TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ብአዴን⬆️

የብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ አቶ #በረከት_ስምኦን እና አቶ #ታደሰ_ካሳ አሁን ባላቸው ወቅታዊ አቋም የአማራን ህዝብ ጥቅም እንደማያስጠብቁ በመረጋገጡና በጥረት ኮርፖሬት ላይ በሰሩት #ጥፋት እስከ ሚቀጥለው የድርጅቱ መደበኛ ጉባኤ ድረስ ከብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት #ታግደዋል፡፡

ነባር አመራሮች በማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ እንዲሳተፉ የሚፈቅደው መመሪያም #ተሽሯል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በኋላ በሚኖረው የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ አባል ያልሆነ አመራር #አይሳተፍም፡፡

📌ማዕከላዊ ኮሚቴው የሁለት ቀን ስብሰባውን ዛሬ አጠናቋል፡፡

©AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጥረት ኮርፖሬት⬆️

▪️ጣና ኮሚኒኬሽን
▪️ዳሽን ቢራ
▪️አምባሰል የንግድ ስራዎች ድርጅት
▪️ጥቁር አባይ ትራንስፖርት
▪️ዘለቀ እርሻ ልማት ድርጅት
▪️እሸት የእስታርች ውጤቶች ማምረቻ
▪️በለሳ ሎጅስቲክ
▪️BDC ኮንስትራክሽን
▪️TT ኢንጂነሪንግ
▪️አዚላ ኤሌክትሮኒክስ
▪️ዋሊያ ቆርኪ ፋብሪካ
▪️ተክራርዋ የፕላስቲክ ማምረቻ
▪️የትመን የጅብሰም ውጤቶች ማምረቻ
▪️ጎንደር ብቅል ማምረቻ ፋብሪካን ጨምሮ ከ20 የሚበልጡ ድርጅቶችን በስሩ ያስተዳድራል።

እንዲሁም፦ ጥረት ኮርፖሬት በወጋገን ባንክ፣ በአባይ ባንክና ኢንሹራንስ፣ በአፍሪካ ኢንሹራንስ፣ በፋና ብሮድካስቲንግና በሌሎች ድርጅቶች ከፍተኛ የአክሲዮን ድርሻ አለው።

አቶ በረከት ስምዖን እና አቶ ታደሰ ካሳ በጥረት ኮርፖሬት ውስጥ በሰሩት #ጥፋት ነው እስከ ሚቀጥለው የድርጅቱ መደበኛ ጉባኤ ድረስ ከብአዴን ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልነት እንዲታገዱ የተደረገው፡፡

📌አቶ በረከት ስምዖን የጥረት ኮርፖሬት ቦርድ ሰብሳቢ ነበሩ እንዲሁም አቶ ታደሰ ካሳ የጥረት ኮርፖሬት ስራ አስፈጻሚ ነበሩ።

#TIKVAHETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአየር ትራፊክ ባለሞያዎች⬇️

ትናንት በቁጥጥር ሥር የዋሉት 9 የአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪ ባለሙያዎች የተያዙት ከ6 ወር እስከ 3 ዓመት እሥራት ሊያስቀጣ በሚችል #ጥፋት መሆኑ ተገለጸ፡፡ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ዘይኑ ጀማል ናቸው ይሕን ያሉት። ኮሚሽነሩ ከቪኦኤ ጋር ባደረጉት ቃለ-ምልልስ በአየር ትራፊክ ተቆጣጣሪ ሠራተኞቹና በአሠሪያቸው ሲቪል አቪየሽን ባለሥልጣን መካከል የተፈጠረውን ውዝግብ በድርድር ለመፍታት ጥረት መደረጉንና ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽንም ጣልቃ ገብቶ ማደራደሩን ተናግረዋል።

“የተወሰኑ የእንቅስቃሴው መሪዎች ሠራተኛው #አድማ እንዲመታ በማስተባበር ቀጥለውበታል” ያሉት ኮሚሽነሩ “የኢትዮጵያን አየርም ሆነ የአየር መንገዱን ዝና ጥያቄ ውስጥ የሚያስገቡ
መልዕክቶችን ለዓለምአቀፍ ድርጅቶች ሲያሠራጩ ቆይተዋል” ብለዋል።

©ዋዜማ ሬድዮ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል ፖሊስ‼️

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በህገ-ወጥ መንገድ ግለሰቦችን በመመልመል በጫካ ውስጥ ወታደራዊ ስልጠና ሲሰጡ የነበሩ 10 አሰልጣኞች #መያዛቸውን ፖሊስ ገለጸ፡፡

በክልሉ ህዝብ ላይ #ጥፋት ለመፈጸም በአሶሳ ወረዳ ገንገን ቀበሌ በጫካ ውስጥ ህገ-ወጥ ወታደራዊ ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ 51 #ተጠርጣሪዎች በቅርቡ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው ይታወሳል፡፡

የክልሉ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነር ኮማንደር ነጋ ጃራ ዛሬ ለኢዜአ እንዳስታወቁት በሕገ ወጥ መንገድ ስልጠና ሲሰጡ የነበሩት አሠልጣኞች ሰሞኑን በቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ህዝቡ አንዱ በሌላው ላይ እንዲነሳ ለማድረግ እየተፈፀሙ ያሉ ሴራዎችን መታገል አለበት"– የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት
.
.
የተለያዩ የአገሪቱ የፖለቲካ ጉዳዮችን ሌላ መልክ በመስጠት አንዱ በሌላው ላይ እንዲነሳና እርስ በእርሱ እንዲጋጭ ለማድረግ እየተፈፀሙ ያሉ ሴራዎችን መላው ህዝብ እንዲታገል የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት አቶ #ለማ_መገርሳ ጥሪ አቀረቡ።

የክልሉ ፕሬዚዳንት ጥሪውን ያቀረቡት በአዳማ ከተማ ዛሬ በተጀመረው 9ኛው የጨፌው ጉባኤ ላይ ከጨፌው አባላት በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለተነሱ ጥያቄዎች ምላሽ በሰጡበት ወቅት ነው።

አባላቱ በክልሉ ሰላም፣ የህግ የበላይነትን ማስከበር፣ ህገ-ወጥነትን በመከላከል፣ ክልሉ በአዲስ አበባ ላይ ካለው ጥቅም ጋር የተያያዘ እና ሌሎች በርካታ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ጥያቄ አንስተዋል።

የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ለማ በዚሁ ወቅት ህዝቡ ጠረፍ አካባቢ ይፈፀም የነበረውን የፖለቲካ #ሴራ ወደመሃል አገር ለማምጣት እየተደረገ ያለውን ጥረት ሊገታ ይገባል ብለዋል።

ህገ-ወጥነትን ለመከላከል የሚወሰደውን እርምጃ እንደአብነት ያነሱት አቶ ለማ የህዝቡን ጥቅም ማእከል አድርጎ የሚሰራ አመራር እና ህዝቡ ሌሎች በሚቀርፁለት አጀንዳ መመራት እንደሌለበት አስገንዝበዋል።

እንዲያም ሆኖ “ህገ-ወጥ ቤቶች ሲገነቡ ቁጭ ብሎ የሚመለከት አመራር እያለ ቤት እንዲፈርስ መደረጉ በራሱ #ጥፋት ነው” ሲሉም ገልፀዋል።

የቀበሌና የጎጥ አመራር እንዲሁም የከተሞቹ ካቢኔዎች ቤቶቹ ሲገነቡ ያለእነርሱ እውቅና መገንባታቸው፤ ከዚህም አልፎ ግንባታዎቹን በእጅ አዙር ህጋዊ ሲያስደርጉ በመቆየታቸው ግንባር ቀደም ተጠያቂ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

ኦሮሞ እና ኦሮሚያ በአዲስ አበባ ላይ ያላቸውን ጥቅም አስመልክቶ በተነሳው ጥያቄ ላይ ማብራሪያ ሲሰጡም ለውጡን ለመቀልበስ በዳራ አገር ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ቡድኖች አሁን በአዲስ አበባ ጉዳይ አንዱን በሌላው በማስነሳት እርስ በእርስ ለማበላላት የሚፈፅሙት ተግባር ስለሆነ ህዝቡ ጉዳዩን በጥንቃቄ ማየት እንዳለበት አሳስበዋል።

