TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ጀርመን

በፍራንክፈርት የስምንት አመት ልጅ ከነ አናቱ ወደ ባቡር ሐዲድ ገፍቶ በመጣል የተጠረጠረው ኤርትራዊ በጥምር ግድያ ወንጀል ክስ ሊመሰረትበት ነው፣ የ40 አመቱ ተጠርጣሪ ባለትዳርና የ3 ልጆች አባት ነው። ስዊትዘርላንድ ከገባ 13 አመታት አስቆጥሯል።

Via #EsheteBekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ ፦

#ሳዑዲ_አረቢያ ፦ ሳዑዲ አረቢያ የሃጅ ተጓዦችን እየተቀበለች ትገኛለች። ከቀናት በፊት የመጀመሪያው የሃጅ ተጓዦች ቡድን ከኢንዶኔዥያ ወደ ሳዑዲ መግባቱ ይታወሳል። ዛሬ ባገኘነው መረጃ እስከ ትላንት እሁድ ድረስ ከተለያዩ ሀገራት ለሃጅ ጉዞ ሳዑዲ የገቡ ተጓዦች 955 ደርሰዋል። ሳዑዲ አረቢያ ዘንድሮ ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ 1 ሚሊዮን የሃጅ ተጓዦችን እንደምታስተናግድ ይታወቃል።

#ጀርመን ፦ የጀርመኑ መኪና አምራች ኩባንያ መርሴዲስ-ቤንዝ 1 ሚሊዮን ገደማ አሮጌ መኪናዎችን ለጥገና ጠርቷል። ኩባንያው እኚህ መኪናዎች ፍሬናቸው ችግር አለባቸውና ጠግኜ ልመልስላችሁ ብሏል። ኩባንያው መኪኖቹ ከፍተኛ በሆነ ዝገት ምክንያት የፍሬን ሰርዓታቸው ተገቢውን ሥራ ላይሰራ ይችላል ብሏል። ጀርመን ያሉ 70 ሺህ መኪናዎችን ጨምሮ ከ993 ሺህ በላይ መኪናዎች መጠገን አለባቸው።

#UK ፦ ዩናይትድ ኪንግደም ለመጀመርያ ጊዜ ኤም 270 የተባሉ ረዥም ርቀት ተወንጫፊ ሚሳኤሎችን ለዩክሬን ልትሰጥ ነው። እነዚህን እጅግ ዘመናዊ ሮኬት ማስወንጨፍያ መሣሪያዎች መቼ እና በምን ያህል መጠን ወደ ዩክሬን እንደምትልክ አልገለጸችም።

#ሩስያ ፦ የሩስያ ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን ለአሜሪካ ማስጠንቀቂያ ልከዋል። ሀገሪቱ ለዩክሬን የጦር መሣሪያ ልገሳ እንድታቆም ያስጠነቀቁ ሲሆን ይህ የማይሆን ከሆነ ሩሲያ በዩክሬን የምታደርሰው ጥቃት መጠኑ እየሰፋ እንደሚመጣ ገልፀዋል። አሜሪካ ባለፈው ሳምንት ዘመናዊ ተወንጫፊ ሚሳኤል ሲስተምን ወደ ዩክሬን ልካለች። አሜሪካ መሣሪያውን ብትሰጥም ዩክሬን ይህን መሣሪያ ወደ ሩሲያ ግዛት እንዳትተኩስ አሳስባ ነው።

#ቢቢሲ #ሳዑዲጋዜቴ #ኤፒ

@tikvahethiopia
ከስራ ቦታ እንደወጡ ያልተመለሱት አቶ ኢብራሂም በያን !

በኦሮሚያ ክልል ሰበታ ከተማ፣ ቀበሌ 04 ነዋሪ እና የሐጂ መሐመድ ሪል ስቴት ምክትል ሥራ አስኪያጅ የሆኑት ኢብራሂም በያን ሠይድ መጋቢት 29/2014 ከሥራ ቦታ እንደወጡ እስከአሁን አለመመለሳቸውን ፤ የት እንዳሉም እንደማይታወቅ ቤተሰቦቻቸው ገልጸዋል።

በወቅቱ አቶ ኢብራሂም ከሥራ ወጥተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው በመመለስ ላይ እያሉ የስልክ ግንኙነት እንደነበራቸው የገለፁት ቤተሰቦቻቸው ከምሽቱ 3 ሰዓት አካባቢ ግን የስልክ ግንኙነቱ መቋረጡን፤ የስልክ ግንኙነቱ ሲቋረጥም በአዲስ አበባ ከተማ ልዩ ቦታው #ጀርመን_አደባባይ አካባቢ እንደነበሩን አታውሰዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኙ የተለያዩ የፖሊስ ጣቢያዎች ፣ ትራፊክ ጽ/ቤቶች፣ ሆስፒታሎችና ጤና ጣቢያዎች ጠይቀውም ምንም ፍንጭ ባለማግኘታቸው ለአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እንዳመለከቱ የገለጹት የአቶ ኢብራሂም ወንድም አብዱልሀዲ በያን እና የቅርብ ቤተሰባቸው ሩቅያ ሀሰን በወቅቱ ጉዳዩን መዝግቦ መርማሪ በመመደብ ተከታትሎ እንደሚያሳውቋቸው ፖሊስ እንደተነገራቸው ገልጸዋል።

ቢሆንም ግን ከመጋቢት 29 ቀን 2014 እስከ ዛሬ ምንም አይነት መፍትሄ እንዳልተገኘ አስረድተዋል።

አቶ ኢብራሂም ለረጅም ጊዜያት በመጥፋታቸውና ያሉበት ቦታ ባለመታወቁ ቤተሰቦቻቸው በጭንቀት ውስጥ የሚገኙ ሲሆን አሁንም ፍለጋቸውን መቀጠላቸውን ገልፀዋል።

የኢብራሂም ቤተሰቦች አቶ ኢብራሂምን ያየ ወይንም ያሉበትን ቦታ የሚያውቅ በስልክ 0911149306፣ 0911616199 ፣ 0911438549 ላይ በመደወል እንዲያሳውቃቸው ተማፅነዋል።

@tikvahethiopia
#ጀርመን

ጀርመን ውስጥ በአስራዎቹ የዕድሜ ክልል ውስጥ የሚገኙ ሁለት ሴቶችን በስለት የወጋው ኤርትራዊ የዕድሜ ልክ እስራት ተፈረደበት።

ጥገኝነት ጠያቂ የሆነው ይህ ኤርትራዊ በስለት ከወጋቸው ሁለት ታዳጊ ሴቶች መካከል የአንዷ ሕይወቷ አልፏል።

ኡቁባ ቢ በሚል ስም ብቻ የተጠቀሰው የ27 ዓመቱ ግለሰብ፣ ሁለቱ ታዳጊ ሴቶች ላይ ጥቃቱን የፈጸመው በዚህ ዓመት ኅዳር ወር ላይ " ኢሌራኪራቸበርግ " ተብላ በምትጠራ የጀርመን ከተማ ውስጥ ነው።

በጀርመን ከፍተኛ ቁጣን በቀሰቀሰው በዚህ የወንጀል ድረጊት ኤስ የተባለችው የ14 ዓመት ታዳጊ 23 ጊዜ በስለት ተወግታ ሕይወቷ ሲያልፍ፤ የ13 ዓመት ጓደኛዋ ደግሞ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባታል።

ዐቃቤ ሕግ ምን አለ ?

የዕድሜ ልክ እስራት የተፈረደበት ኤርትራዊ ስለቱን የያዘው በአካባቢው በሚገኝ የኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት ውስጥ ሊጠቀመው አስቦት የነበረ ነው።

ነገር ግን ግለሰቡ የያዘውን ቢላ ታዳጊዎቹ ከተመለከቱበት በኋላ ጥቃት ሰንዝሮባቸዋል አንደኛዋን ለሞት ሲዳርጋት ሌላኛዋ ክፉኛ ጎድቷታል።

ዐቃቤ ሕግ እንዳለው ግለሰቡ ታዳጊ ሴቶቹ " ለፖሊስ ይጠቁሙብኛል " በሚል ድንገት ወንጀሉን ፈጽሞባቸዋል።

ግለሰቡ ወደ #ኢትዮጵያ ተጉዞ ጋብቻ ለመፈጸም ከጀርመን ባለሥልጣናት የጠየቀው የጉዞ ሰነድ ስላልተሰጠው በኢሚግሬሽን ኃላፊዎች ተበሳጭቶ ነበር።

በደቡብ ጀርመን የሚገኘው ፍርድ ቤት ኤርትራዊው የፈጸመው ወንጀል " እጅግ ከባድ " በመሆኑ ግለሰቡ 15 ዓመታት በእስር ከቆየ በኋላ እንኳን ከእስር የመለቀቅ ዕድሉ በጣም የጠበበ ነው ተብሏል።

ኤርትራዊው ጀርመን መች ገባ ?

ይህ ኤርትራዊ ጀርመን የገባው ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ስደተኞች ጦርነት እና እስርን በመሸሽ አውሮፓን ባጥለቀለቁበት ዓመት እአአ 2015 ላይ ነበር።

ኡቁባ ቢ ለፍርድ ቤት ምን አለ ?

ኡቁባ ቢ ፍርድ ቤት በቀረበበት ወቅት በፈጸመው የወንጀል ድርጊት #መጸጸቱን ገልጾ የተጎጂ ቤተሰቦች ይቅርታን ጠይቋል።

ይግባኝ ...

ግለሰቡ የተላለፈበትን ብይን ይግባኝ መጠየቅ ይችላል ተብሏል።

ፍርደኛው የሚያቀርበው ይግባኝ ውድቅ ከተደረገ ግን በእስር ጊዜው ወቅት ወደ ትውልድ አገሩ እንዲመለስ ሊደረግ እንደሚችል ዐቃቤ ሕግ ገልጿል።

መረጃው የቢቢሲ ነው።

@tikvahethiopia
#አውሮፓ

የአውሮፓ ፓርላማ የህብረቱን #የስደተኞች እና #የጥገኝነት ደንቦችን የሚያጠናክር ትልቅ ማሻሻያ አጽድቋል።

የአውሮፓ ህብረት የጥገኝነትና ፍልሰት ስምምነት ከ2015 ጀምሮ ሲመከርበት የቆየ ሲሆን በ2 ዓመት ውስጥ ተግባራዊ ይሆናል ተብሏል።

አዲሱ ሕግ ምን ይዟል ?

➡️ የጥገኝነት ሂደት ጥያቄ #ያፋጥናል ፤ መደበኛ ያልሆኑ ስደተኞች ወደ አገራቸው እንዲመለሱ #ያስገድዳል

➡️ የአውሮፓ ህብረት አባል አገራት የጥገኝነት ጠያቂዎችን ኃላፊነት እንዲጋሩ ያደርጋል።

➡️ የአውሮፓ ህብረት 27 አባል አገራት በሺህዎች የሚቆጠሩ ስደተኞችን ከጣሊያን፣ ግሪክ እና ስፔን ካሉ " #የድንበር " አገራት እንዲወስዱ ወይም በምትኩ ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ እንዲያቀርቡ ያደርጋል።

➡️ ዝቅተኛ ተቀባይነት የማግኘት እድል ያላቸው የጥገኝነት ጠያቂዎች ወደ አውሮፓ ህብረት ግዛት ሳያስገቡ ጉዳያቸው በፍጥነት መታየት አለበት ይላል።

➡️ የጥገኝነት ጥያቄዎች ቢበዛ በ12 ሳምንታት ውስጥ እንዲያልቁ ይላል።

➡️ የጥገኝነት ጥያቄያቸው ውድቅ የተደረገባቸው በ12 ሳምንታት ጊዜ ውስጥ #በግዳጅ ወደ አገራቸው መመለስ አለባቸው  ይላል።

➡️ ስደተኞች ከመግባታቸው በፊት ባሉ በ7 ቀናት ውስጥ ጠንከር ያለ የማጣራት ሂደት ይደረግላቸዋል። የጤና እና የደህንነት ፍተሻዎችን ይጨምራል።

➡️ ከ6 ዓመት እና ከዛ በላይ ለሆኑ ማናቸውም ስደተኞች የባዮሜትሪክ መረጃ ይሰበሰባል። ስደተኞች ቁጥር በአጋጣሚ ካሻቀበም ምላሽ የሚሰጥበት አሠራር ተዘርግቷል።

ምንም እንኳን አንዳንድ የአውሮፓ ህብረት አገራት የተወሰኑ የስምምነቱን ክፍሎችን ቢቃወሙም በሚያዝያ ወር መጨረሻ በሚደረግ ድምጽ አሰጣጥ የአብዛኛውን ይሁኝታ ያገኛል ተብሎ ይጠበቃል።

ባለፈው አመት 380 ሺህ የሚጠጉ ሰዎች የአውሮፓ ህብረትን ድንበር በህገ ወጥ መንገድ አቋርጠዋል። ይህም እ.አ.አ ከ 2016 ወዲህ ከፍተኛው ቁጥር ነው።

ስለ ሕጉ ምን ተባለ ?

#ጀርመን፦ የጀርመን መራሄ መንግስት ኦላፍ ሾልስ “ ታሪካዊና አስፈላጊ እርምጃ ” ብለውታል።

#የአውሮፓ_ፓርላማ፦ የፓርላማው ፕሬዝዳንት ሮቤታ ሜሶላ “ በአብሮነት እና በኃላፊነት መካከል ያለውን ሚዛን ጠብቋል ሁሉንም ነገር በአንድ ጀምበር ባይፈታም ግን 10 ግዙፍ እርምጃ የተጓዘ ነው " ብለዋል።

#ሀንጋሪ ፦ ምንም አይነት የስደት ስምምነት ቢደረስ መደበኛ ያልሆኑ ስደተኞችን አልወስድም ብላለች።

#ፖላንድ ፦ የፖላንድ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶናልድ ቱስክ የተወሰኑ ጥገኝነት ጠያቂዎችን መውሰድ አልያም ለድንበር አገራት ገንዘብ መክፈል የሚለውን ሃሳብ " ተቀባይነት የሌለው " ሲሉ ውድቅ አድርገዋል።

#ስሎቫንያ፦ “ ልንሰራበት የምንችለው ስምምነት ነው ” ስትል ደግፋለች።

#ቤልጂየም፦ “ ፍፁም አይደለም (ሕጉን) ግን እንደግፈዋልን ” ስትል አሳውቃለች።

#ፈረንሳይ ፦ ፕ/ት ኢማኑኤል ማክሮን ድጋፍ ሰጥተዋል። የፈረንሣዩ ቀኝ አክራሪ ናሽናል ራሊ አባል ጆርዳን ባርዴላ ስምምነቱ “ #አስፈሪ ” ነው ሲሉ ተቃውመዋል።

#አምነስቲ_ኢንተርናሽናል ፦ ስምምነቱ ጥገኝነት ጠያቂዎችን ወደ “ከፍተኛ ስቃይ” የሚመራ ነው ሲል አስጠንቅቋል።

ከመንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሚነሳው አንዱ ተቃውሞ ዝቅተኛ ተቀባይነት የሚኖራቸው #ጥገኝነት ጠያቂዎች ጉዳያቸው በድንበር #መግቢያዎች ላይ ወይም #በማቆያ_ስፍራዎች እንዲስተናገዱ በማድረግ ፍትሃዊ ዕድል የማግኘት ተስፋቸውን ያመነምነዋል የሚል ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመረጃው ምንጭ ቢቢሲ መሆኑን ይገልጻል።

@tikvahethiopia