#update ጠ/ሚር ዶክተር ዐቢይ አሕመድ ዛሬ ጠዋት ወደ ገደብ ወረዳ በመጓዝ በጊዜያዊ መጠለያ ጣቢያ የሚገኙ #የጌዲዮ ማኅበረሰብ አባላትን ሁኔታ ተዘዋውረው ጎበኙ። ተፈናቃዮቹ #ቅሬታቸውን ለጠ/ሚር ዐቢይ አሕመድ አቅርበዋል። በአሁኑ ሰዓት ጠ/ሚሩ ከተፈናቃዮቹ ተወካዮች ጋር ረጅም #ውይይት እያደረጉ ይገኛሉ። ፌዴራል መንግሥት ከዞንና ክልል አስተዳደር ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ በቀረበ ጥሪ መሠረት በብሔራዊ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ኮሚሽን አስተባባሪነት ከመጋቢት 2 ቀን 2011 ጀምሮ አስቸኳይ የምግብና ሌሎችም አስፈላጊ አቅርቦቶችን ለተረጂዎች በማድረስ ላይ ይገኛል፡፡

#PMOEthiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia