TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሰበር ዜና‼️

#የህዝብ_ተወካዮች_ምክር_ቤት መስሪያ ቤቶች የጤና ተቋማትና የወጣቶች መዝናኛ በሚገኙባቸው አከባቢዎች 100 ሜትር ርቀት ውስጥ #ማጨስ የሚከለክልን ረቂቅ አዋጅ መርምሮ አጸደቀ፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ከአልኮል መጠጦች ጋር በተያየዘም ከ21 አመት በታች ለሆኑ ታዳጊዎች አልኮል #መሸጥ የሚከለክለውንም ረቂቅ አዋጅ በሙሉ ድምጽ #አጽድቋል፡፡

ማንኛውንም #የአልኮል_ምርት በብሮድካስት ሚድያ #ማስተዋወቅ የሚከለክለውን ረቂቅ አዋጅ ምክር ቤቱ በአብላጫ ድምጽ ወስኗል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እጩ ዋና ኮሚሽነር ተጠቋሚዎች የሚለዩባቸውን መመዘኛ መስፈርቶችና #የጥቆማ ጊዜ ይፋ ሆነ።

#የህዝብ_ተወካዮች_ምክር_ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ታገሰ ጫፎ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት እጩ ኮሚሽነር የጥቆማ ማቅረቢያ ጊዜ ከመጋቢት 1/07/2011ዓ.ም እስከ መጋቢት 20/07/2011ዓ.ም ድረስ በስራ ስዓት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

የእጩ ኮሚሽነር መመዘኛ መስፈርቶችም፦

•እድሜው/ዋ/ ከ 35 ዓመት በላይ የሆነ

•ከደንብ መተላለፍ ውጭ በሌላ የወንጀል ጥፋት ተከሶ ያልተፈረደበት

•ዜግነቱ/ቷ/ ኢትዮጵያዊ የሆነ

•በህግ ወይም አግባብ ባለው ሌላ ሙያ የሰለጠነ ወይም በልምድ ሰፊ እውቀት ያካበተ

•ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ተቆርቋሪ የሆነ

•ለህገ-መንግስቱ ተገዥ የሆነ

•ስራውን ለመስራት የሚያስችል የተሟላ ጤንንት ያለው

•በታታሪነቱ ፣ በስነ-ምግባሩና በታማኝነቱ መልካም ስም ያተረፈ
የትምህርት ዝግጅትን በተመለከተ

•ተጠቋሚው ያቀረበው ሰነድ / የልደት ዘመን፣ የትምህርት ማስረጃ፣ የስራ ልምድ እና cv /ግላዊ መረጃዎች/ ወዘተ በግብዓትነት ያቀርባል፡፡

•በቀጥታ በህግ፣ በሰብዓዊ መብት ትምህርቶች እንዲሁም በአመራር፣ ማኔጅመንት፣ ሰላምና ደህንነት፣ የስነ-ምግባርና ስነ-ዜጋ፣ የህዝብ አስተዳደር፣ ሳይኮሎጅ፣ ሶሾሎጅና ሶሻል ወርክ፣ የሰለጠኑ ሆነው ዲግሪና ከዚያ በላይ የትምህርት ደረጃ ያላቸው እንደሚሆኑ አቶ ታገሰ በመግለጫቸው ገልጸዋል።

አቅራቢ ኮሚቴ እስከ ሚያዚያ ወር መጨረሻ ድረስ አጠናቆ ለፓርላማ ሪፖርት ቀርቦ እንደሚፀድቅ የኢቢሲ ዘገባ ያመለክታል፡፡

ህዝቡ ከተጠቀሰው ቀን ጀምሮ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት እጩ ኮሚሽነር አቅራቢ ኮሚቴ በሚከተሉት ዘዴዎች ማቅረብ ይችላሉ ተብሏል፡፡
በስልክ 0111241036 ፤በፋክስ 0111241060 ፤ ኢሜል hprhumanright@gmail.comPo box:- 80001 መላክ ይቻላል ተብሏል፡፡

ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አምቦ ዝግጁ

የኦሮሚያና የአማራ ክልል #የህዝብ_ለህዝብ መድረክ የፊታችን እሁድ በአምቦ ከተማ ይካሄዳል፡፡

የኦሮሚያ ክልል መንግስት ኮሙዩኒከሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊ አቶ አድማሱ ዳምጠው ለfbc እንደገለጹት÷ ለውይይት መድረኩ በነገው ዕለት ከአማራ ክልል እንግዶቹ ወደ አምቦ ከተማ ያቀናሉ፡፡