የአዲስ አበባ ጉዳይ በታሪክና በህገ-መንግስቱ መሰረት በምክክርና ህግን በተከተለ ሁኔታ ብቻ የሚፈታ እንደሚሆነም ነው አቶ ለማ ያብራሩት።

የልማት ፕሮጀክቶች መጓተት ዋነኛው ምከንያቶች የፋይናንሰ ችግር፣ የተቋራጮች አቅም ማነስ እንደሆነም አነሰተዋል።

የእነዚህ ሁለት ችግሮች ውጤት ተደማምሮ በልማት ፕሮጀክቶቹ ላይ ጫና ማሳደሩን የክልሉ ፕሬዚዳንት አቶ ለማ ተናግረዋል።

ከዚሀም በተጨማሪ የክልሉ መንግስት በሰላም ማስከበርና በተፈናቃዮች ጉዳይ ላይ መጠመዱ የልማት ፕሮጀክቶቹ ቁጥጥር እንዲላላ ማድረጉንም አንስተዋል።

በሰላም ማስፈን ተግባር ላይ የክልሉ መንግስት ከኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ) ጋር ሰላም ለማውረድ በትእግስት ያከናወነውን ተግባር እንደ ድል መቁጠር ይገባል ሲሉም ፕሬዚዳንቱ ገልፀዋል።

አስከ ነገ የሚቆየው ጉባኤው በአስፈጻሚ አካላት የተከናወኑ ስራዎችን ይገመገማሉ፣ አዋጆችን ይጸድቃል፤ ልዩ ልዩ ሹመቶችን ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሁኔታው አሁንም አሳሳቢ ነው...

በቤኔሻንጉል ጉሙዝ ብሔራዊ ክልል ያለው #የፀጥታ ሁኔታ አሁንም #አሳሳቢ መሆኑን አብመድ ያነጋገራቸው ነዋሪዎች እየገለጹ ነው፡፡ ከፓዊ ወረዳ ሕዳሴ ቀበሌ አባወረኛ አካባቢ ነዋሪዎች ለአብመድ እንደተናሩት ከትናንት ከሰዓት በኋላ ጀምሮ የተኩስ ልውውጥ #ቆሟል፤ ቀስት #የሚያስወነጭፍም የለም፡፡ ጥቃት አድራሾቹ በከፊል ወደ #ጫካ ውስጥ #ሸሽተዋል፤ በከፊልም በቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ ‹‹በዚህም ግልጽ የሚታይ ግጭት የለም፤ የሰላም ድባብ ግን #አይታይም›› ብለዋል፡፡

ሌላኛው ነዋሪ ደግሞ ከትናንት ምሽት 12፡00 አካባቢ ጀምሮ እስካሁን ግጨት አለመኖሩን ገልጸው ያንዣበበ #ስጋት መኖሩን አመልክተዋል፡፡ ትናንት ቤቶች መቃጠላቸውንና የተናገሩት እኚሁ አስተያየት ሰጪ ዛሬ ከሰዓት በኋላ #የአፀፋ እርምጃ ለመውሰድ ቅድመ ዝግጅት እንዳለ በመጠቆም መንግሥት #ጥፋት እንዳይደርስ እንዲቆጣጠር #አሳስበዋል፡፡ ‹‹ወንዶች ሚስቶቻቸውንና ልጆቻቸውን እያሸሹ ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ ነው፡፡ ትናንት ሙሉ በሙሉ ቤተሰባቸውን ከአካባቢው ያሸሹ ሰዎችም አሉ፤ የትናንቱ ጥቃት አድራሽ ቡድንም ዛሬም ለሌላ ጥፋት እየተንቀሳቀሰ በከፊል በቁጥጥር ሥር ሲውል ተመልክቻለሁ፡፡ ቀስትና የጦር መሣሪያ የያዙ ቡድኖች ወደ መንደር 49 እየተንቀሳቀሱ አባት በለስ ወንዝ ድልድይ ላይ መከላከያና የፌዴራል ፖሊስ ይዘዋቸዋል›› ብለዋል አስተያየት ሰጪው።

በበለስ ከተማ መንደር ሁለት ነዋሪ የሆኑ አስተያየት ሰጪም የጦር መሣሪያና ቀስት የያዙ ከ30 በላይ ሰዎች በለስ ወንዝ አካባቢ መከላከያ ሠራዊትና የፌዴራል ፖሊስ አባላት ዛሬ ረፋድ 3፡30 አካባቢ #ተይዘው መመለሳቸውን ተናግረዋል፡፡ ‹‹አባወረኛ ላይ ብዙ ነገር ወድሟል፤ የክልሉ መንግሥት ምን እንደሚያደርግ #አናውቅም፤ እንዲያውም የመንግሥት ባለስልጣናት ሴራ እንዳለበት እናምናለን፡፡ የምናደርገው ግራ ገብቶናል›› ብለዋል ነዋሪው፡፡

መንግሥት ግጭቶችን ከማብረድ በውጥን ላይ ማስቀረትን ትኩረት እንዲሰጥ ያሳሰቡት ነዋሪዎቹ የመከላከያና የፌዴራል ፖሊስ ኃይል በብዛት ወደ አካባቢው እንዲገቡና ለረዥም ጊዜ ቁጥጥር እንዲያደርጉ በተለይም ዛሬ ከሰዓት በኋላ እንደሚኖር የሚሰጋውን ጥቃት እንዲያከሽፉም ጠይቀዋል፡፡ ‹‹አሁን ግጭቱ ያለው ቀይና ጥቁር በሚል ነው፤ ልዩ ትኩረት ሰጥቶ የፌዴራል መንግሥት ዘላቂ መፍትሔ ካልፈለገ ሁኔታው አሳሳቢ ነው›› ብለዋል አስተያዬት ሰጭዎቹ፡፡

Via AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert

የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ድራማዊና አሳዛኝ ሂደቶችን አስተናግዶ ተጠናቋል አለ ፋሲል ከነማ የእግር ኳስ ስፖርት ክለብ፤ ክለቡ በይፋዊ የፌስቡክ ገፁም ተከታዩን መረጃ አሰራጭቷል፦

"የፋሲል ከነማ ስፖርት ክለብ ሽሬን ገና በ5ኛው ደቂቃ መምራት ቢጀምርም በደጋፊዎቻችን ላይ በደረሰው ጉዳት ውጥረት ላይ የገቡት ተጫዋቾቻችን በጥንቃቄ በመጫዎት መሪነታቸውን ቢያስጠብቁም በ70ኛው ደቂቃ #ጥፋት ተሰርቷል በማለት በፍፁም ጨዋታውን ካስጀመሩ በኃላ ፍፁም ቅጣት ምት የሰጡብን ሲሆን ከጎሉ መቆጠር በኃላ በደጋፊዎቻችን ላይ በደረሰው የድንጋይ ውርዋሮ ብዛት ያላቸው ደጋፊዎች #ጉዳት በማስታገሳቸው ጨዋታው ለበርካታ ደቂቃዎች ተቋርጦ የጀመረ ሲሆን በዛው 1ለ1 ተጠናቋል።"

በሌላ በኩል፦ ቡድኑ በይፋዊ የፌስቡክ ገፁ ባሰራጨው መረጃ እስካሁን ድረስ ደጋፊዎቼ ከስታዲየሙ #ሊወጡ አልቻሉም ብሏል።

የኢትዮጵያ ፕሪሜር ሊግ
🗞ቀን ሰኔ 30/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbaba

“ በእኛ የህግ አማካሪ በኩል ጥፋት ነበረ ” - ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው

በአዲስ አበባ ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ዋቢ ሸበሌ ሆቴል አጠገብ የሚገኘው፣ 90 ዓመት ያስቆጠረ፣  በታሪካዊ ቅርስነት መመዝገብ አለበት በሚል በፍርድ ቤት በኩል ጉዳዩ ተይዞ ነበር የተባለለት ሎሞባርዲያ ሬስቶራንት ሳይፈርስ እንዲቆይ ፍርድ ቤት ውሳኔ ቢሰጥም ሰሞኑን በግብረ ኃይሎች እንዲፈርስ መደረጉ ብዙዎቹን ቅር አሰኝቷቶ ተስተውሏል።

