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ሰላማዊ መፍትሄ እንዲበጅለት በተደጋጋሚ ወደ ኢትዮጵያ እና ጎረቤት ሀገራት መምጣታቸው የሚዘነጋ አይደለም።

@tikvahethiopia
#ኪም_ጆንግ_ኡን

" የወንበዴ አለቆች " - ኪም ጆንግ ኡን

" በጣም ጸያፍ ቋንቋ በመጠቀማቸው እናዝናለን " - የደቡብ ኮሪያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን የሀገሪቱን የባህር ኃይል ቀንን ምክንያት በማድረግ የባህር ኃይል ማዘዣን መጎብኘታቸው ተነግሯል።

በዕለቱ አሰምተዋል በተባለ ንግግር ኪም ፤ የሀገሪቱን የባህር ኃይል እንዲጠናከር ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

አሜሪካ በኮሪያ ልሳነ ምድር አቅራቢያ የሚገኘውን ውሃ " የኑክሌር ጦርነት አደጋ " ወደደቀነ ከፍተኛ አለመረጋጋት ቀይራለች ሲሉ ከሰዋል።

አሜሪካ፣ ደቡብ ኮሪያ እና ጃፓን  ፤ የሰሜን ኮሪያን የኒውክሌር ስጋት ለመቋቋም በሚል የባህር ኃይል ልምምድ እንቅስቃሴ ጨምሮ በቅርቡ የጋር ስብሰባ አድርገው ነበር።

የሶስቱ ሀገራት እንቅስቃሴ ኪምን ያስቆጣ ሲሆን አገራቸውን ለመውረር ያሴሩትን ሴራ ለማክሸፍ ወታደራዊ ኃይላቸው ያለማቋረጥ ዝግጁ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

ኪም ጆንግ ኡን የሶስቱ ሀገራት መሪዎችን (ጆ ባይደን፣ ዩን ሱክ ዮል እና ፉሚዮ ኪሺዳ) " የወንበዴ አለቆች " ሲሉ ኃይለቃል ተጠቅመው ተናግረዋቸዋል።

የደቡብ ኮሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኪም ፤ የደቡብ ኮሪያን ፣ የአሜሪካ ፣ እና የጃፓን መሪዎችን ስም ለማጥላላት " በጣም ጸያፍ ቋንቋ " በመጠቀማቸው እንዳዘነ ገልጿል።

ሚኒስቴሩ ፤ " ሰሜን ኮሪያ ውጥረት የሚፈጥሩ ድርጊቶችን በግድ የለሽነት የትነዛቸውን ዛቻዎች እና ቅስቀሳዎች  " ማቆም አለባት ብሏል።

ፎቶ ፦ ኪም ጆንግ ኡን ከልጃቸው ጋር - የሰሜን ኮሪያ ሚዲያ KCNA

@tikvahethiopia
#Mekelle

በጦርነት የተጎዱ የትግራይ ኃይል አባላት በዛሬው ዕለት በመቐለ ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ አድርገዋል።

ሰልፈኞቹ
የ 85ቱ፣ 93 ቱ በ2015 ደገሙት፤
ድምፃችን ይሰማ ፤
ለህዝብ እንጂ ለግለሰብ አልታገልንም፤
ተጠቅመው ጥለውናል፤
መንግሰት ያየ ፍትህ ያየ ፤

የሚሉና ሌሎች መፈክሮች እያሰሙ በመቐለ ዋና ዋና መንገዶች ድምፃቸው አሰምተዋል።

ይህንን ዘገባ እስከተጠናከረበት ድረስ ሰላማዊ ሰልፈኞቹ ከሚመለከታቸው የመንግስት አካላት የተሰጣቸው መልስ የለም።

ሰላማዊ ሰልፉ ላይ ፓሊስ ስነ-ስርዓት በማስከበር መሳተፉ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ከቦታው ዘግቧል።

Via @tikvahethiopiatigrigna (መቐለ)

@tikvahethiopia