በፍቼ በኩል ለሚገቡት ከአባይ ወንዝ ጀምሮ፣ በደብረ ብርሃን በኩል ለሚገቡት ደግሞ በየከተሞቹ አቀባበል እንደሚደረግላቸውም አቶ አድማሱ ተናግረዋል፡፡

መድረኩ የህዝብ ለህዝብ ትስስርን በማጠናከር ባልተገባ ትርክት ህዝብን ለማጋጨት የተወጠኑ ሴራዎችን በማክሸፍና ወንድምና እህት ህዝቦች በጋራ በመቆም ሀገራዊ ለውጡን ለማስቀጠል የሚያስችል መሆኑንም ነው ሃላፊው የተናገሩት፡፡

በውይይት መድረኩ ላይም የሁለቱ ክልልሎች ከፍተኛ አመራሮች የፌደራል መንግስትና ከሁለቱ ክልሎች የተወከሉ ተሳታፊዎች ይገኙበታል፡፡

የምስራቅ ሸዋ ዞንና የአምቦ ከተማም እንግዶቻቸውን ለመቀበል ቅድመ ዝግጅታቸውን ማጠናቃቸውን ገልጸዋል፡፡

Via #fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#KOBO የኢትዮጵያ መከላከያ " ቆቦ " ን ለቆ መውጣቱን መንግስት ገለፀ። የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚኒኬሽን ማምሻውን ባወጣው መግለጫ ፥ " አሻባሪው ህወሓት የሰው ኃይል ማዕበልን በመጠቀም የቆቦ ከተማን ከውጭ በብዙ አቅጣጫ እያጠቃ ነው " ብሏል። በሌላ በኩል ደግሞ በከተማ ውስጥ ሠርጎ ገቦችን በማሥረግ የሕዝቡን ደኅንነት አደጋ ውስጥ በሚያስገባ መልኩ የከተማ ውስጥ ውጊያ ለማድረግ የሚያስችል ሁኔታ እየፈጠረ…
#ወልድያ

የወልድያ ሕዝብ ተረጋግቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ መልዕክት ተላለፈ።

የወልድያ ከተማ አስተዳደር የከተማው ሕዝብ ተረጋግቶ አካባቢውን እንዲጠብቅ እና ለጥምሩ ጦር ደጀንነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ዛሬ ጥሪ አቅርቧል።

" የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ፋኖ እና ሚኒሻው እየተፋለሙ ነው "  ያለው የወልድያ ከተማ " የአካባቢው ማኅበረሰብ አካባቢውን ተረጋግቶ በመጠቅ ለጥምር ጦሩ የተለመደ ሁለተናዊ ደጀንነቱን አጠናክሮ ይቀጥል " ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

ከተማ አስተዳደሩ " የጦርነቱ የፍልሚያ ቦታ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ከራያ ሚዳ አልዘለለም " ያለ ሲሆን ሾልኮ ለማለፍና በወሬ ለመፍታት የተደረገው ስልትም እስካሁን አልሰመረም ብሏል።

የከተማ አስተዳደሩ ዛሬ መልዕክቱን ያሰራጨው የአካባቢውን ተጨባጭ ሁኔታ በአካላዊ እንቅስቅሴ ጭምር በማጣራት መሆኑን አመልክቷል።

ምንም እንኳን አሁንም መሳሪያ ወርዶ ችግሮች በሰላም እንዲፈቱ የሚቀርቡ የሰላም ጥሪዎች ከሀገር ውስጥ እና ከውጭ እየቀረቡ ቢሆንም በሰሜን ኢትዮጵያ ዳግም ያገረሸው ግጭት ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ መጥቷል። ህወሓት ከዚህ ቀደም ለሰብዓዊነት ሲባል ተኩስ አቁም በታወጀበት ወቅት ከነበረበት ቦታ ወደፊት በመምጣት የአማራ ክልል ቦታዎችን እየያዘ ነው።

በትላንትናው ዕለት በኢትዮጵያ መንግስት እንደተገለፀው የኢትዮጵያ መከላከያ ከቆቦ ከተማ ለቆ ወጥቷል፤ በዚህም ቆቦ በህወሓት ስር ይገኛል።

መንግስት ፤ ህወሓት #የህዝብ_ማዕበል ስልት በመጠቀም ጥቃት እያደረሰ መሆኑን በመግለፅ የህዝብ ከፍተኛ ፍጅት ለማስወገድ መከላከያው " ቆቦ " ን መልቀቁን በትለንትናው መግለጫ ማስረዳቱ ይታወሳል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Peace

የሰላም ስምምነቱን በተመለከተ ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ከሃይማኖት ተቋማት እና ሲቪክ ማህበራት ጋር ውይይት አድርገው ነበር።

በዚህ ውይይት ላይ ምን አሉ ?