ሎሞባርዲያ እንዳይፈርስና እንዲቆይ ፍርድ ቤት ውሳኔ ካስተላለፈ የፈረሰበት ምክንያት ምን እንደሆነ ማብራሪያ እንዲሰጡ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ጥያቄ የቀረበላቸው የቅርስ ጥበቃ ባለስልጣንን ጠይቋል።

የተቋሙ ዋና ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አያሌው ለቀረበላቸው ጥያቄ፣ “በእኛ የህግ አማካሪ በኩል #ጥፋት ነበረ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

አክለውም፣ “ምክንያቱም የፍርድ ሂደቱ እንዴት ፕሮሰስ እንዳደረገ አላሳወቀንም። ከዚህ በፊት ሰበር እስከሚቀርብ ድረስ አሁን ያለን የህግ አማካሪ ነው ሲከራከር የነበረው። መመሪያ ስናጸድቅና ይህን ዲስከስ ስናደርግ፣ ለማኔጅመንት፣ ለውይይት ለባለሙያ ሲቀርብ ሁሉ ነበር” ብለዋል።

“መጨረሻ ላይ እኔን #‘ታስሮ ይቅረብ’ የሚል ፍርድ መጣ (አፈጻጸም ላይ ደርሶ ማለት ነው)። መጨረሻ ላይ ‘ምንድን ነው?’ ስንል ዶክሜንት ሲመጣ የህግ አማካሪው ያሉት ‘የተቋሙ ኃላፊ ናቸው እንጂ #መመሪያውም አይፈቅድም’ የሚል ነው” ሲሉ ሁነቱን አስረድተዋል።

ረዳት ፕሮፌሰር አበባው አክለውም፣ “መሀል ላይ ገባንና እኛ፣ ለፍርድ ቤት ይሄ ሁሉ አልደረሰም አንድ፣ ሁለተኛ አዋጁን ተንተርሰን በወጣ መመሪያ መሠረት ነው ውሳኔ የሰጠነው። ይሄ የዋና ዳይሬክተሩም ሳይሆን የባለሙያ ውሳኔ ነው” ብለው እንዳስረዱ ገልጸዋል።

“እሱን ከኬዙ ለጊዜው አስወጥተነዋል። ምክንያቱም አንድ የተቋም አማካሪ ወይም ነገረ ፈጅ የተቋሙን ውሳኔ ነው አይደል ማስከበር ያለበት!? መከራከር ያለበት!?” ያሉት አቶ አበባው፣ “እሱ በእኛ የሚሆነው ይሆናል” ነው ያሉት።

ዋና ዳይሬክተሩ የሎሞባርዲያን መፍረስ በተመለከተ ማብራሪያ በሰጡበት አውድ፣ “ለባለሙያ አውርደን አምና በዚህ ሰሞን ተመዘነ። ስለዚህ አላሟላም። ከመቶ ነው የሚመዘነው። ሲመዘን 38 ነጥብ ነው ያመጣው። ይሄ ማለት ቅርስ ብለን ልንይዝ አንችልም ማለት ነው” ብለዋል።

በቅርስነት እንዲቆይ (ላለመፍረስ) ሲመዘን ስንት ነጥብ ማምጣት ነበረበት? ተብሎ ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ለቀረበላቸው ጥያቄም፣ “ከ50 በላይ መሆን አለበት። ከ49 በታች ቅርስ ሊሆን አይችልም” የሚል ምላሽ ሰጥተው፣ የአቶ ጌትነትን ሞት በተመለከተ ተቋሙ ከለላ የማድረግ ኃላፊነት እንደደሌለው፣ በግለሰብ ደረጃ በሟቹ ሀዘን እንደተሰማቸው ተናግረዋል።

(ሬስቱራንቱ ከ100/38 አምጥቷል ያሉባቸውን እያንዳንዱን መለኪያ መስፈርቶች እንዲያስረዱና ሌሎች ተጨማሪ ማብራሪያ እንዲሰጡ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ጠይቋቸው የሰጡበትን የአቶ አበባውን ዝርዝር ሀሳብ በቀጣይ የምናቀርብ ይሆናል።)

ዘገባውን የላከው የአ/አ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል ነው።

@tikvahethiopia