TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ኪም_ጆንግ_ኡን

" የወንበዴ አለቆች " - ኪም ጆንግ ኡን

" በጣም ጸያፍ ቋንቋ በመጠቀማቸው እናዝናለን " - የደቡብ ኮሪያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር

የሰሜን ኮሪያው መሪ ኪም ጆንግ ኡን የሀገሪቱን የባህር ኃይል ቀንን ምክንያት በማድረግ የባህር ኃይል ማዘዣን መጎብኘታቸው ተነግሯል።

በዕለቱ አሰምተዋል በተባለ ንግግር ኪም ፤ የሀገሪቱን የባህር ኃይል እንዲጠናከር ጥሪያቸውን አቅርበዋል።

አሜሪካ በኮሪያ ልሳነ ምድር አቅራቢያ የሚገኘውን ውሃ " የኑክሌር ጦርነት አደጋ " ወደደቀነ ከፍተኛ አለመረጋጋት ቀይራለች ሲሉ ከሰዋል።

አሜሪካ፣ ደቡብ ኮሪያ እና ጃፓን  ፤ የሰሜን ኮሪያን የኒውክሌር ስጋት ለመቋቋም በሚል የባህር ኃይል ልምምድ እንቅስቃሴ ጨምሮ በቅርቡ የጋር ስብሰባ አድርገው ነበር።

የሶስቱ ሀገራት እንቅስቃሴ ኪምን ያስቆጣ ሲሆን አገራቸውን ለመውረር ያሴሩትን ሴራ ለማክሸፍ ወታደራዊ ኃይላቸው ያለማቋረጥ ዝግጁ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል።

ኪም ጆንግ ኡን የሶስቱ ሀገራት መሪዎችን (ጆ ባይደን፣ ዩን ሱክ ዮል እና ፉሚዮ ኪሺዳ) " የወንበዴ አለቆች " ሲሉ ኃይለቃል ተጠቅመው ተናግረዋቸዋል።

የደቡብ ኮሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ኪም ፤ የደቡብ ኮሪያን ፣ የአሜሪካ ፣ እና የጃፓን መሪዎችን ስም ለማጥላላት " በጣም ጸያፍ ቋንቋ " በመጠቀማቸው እንዳዘነ ገልጿል።

ሚኒስቴሩ ፤ " ሰሜን ኮሪያ ውጥረት የሚፈጥሩ ድርጊቶችን በግድ የለሽነት የትነዛቸውን ዛቻዎች እና ቅስቀሳዎች  " ማቆም አለባት ብሏል።

ፎቶ ፦ ኪም ጆንግ ኡን ከልጃቸው ጋር - የሰሜን ኮሪያ ሚዲያ KCNA

@tikvahethiopia