TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ሄሜቲ ሞስኮ ምን ይሰራሉ ? የጎረቤታችን ሀገር ሱዳን ሉአላዊው የሽግግር ም/ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) ሩስያ፣ ሞስኮ ይገኛሉ። የሄሜቲ የሩስያ ጉብኝት በምዕራባውያን ሀገራት እና በሱዳን ወታደራዊ ክንፍ መካከል ውጥረት ባለበት እንዲሁም በዩክሬን ጉዳይ ምዕራባውያን ሩስያን በዲፕሎማሲያዊ መንገድ ለማግለል ማዕቀብም ለመጣል እየዛቱ ባሉበት ወቅት ነው። ሄሜቲ በትዊተር…
#SUDAN #RUSSIA

የሱዳን ሉአላዊ የሽግግር ም/ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንት ጄነራል መሐመድ ሃምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) ሩስያ ሞስኮ የሚገኙ ሲሆን ከሀገሪቱ ባለስልጣናት ጋር ውይይት አድርገዋል።

ሄሜቲ ከሩስያ ምክትል ጠ/ሚ አሌክስአንደር ኖቫክ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ጋር ተገናኝተው መክረዋል።

ይኸው ጉዧቸው ሀገራቸውና ወታደራዊ መንግስታቸው ከምዕራብ ሀገራት ያገኝ የነበረው የገንዘብ ድጋፍ ስለተቋረጠ ከሩሲያ ድጋፍ ለማግኘት እየጣረ መሆኑ ማሳያ ተደርጎ ተወስዷል።

ሳመህ ሳልማን የተባሉ የምጣኔ ኃብት ተንታኝ ለቪኦኤ በሰጡት ቃል የሄሜቲ የሞስኮ ጎብኝት በምጣኔ ሃብት ቅውስ ውስጥ ከምትገኘው ሱዳን ወቅታዊ ሁኔታ አንጻር እንደሚታይ ያስረዳሉ።

አሜሪካ እና ምዕራብ ሀገራት ይሰጡት የነበረውን የገንዘብ ድጋፍ ካቋረጡ እና የሱዳንን ብድር ለመሰረዝ ያስተላለፉት ውሳኔ ከሰረዙ ወዲህ የሱዳን ምጣኔ ኃብቷ ይዟታ በእጅጉ እንደተዳከመ ገልፀዋል።

የሀገሪቱ መገበያ ገንዘብ #ከዶላር ጋር ያለው ንጽጽር እየሰፋ በመጣበት በአሁኑ ሰዓት በሀገሪቱ ውስጥ ያለው የሸቀጦች ውድነት ከቀዳሚዎቹ መካከል ሆኗልም ብለዋል።

አሜሪካ በጀነራል ሄሜቲ እና ሌ/ ጄኔራል አብድል ፈታ አልቡራንን በመሰሉ የጦር አመራሮች ላይ ድንገት ማዕቀቦች ከጣለች በሚል ሱዳን የሩሲያን ድጋፍ ለማግኘት እየጣረች ሊሆን ይችላል ሲሉ ሳማህ ሳልማን ጠቁመዋል።

ካሜሮን ሀድሰን የተባሉ አትላንቲክ ካውንስል ውስጥ የሚሰሩ የአፍሪካ ጉዳዮች ተንታኝ በበኩላቸው የአሁኑ የሱዳንና ሩሲያ ግንኙነት ከኢኮኖሚ ፍላጎት በዘለለ የስትራቴጂ ሽግሽግ ማሳያ ሊሆን እንደሚችል ለቪኦኤ ጠቁመዋል።

ፎቶ ፦ የሄሜቲ ትዊተር ገፅ

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#BRICS BRICS ዛሬ አዳዲስ አባል ሀገራትን መቀበሉን አሳውቋል። እነዚህም ፦ 🇪🇹 #ኢትዮጵያ 🇦🇷 አርጀንቲና 🇪🇬 ግብፅ 🇮🇷 ኢራን 🇸🇦 ሳዑዲ አረቢያ 🇦🇪 የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስ ናቸው። አዳዲሶቹ አባል አገራት ከጥር 1 ቀን 2024 ጀምሮ ቡድኑን ሙሉ በሙሉ እንደሚቀላቀሉ  የደቡብ አፍሪካው ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎዛ ተናግረዋል፡፡ የሀገራችን ኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ የBRICS…
ስለ BRICS ምን ይታወቃል፤ ዓላማውስ ምንድነው ?

- BRICS አሁን ላይ አዳዲስ አባል ሀገራትን ሳይጨምር የተመሰረተው እኤአ 2001 ላይ በብራዚል፣ ሩስያ፣ ህንድ፣  ቻይና  ነው። በኃላም ደቡብ አፍሪካን አካቷል።

- የምዕራባውያን ተፅእኖን ለመገዳደር የተመሰረተ ስብሰብ ነው። በተጨማሪ እንደ IMF እና ዓለም ባንክ ያሉ የገንዘብ ተቋማትን አሰራር የማሻሻያ መንገዶችን ለመፈለግ፣ ለታዳጊ አገራት ምጣኔ ሃብት ድምጽ እና ውክልና ለመፍጠር ነው።

- አባል ሀገራቱ የቡድኑ አላማ ፍትህ እንደሆነ እና ብዝሃነት ያለው የዓለም ስርአት እንዲፈጠር መስራት መሆኑን ይናገራሉ። በምዕራባውያን የበላይነት የሚመራው የዓለም ስርአት እንዲያከትም ይፈልጋሉ።

- አሁን ይቀላቀለሉ የተባሉ አባል ሀገራትን ሳይጨምር አምስቱ ሀገራት ብቻቸውን 3.24 ቢሊዮን የህዝብ ብዛት አላቸው። ያላቸው ብሔራዊ ገቢም አንድ ላይ ሲሰላ 26 ትሪሊዮን ዶላር ይደርሳል። ይህ ከዓለም ምጣኔ ሃብት 26 በመቶውን የሚይዝ ነው።

- የBRICS አባል ሀገራት ለዓለም ንግድ #ከዶላር ውጪ ተጨማሪ መገበያያ ገንዘብ መኖር እንዳለበት ያምናሉ።

- ለዓለም ንግድ ዋነኛ መገበያያ ከሆነው ዶላር ተጨማሪ የመገበያያ ገንዘብ እንደሚያስፈልግ የሚያምኑት አባል ሀገራቱ ዓለም በጥቂት ሀገራት የበላይነት መመራቷ ማብቃት አለበት የሚል የፀና አቋም አላቸው።

- የኢኮኖሚ የበላይነቱ የተወሰኑ ቦታዎች ላይ ብቻ መወሰኑ ብዙ ሀገራትን በጥቂቶች ጫና ስር እንዲወድቁ በማድረጉ ይህን ለማስተካከል እንደሚሰሩ አባል ሀገራቱ ይናገራሉ።

የብራዚል፣ ሩስያ፣ ሕንድ ፣ ቻይና እና ደ/አፍሪካ ስብስቡ BRICS " ልንቀላቀላችሁ እንፈልጋለን " ብለው ጥያቄ ካቀረቡለት ሀገራት መካከል በነዳጅ ሀብታም የሆኑትን ሳዑዲ አረቢያ ፣ የተባበሩት አረብ ኤሜሬትስን ጨምሮ ኢራን፣ #ኢትዮጵያ፣ ግብፅ ፣ አርጀንቲናን በመጨመር እና አባል እንዲሆኑ በማፅደቅ አጠቃላይ የአባል ሀገራቱን ስብሰብ ወደ 11 አሳድጓል።

@tikvahethiopia