- የሰላም ስምምነቱ #የህዝብ ፍላጎትን መሰረት ያደረገ ነው ብለዋል።

- የሰላም ስምምነቱ ፤ ከፍተኛ የሆነ ችግር ላይ ያለውን ህዝብ ለማዳንና ህዝቡ መሰረታዊ አገልግሎቶችን እንዲጠቀም ሰላም እንዲያገኝ ለማድረግ የተደረሰ መሆኑን ገልፀው ሌሎች ጉዳዮች በህገመንግስት መሰረት ፖለቲካዊ መፍትሄ የሚፈለግላቸው መሆኑን ገልፀዋል። ስምምነቱ ከምንም በላይ ተኩስ የማቆም ጉዳይ ነበር ሲሉ ተናግረዋል።

- የተደረሰው  የሰላም  ስምምነት  ተግባራዊ እንዲሆን እየተሰራ ባለበት በዚህ ወቅት ላይ አሁንም የኤርትራው ፕ/ት ኢሳያስ አፈወርቂ ኃይል በህዝቡ ላይ ከፍተኛ ግፍ እየፈፀመ፣ ንብረት እየዘረፈ ፣ እያወደመ መሆኑና ስምምነቱ እንዲደናቀፍ እየሰራ እንደሆነ ገልፀው የፌዴራል መንግስት የህዝቡን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነበት ስላለበት ኃላፊነቱን እንዲወጣ ጠይቀዋል።

- በስምምነቱ መሰረት ሰብዓዊ እርዳታ እና መድሃኒት እየገባ መሆኑን ተናግረዋል። " ስምምነቱ ላይ ድጋፍ በአቸኳይ እንዲገባ የሚል ነገር ነበር በወቅቱ ወዲያው የገባ ድጋፍ አልነበረም አሁን ግን ቀስ በቀስ የሚገባው ሰብዓዊ ድጋፍ እየጨመረ ነው " ብለዋል። እህል እና መድሃኒት ይዘው የሚገቡ ተሽከርካሪዎች እየጨመሩ መሆኑን የገለፁት ዶ/ር ደብረፅዮን ፤ ዓለም አቀፍ እርዳታ አቅራቢዎች በሙሉ ወደ እንቅስቃሴ ገብተዋል ብለዋል።

- ወደ ክልሉ ከሚገባው የሰብዓዊ እርዳታ ጋር በተያያዘ በስምምነቱ መጀመሪያ ሰሞን ላይ አስፈላጊው ስራ በጊዜ ስላላለቀ እና ባለመዘጋጀቱ ወደ ትግበራ እንዳልተገባ አሁን ላይ ግን ሁሉም ዝግጁ መሆኑን ፣ የሚያደናቅፍ ነገር እንደሌለው ፣ በመንገድ ላይ የነበረው በርካታ ፍተሻና የቁጥጥር ጣቢያዎች አሁን መስተካከሉን ተናግረዋል።

- ዶክተር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ፤ " የተቋረጡት መሰረታዊ አገልግሎቶች መልሰው አልተከፈቱም " ያሉ ሲሆን " በኛ በኩል ሙሉ ዝግጅት አድርገናል #ባንክ#ቴሌኮም እንዲጀምር ፤ የኤሌክትሪክ ኃይል ባለን አነስተኛ አቅም እየተጠቀምን ብንቆይም መስተካከል ያለባቸው ነገሮች መስተካከል አለባቸው። በፌዴራል አገልግሎት ሲሰጡ የነበሩ እያንዳንዳቸው ተፈትሸው ስራ ለመጀመር ምን ያስፈልጋቸዋል  ?  የሚለው ተጠንቷል። አገልግሎት ወደ ነበረበት ለመመለስ ሙሉ ዝግጅት ተደርጓል ፤ አሁን የሚቀረው ስርዓት አስይዞ ከፌዴራል አገልግሎት ሰጪ አካላት ጋር በመነጋገር በቅደም ተከተል ማስፈፀም ነው " ሲሉ ተናግረዋል።

@tikvahethiopia