TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ከደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ፦

የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) የክልሉን ብሔር፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በሰጡት ህገ-መንግስታዊ የሥልጣን ውክልና ላለፉት ሃያ ስድስት ዓመታት ሕዝቡን በማስተባበር እና በክልሉ ውስጥ ያለውን እምቅ የልማት ፀጋዎች እንዲሁም ውስን የሆነው የካፒታል አቅሞች አቀናጅቶ በመምራት አበረታች ውጤቶችን ማስመዝገቡን ሕዝቡም በየደረጃው
ተጠቃሚ መሆን ስለመቻሉ ሕዝቡ ራሱ የሚመሰክረው ሀቅ ነው፡፡

ይሁን እንጂ አሁንም ቢሆን በርካታ ያልተፈቱ የሰላም፣ የልማት እና የዴሞክራሲ ጥያቄዎች ያሉት መሆኑን ደኢህዴን በተገቢ ሁኔታ ይገነዘባል፡፡
በአገር ደረጃ ለመጣው አዲስ የለውጥ ምዕራፍ ደኢህዴን ከፍተኛ የማይተካ ሚና ተጫውቷል፡፡ የተጀመረው የለውጥ እንቅስቃሴ በትክክለኛ አቅጣጫ እንዲመራ እና ሕዝቡም በለውጡ የተሟላ ተጠቃሚነቱ እንዲረጋገጥ አበክሮም ይሰራል፡፡

በ10ኛው የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባኤ የተቀመጡ አቅጣጫዎች አፈጻጸማቸው የደረሰበትን ደረጃ የድርጅቱ የሥራ አስፈጻሚ እና ማዕከላዊ ኮሚቴ በዝርዝር ገምግሟል፡፡ ከጉባኤ ማግስት ጀምሮ
በኃላፊነት መንፈስ መፍትሄ እና ምላሽ ማግኘት ያለባቸውን ጥያቄዎች በድርጅቱ መሪነት እየተፈጸመ ያለበትን ሁኔታ ፈትሸዋል፡፡ ሥራ አስፈጻሚው እና ማዕከላዊ ኮሚቴው በዝርዝር የገመገማቸውን ጉዳዮች እና በቀጣይ ወራት ርብርብ ማድረግ በሚገቡ ጉዳዮች ላይ በየደረጃው ከሚገኘው የደኢህዴን አመራሮች ጋር ውይይት ለማድረግ ከየካቲት 28 እስከ መጋቢት 1/07/2011 ዓ.ም በክልሉ ርዕሰ መዲና ሀዋሣ ውይይት እየተደረገ ይገኛል፡፡

ይሁን እንጂ ውይይቱ በሰከነ ሁኔታ እየተካሄደ ባለበት የተወሰኑ በብድን የተደራጁ አካላት ውይይቱ አዳራሽ ጭምር በመግባት ህግንና ሥርዓትን ባልተከተለ አግባብ የውይይት መድረኩ እንዲታወክ፣ እንዲቋረጥ እንዲሁም
በአንዳንድ አመራሮች ላይ ድብደባ ፈጽመዋል፡፡ ድርጊቱን የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት በጽኑ ያወግዛል፡፡ ሁኔታው ወደ ከፋ ጫፍ እንዳይደርስ የውይይቱ ተሳታፊ አመራሮች ያሳዩትን ኃላፊነት የተሞላበት ትዕግስትና ጨዋነት የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ያደንቃል፡፡

ለውይይቱ መነሻ የተዘጋጀውን ሰነድ አስመልክቶ #የተሳሳቱና #የተዛቡ መረጃዎች ለህብረተሰቡ እየተላለፈ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሰነዱ የትኛውንም የሕዝብ ሁኔታ በአሉታዊና በነቀፌታ የማይገልጽ የድርጅትና የመንግስት ስራዎችን የሚዳስስ፣ በድርጅቱ አሰራርና አካሄድ መሰረት መስተካከልና መጥራት የሚገባቸውን ጉዳዮች፣ የተከሰቱ ችግሮችና መፍትሄዎችን በተገቢው ሁኔታ የሚያሳይ ሰነድ ነው፡፡ በመሆኑም ደኢህዴን የሕዝቦቻችንን ቱባ ባህልና እሴቶቻቸውን የሚያከብር የታገለለትንና በክልላችን እየደመቀ የመጣውን የሕዝቦችን ሁለንተናዊ መብትና ጥቅም ማንነት፣ ቋንቋ፣ እና ትውፊት አክብሮ የሚንቀሳቀስ ሕዝባዊ ድርጅት ነው፡፡ ለዚህም ሁልጊዜ ጽኑ አቋምና የጠራ መስመር ያለው ድርጅት ነው፡፡

ሰነዱ በድርጅቱ ባህል መሰረት ዝርዝር ጉዳዮች #የተፈተሹበትና ችግሮችን አንጥሮ ያወጣ ሰነድ ሲሆን ሰነዱ ላይ የተመላከተው ዝርዝር ግምገማ ያልጣማቸው ግለሰቦች የሚፈጥሩት #ውዥንብር እንደሆነ ደኢህዴን ማስገንዘብ ይወዳል፡፡ ይህ ሰነድ ለበርካታ ቀናት በደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴና በሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ዘንድ የሰላ #ውይይት ተደርጎበትና በሁሉም ዘንድ የጋራ መግባባት ተደርሶበት የተዘጋጀ ሰነድና የዳበረ በቀጣይም የድርጅትና የመንግስት ሥራዎችን በክልላችን በሰከነ አግባብ ለመምራት እንዲሁም የክልላችን ሕዝቦች ዘላቂ ጥቅምና መብት የሚያስጠብቅ ሁኔታ ከሁሉም የክልላችን አመራሮች ጋር የጋራ መግባባት ለመፍጠር እና በቀጣይ ለመስራት የተዘጋጀ ሰነድ መሆኑን በአጽንኦት ለማረጋገጥ ይወዳል፡፡

የሲዳማ ሕዝብ ባለው #ኩሩ እና #ቱባ ባህላዊ እሴቶች በባለፉት ሃያ ሰባት ዓመታት ከሌሎች የክልሉ ሕዝቦች ጋር አብሮ የመኖር የዳበረ የእንግዳ ተቀባይነት ባህል ያለው ታላቅ ሕዝብ ነው፡፡ የሲዳማ ብሔር ሌሎች ሕዝቦችን "ዳኤቡሹ" ብለው ተቀብሎ አቅፎ የሚኖር፣ የሚያስተናግድ ታላቅ እንግዳ ተቀባይ ሕዝብ ነው፡፡ ደኢህዴንም ለዚህ ታላቅ ሕዝብ ከፍተኛ አክብሮት አለው፡፡
ሕዝቡም በደኢህዴን መስመር ተጠቃሚ በመሆኑ ኩራት ይሰማዋል፡፡

ይሁን እንጂ ሕዝቡን የማይወክሉ የተወሰኑ ቡድኖች እየተካሄደ የነበረውን የውይይት መድረክ እንዲቋረጥ አድርገዋል፡፡ የትኛውም ጥያቄ በዴሞክራሲያዊ አግባብ በሰለጠነ መንገድ መስተናገድ ሲገባው የኃይል እርምጃን አማራጭ በማድረግ የሚቀርብ ጥያቄ ተቀባይነት የሌለውና ተገቢነት የጎደለው በመሆኑ ደኢህዴን ያወግዛል፡፡ ሕግን የተላለፉ አካላትንም መንግስት ተከታትለው ለሕግ እንዲያርብ ይጠብቃል፡፡ የዜጎች ሕገ መንግስታዊ፣ በነጻነት የመዘዋወር እና የመሰብሰብ መብታቸው ሊከበር ይገባል፡፡

በሀዋሳ እና በሲዳማ ዞን የሚትገኙ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ኃይማኖት መሪዎች፣ ሴቶች፣ ወጣቶች እና መላው የህብረተሰብ አባላት ሁኔታዎች እንዳይባባሱ ላሳያችሁት ትዕግስትና ጨዋነት ለተሞላበት ኃላፊነት ደኢህዴን አድናቆቱን ያቀርብላቸኋል፡፡ ይኸው አርአያነት ያለው ተግባራችሁ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ደኢህዴን ሙሉ እምነት አለው፡፡

በውይይቱ መሰነካከልና መስተጓጎል ምክንያት የተረበሻችሁ አመራሮች ድርጅታችሁ ደኢህዴን ታላቅ ይቅርታ ይጠይቃል፡፡ የተቋረጠው ውይይትም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ደኢህዴን ያረጋግጣል፡፡ በውይይቱ የሚቀመጡ አቅጣጫዎች ለክልላችን ሕዝቦች ተጠቃሚነታቸውና ጥያቄያቸው ምላሽ እንደሚያገኝ ማረጋገጥ እንወዳለን፡፡

ደኢህዴን ወትሮኑም ፈተናዎችን ተጋፍጦ እንደሚያልፈው ሁሉ በቀጣይ ጊዜ ይበልጥ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ለመላው አባሎቻችንና ደጋፊዎቻችን እንዲሁም ለክልላችን ሕዝቦች ለማረጋገጥ እንወዳለን፡፡

የደኢህዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ ጽ/ቤት
የካቲት 29/2011 ዓ.ም
ሀዋሣ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ🔝

"በአሁን ሰዓት የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እና ሰራተኞች ከፕሮፌሰር #መረራ_ጉዲና ጋር ስለሀገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ #ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ። የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት የሆኑት ፕሮፌሰር #ደጀኔ_አየለም ተገኝተው ተማሪውን እያወያዩ ነው።" Dagi D.

ፎቶ: ዳጊ እና ጌድዮን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ጠዋት ወደ ገደብ ወረዳ በመጓዝ በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ #የጌዲዮ ማኅበረሰብ አባላትን ሁኔታ ተዘዋውረው ጎበኙ። ተፈናቃዮቹ #ቅሬታቸውን ለጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ አቅርበዋል። በአሁኑ ሰዓት ጠ/ሚሩ ከተፈናቃዮቹ ተወካዮች ጋር ረጅም #ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ። ፌዴራል መንግሥት ከዞንና ክልል አስተዳደር ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ በቀረበ ጥሪ መሠረት በብሔራዊ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስተባባሪነት ከመጋቢት 2 ቀን 2011 ጀምሮ አስቸኳይ የምግብና ሌሎችም አስፈላጊ አቅርቦቶችን ለተረጂዎች በማድረስ ላይ ይገኛል፡፡

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢንተርን ሀኪሞች...

በጅማ ዩኒቨርስቲ #የኢንተርን_ሀኪሞች ባነሷቸው ጥያቄዎች ዙሪያ አዲሱ #ፕሬዘዳንት/ዶክተር ጀማል አባፊታ/ ከሚመለከታቸው የፌደራል መስሪያ ቤት #ተወካዮች እና ሌሎች አካላት ጋር #ውይይት ያደርጋሉ።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፍቅር #ጉዟችንን በተመለከተ...

በTIKVAH-ETH በኩል #የተሰባሰቡት ወጣቶች ከሁሉም የሀገሪቱ ክፍል የተውጣጡ ትክክለኛውን የኢትዮጵያ ቀለም የያዙ ናቸው። ሁሉም ወጣቶች እናት ሀገራቸውን የሚወዱ እና በሀገሪቱ ላይ አዲስ ታሪክ ለመፃፍ ከሳምንት እስከ ሳምንት ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ፤ የትምህርት እና የግል ጊዜያቸውን ትተው ለሰላምና ፍቅር የሚጓዙ ናቸው። ለዚህም ሰላም ወዳዱ የኢትዮጵያ ህዝብ #ሊያመሰግናቸው ይገባል።

ዩኒቨርስቲዎችን በተመለከተ፦

#StopHateSpeech በሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚካሄድ ሲሆን የመጀመሪያው ምዕራፍ ከተማሪዎች ጋር የሚደረግ #ውይይት እና #ንግግር የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ነው። ምክንያቱም ወጣቶች ከጥላቻ እና ከስሜታዊነት ርቀው ሀገር መገንባትና ለህዝብም #ተስፋ የሚሰጡ ዜጎች እንደሆኑ ማስመስከር ስለምንፈልግ ነው።

ይህ ጉዞ እና እንቅስቃሴ ከየትኛውም አይነት የፖለቲካ አመለካከት ነፃ የሆነ፤ ከየትኛውም ድርጅትም ሆነ ቡድን ገለልተኛ የሆነ በወጣቶች የሚደረግ እንቅስቃሴ ነው። ወጣቶቹም ትክክለኛ የሀገሪቱን ቅርፅ የያዙ በፍቅር እና በንግግር የሚያምኑ ሀገሪቷን ከጥላቻ አላቀው ትልቅ ሀገር የመገንባት ህልም ያላቸው ናቸው።

√ወጣቶቹ የሰላምን አርማ ይዘው በየሄዱበት የሚሰብኩት ስለፍቅር እና መተባበር እና መተጋገዝ ብቻ ነው። በሚዘጋጁት መድረኮችም የጥላቻ መዘዞችን ማስገንዘብ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀማቸውን እንዲያሻሽሉ ማስገንዘብ ነው።

√ውይይቶች በጠቅላላ የሚደረጉት #በወጣት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች #መካከል ብቻ ነው። ሌላው ተናጋሪዎች ተማሪዎች እና የዩኒቨርሲቲው አካላት ብቻ ናቸው።

በቀጣይ ምዕራፍ 2፦ ከዩኒቨርሲቲ #አመራሮች እና #ሰራተኞች ጋር ተመሳሳይ መድረክ ይኖረናል።

ኢትዮጵያን በፍቅር እንገንባ!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ

በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ የተፈጠረው ችግር ዛሬም ድረስ እልባት አላገኘም። እሁድ ምሽት ከነበረው ውጥረት በኃላ ሰኞ ውይይት ለማድረግ ተሞክሮ ነበር በውይይቱ ላይ በተደረሰው ስምምነትም ተማሪዎች ማክሰኞ ጥዋት ትምህርት እንዲጀምሩ ተደርጎ ነበር ነገር ግን ጥያቄዎቻችን አልተመለሱም በሚል ከማክሰኞ ከሰዓት በኃላ እስከአሁን ድረስ ትምህርት እንደተቋረጠ ነው። ዋነኛው የተማሪዎች ጥያቄ እንደሆነ የሰማሁት ሰሞኑን በተቋሙ ከተፈጠረው ችግር ጋር በተያያዘ የታሰሩ ተማሪዎች እንዲፈቱላቸው ነው። እንዲሁም ሌሎች በግቢው ያሉ ችግሮችን የሚመለከተው የፌደራል መንግስት አካላት ከተቋሙ ጋር #ውይይት አድርገው እንዲፈቱ እንደሚፈልጉ ለጉዳዩ ቅርብ የሆነ ሰው ነግሮኛል።

ትኩረት ለድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ‼️
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Somali #Afar #ሰላም #ውይይት

ትላንት የአፋርና የሱማሌ ኢሳ ማህበረሰብ የሰላም ኮንፈረንስ በአዳማ ተካሂዶ ነበር።

የሰላም ኮንፈረንሱ በሁለቱ ማህበረሰብ መካከል ያሉ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ዘላቂ ሰላምን ማምጣት ዓላማ ያደረገ ነው መሆኑን ሰላም ሚኒስቴር አሳውቋል።

በአካባቢዎቹ የሚታዩ አለመግባባቶችን በውይይት በመፍታት ሰላምን ለማምጣት ወደ ግጭት ለሚያመሩ ጉዳዮችም መፍትሔዎች ተለይተው የተቀመጡበት መድረክ ነው ተብሏል።

የተዘጉ መንገዶች እንዲከፈቱ ማድረግ፤ በግጭት ምክንያት ከኖሩበት ቀዬአቸው ተፈናቅለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በዘመድ አዝማዶቻቸው ቤት ተጠልለው እየኖሩ ችግሮችን እየተጋፈጡ ያሉ ወገኖች ወደ ቀደመው ሰላማዊ ህይወታቸው እንዲመለሱ ሊደረጉ የሚያስፈልጉ ጉዳዮችንም በመድረኩ መነሳቱን ከሰላም ሚኒስቴር በኩል የወጣው መረጃ ያሳያል።

ባለፈው ዓመት በተነሳ ግጭት ከዘጠኝ ወር በላይ ቤታቸው ተፈናውለው በየመጠለያ ጣቢያ እና በየዘመዶቻቸው ቤት የተጠለሉ በርካታ ወገኖች እንዳሉ ይታወቃል።

@tikvahethiopia
#EHRC

" ... ጉዳዩ ከዚህ የበለጠ ሳይባባስ ፓርላማው የመንግስት አስፈፃሚ አካሉን በአስቸኳይ ሊያሳስብ ይገባል " - ዶ/ር ዳንኤል በቀለ

ዛሬ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) የ9 ወራት የእቅድ አፈፃፀሙን ሪፖርት ለህ/ተ/ም/ቤት የዴሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አቅርቧል።

በዚህም ወቅት የኢሰመኮ ዋና ኮሚሽነር ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ፥ በአማራ ክልል የሰብዓዊ መብት ጉዳዮች አሳሳቢ እንደሆኑ ቀጥለዋል ብለዋል።

ከቅርብ ጊዜ አንስቶ መንግሥት በአማራ ክልል እያካሄደ ያለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ከሰብዓዊ መብቶች አንፃር በጣም የሚያሰጋነው ሲሉ ገልጸዋል።

ዋና ኮሚሽነሩ ፤ በአሁን ወቅት በአማራ ክልል እየተካሄደ ባለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ #በሲቪል ሰዎች ላይ ፦
- የሞት፣
- የንብረት መውደም፣
- የመፈናቀል ጉዳት መድረሱን በዚህም የሰብዓዊ መብት ስጋቱም መቀጠሉን አንስተዋል።

" መንግሥት የፀጥታ እርምጃ በአማራ ክልል በማካሄድ ላይ የሚገኝ መሆኑን አሳውቋል ፤ " ያሉት ዶ/ር ዳንኤል " ነገር ግን ይህ ወታደራዊ እርምጃ የሰብዓዊ መብት እንድምታ ስላለው ፣ የሰብዐዊ መብት ተፅእኖ ስለሚፈጥር ይሄን በቅርበት እየተከታተልን ነው " ብለዋል።

" እስካሁን ባለው መረጃ በመነሳት ከሰብዓዊ መብቶች አንፃር በጣም የሚያሰጋ ስለሆነ ኢሰመኮ #ውይይት እና #ሰላማዊ መፍትሄ አስፈላጊነትን አበክሮ በማሳሰብ ጉዳዩ ከዚህ የበለጠ ሳይባባስ ፓርላማው የመንግስት አስፈፃሚ አካሉን በአስቸኳይ ሊያሳስብ ይገባል። " ሲሉ አክለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ ዶ/ር ዳንኤል ባቀረቡት ሪፖርት የዘፈቀደ እስር ፣ ሰዎች ሲታሰሩ የሚያዙበት መንገድ፣ ለሰብዓዊ ጉዳዮች አሳሳቢ ሆኖ ቀጥሏል ብለዋል።

ዶ/ር ዳንኤል ፤ " በተለያዩ አካባቢዎች የሚፈፀመው የዘፈቀደ እስር እና በእስር ወቅት የሚፈፀሙ ተገቢ ያልሆኑ አያያዞች / አንዳንድ ቦታዎች ድብደባን ጨምሮ ተገቢ ያልሆነ አያያዝና እስራት እንዲሁም የፍርድ ቤት ትዕዛዝ አለመከበርም ቀጥሏል "  ብለዋል።

ዋና ኮሚሽነሩ ፤ አንዳንድ ቦታዎች ላይ የሚፈፀሙት የዘፈቀደ እስሮች #የቤተሰብ አባላትን ጭምር ለማጥቃት የሚውሉ ናቸው ሲሉ ለፓርላማው በሪፖርታቸው አሳውቀዋል።

@tikvahethiopia
" አሁንም ያለው ችግር በውይይት እና በድርድር የሚፈታበት መንገድ ዝግ ባለመሆኑ ተከታታይ ጥረቶች ይደረጋሉ " - የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት

የብሔራዊ መረጃ እና ደህንነት አገልግሎት ዛሬ ምሽት መግለጫ አውጥቶ ነበር።

በዚሁ መግለጫው በአማራ ክልል ያለው ችግር አሁንም በ #ውይይት እና በ #ድርድር የሚፈታበት መንገድ ዝግ እንዳልሆነ ጠቁሟል።

መ/ቤቱ በመግለጫው ፤ " ከድርድር እና ውይይት ይልቅ መንግሥታዊ ሥልጣንን በኃይል ለመያዝ የሚጥሩ እንዲሁም አጋጣሚዎችን በማቀነባበር ዝርፊያ ለመፈጸም የሚፈልጉ የታጠቁ ቡድኖች፣ ፅንፈኛና አክራሪ ኃይሎች ከውጭ ፀረ ሰላም ኃይሎች ጋር በመቀናጀት ሀገራዊ የጸጥታ ሥጋት ለመደቀን ሙከራ እያደረጉ ነው " ብሏል።

በአማራ ክልልም እየታየ ያለው ሁኔታ ይኸው ነው ሲል ገልጿል።

" ከኢ-መደበኛ አደረጃጀቶች ጋር በተያያዘ የተከሰቱ ችግሮች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ጥረቶች ቢደረጉም ችግሩ በሚፈለገው ልክ አልተፈታም " ያለ ሲሆን ፤ " ለዘረፋ የተደራጁ ጥቂት ኃይሎች አሁን ላይ መንግሥታዊ መዋቅሮች እንዲፈርሱ፤ የፋይናንስ ተቋማት አገልግሎት እንዲቋርጡ፤ አንዳንድ ከፌዴራል መንግሥት ጋር የሚያገናኙ የመንገድ መሠረት ልማቶች እንዲዘጉ በማድረግ፤ ሕዝቡ ላይ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፖለቲካዊ ጫና ለመፍጠር ሙከራ እያደረጉ ይገኛሉ " ብሏል።

ብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት ፤ አስቸኳይ ጊዜ አዋጁን የሚያስፈፅመው የጠቅላይ መምሪያ ዕዝን በማስተባበር የክልሉን ሰላምና ደኅንነትን በአጭር ጊዜ ለማረጋገጥ የሚያግዝ ስምሪት ወስዶ እየሠራ መሆኑን ገልጾ " በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ሕገወጥ እንቅስቃሴ ውስጥ እየተሳተፉ ያሉ ግለሰቦችና ቡድኖች ከድርጊታቸው ይቆጠቡ " ሲል አሳስቧል።

አሁንም በአማራ ክልል ያለው ችግር #በውይይትና #በድርድር የሚፈታበት መንገድ ዝግ ባለመሆኑ ተከታታይ ጥረቶች ይደረጋሉ ሲል አሳውቋል።

" ለዝርፊያ ከተደራጁ ቡድኖች ጋር የሚንቀሳቀሱ አካላት ካሉ ግን አስፈላጊው እርምጃ እንደሚወሰድ እና ሕግ የማስከበር ሂደቱ ተጠናክሮ ይቀጣላል " ሲል ገልጿል።

@tikvahethiopia
#AmharaScholarsCouncil

በአማራ ክልል የምሁራን መማክርት ጉባኤ በላከልን መግለጫ ፤ በክልሉ ውስጥ አሁን የተፈጠረው ቀውስ በዘላቂነት የሚፈታው በውይይት መሆኑን ገልጾ መንግስትና የታጠቁ ሀይሎች ተኩስ አቁመው እንዲወያዩ ጥሪ አቅርቧል።

ጉባኤው  በመግለጫው ፤ " ሕዝባችን ባለፉት አመታት ተደጋጋሚ የሆኑ ማንነትን መሰረት ያደረጉ ግፎች እና በደሎች እየደረሱበት ይገኛል " ብሏል።

ይህንን ለማስቆምና መሠረታዊ ጥያቄዎቹ መልስ እንዲያገኙ በተደራጀ መልኩ መታገል እንደሚያስፈልግ ገልጿል።

ይህ አይነቱ ፖለቲካዊ ትግል ዘላቂ መፍትሔ እንዲያስገኝ በ #መነጋገር እና በ #ውይይት ላይ የተመሠረተ ሊሆን እንደሚገባው አስገንዝቧል።

" በዚህ ረገድ ባለፉት አመታት በርካታ ጥረቶች ተደርገዋል " ሲልም ገልጿል።

የአማራ ምሁራን መማክርት ጉባኤ፤ " ዛሬ ሕዝባችን ዘር የሚዘራበትና የማዳበሪያ እና ምርጥ ዘር ዕጥረቱን ለመቀነስ አይን አይን እያየበት ያለበት ወቅት ነው። በተጨማሪም ትላንት አብረውት ተሰልፈው የተዋደቁ ኃይሎች ዛሬ ከሀገር መከላከያ ሠራዊት ጋር የሚጋጩበት ሁኔታ ሊፈጠር አይገባም። " ብሏል።

ስለሆነም ክልሉ ውስጥ አሁን የተፈጠረው ቀውስ በዘላቂነት የሚፈታው በውይይት መሆኑ ታውቆ መንግስትና የታጠቁ ሀይሎች ተኩስ አቁመው እንዲወያዩ ጥሪ አቅርቧል።

በየአካባቢው ያሉ የሀገር ሽማግሌዎች የሀይማኖት አባቶች እና ምሁራን ሰላም እንዲሰፍን ችግሮች በውይይት እና በሰላም እንዲፈቱ የበኩላቸውን ጥረት እንዲያደርጉ ጥሪውን አስተላልፏል።

(መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia