TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሰበር ዜና‼️

#የህዝብ_ተወካዮች_ምክር_ቤት መስሪያ ቤቶች የጤና ተቋማትና የወጣቶች መዝናኛ በሚገኙባቸው አከባቢዎች 100 ሜትር ርቀት ውስጥ #ማጨስ የሚከለክልን ረቂቅ አዋጅ መርምሮ አጸደቀ፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ከአልኮል መጠጦች ጋር በተያየዘም ከ21 አመት በታች ለሆኑ ታዳጊዎች አልኮል #መሸጥ የሚከለክለውንም ረቂቅ አዋጅ በሙሉ ድምጽ #አጽድቋል፡፡

ማንኛውንም #የአልኮል_ምርት በብሮድካስት ሚድያ #ማስተዋወቅ የሚከለክለውን ረቂቅ አዋጅ ምክር ቤቱ በአብላጫ ድምጽ ወስኗል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት ኮሚሽን እጩ ዋና ኮሚሽነር ተጠቋሚዎች የሚለዩባቸውን መመዘኛ መስፈርቶችና #የጥቆማ ጊዜ ይፋ ሆነ።

#የህዝብ_ተወካዮች_ምክር_ቤት አፈ ጉባዔ አቶ ታገሰ ጫፎ ዛሬ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳስታወቁት ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት እጩ ኮሚሽነር የጥቆማ ማቅረቢያ ጊዜ ከመጋቢት 1/07/2011ዓ.ም እስከ መጋቢት 20/07/2011ዓ.ም ድረስ በስራ ስዓት መሆኑን አስታውቀዋል፡፡

የእጩ ኮሚሽነር መመዘኛ መስፈርቶችም፦

•እድሜው/ዋ/ ከ 35 ዓመት በላይ የሆነ

•ከደንብ መተላለፍ ውጭ በሌላ የወንጀል ጥፋት ተከሶ ያልተፈረደበት

•ዜግነቱ/ቷ/ ኢትዮጵያዊ የሆነ

•በህግ ወይም አግባብ ባለው ሌላ ሙያ የሰለጠነ ወይም በልምድ ሰፊ እውቀት ያካበተ

•ለሰብዓዊ መብቶች መከበር ተቆርቋሪ የሆነ

•ለህገ-መንግስቱ ተገዥ የሆነ

•ስራውን ለመስራት የሚያስችል የተሟላ ጤንንት ያለው

•በታታሪነቱ ፣ በስነ-ምግባሩና በታማኝነቱ መልካም ስም ያተረፈ
የትምህርት ዝግጅትን በተመለከተ

•ተጠቋሚው ያቀረበው ሰነድ / የልደት ዘመን፣ የትምህርት ማስረጃ፣ የስራ ልምድ እና cv /ግላዊ መረጃዎች/ ወዘተ በግብዓትነት ያቀርባል፡፡

•በቀጥታ በህግ፣ በሰብዓዊ መብት ትምህርቶች እንዲሁም በአመራር፣ ማኔጅመንት፣ ሰላምና ደህንነት፣ የስነ-ምግባርና ስነ-ዜጋ፣ የህዝብ አስተዳደር፣ ሳይኮሎጅ፣ ሶሾሎጅና ሶሻል ወርክ፣ የሰለጠኑ ሆነው ዲግሪና ከዚያ በላይ የትምህርት ደረጃ ያላቸው እንደሚሆኑ አቶ ታገሰ በመግለጫቸው ገልጸዋል።

አቅራቢ ኮሚቴ እስከ ሚያዚያ ወር መጨረሻ ድረስ አጠናቆ ለፓርላማ ሪፖርት ቀርቦ እንደሚፀድቅ የኢቢሲ ዘገባ ያመለክታል፡፡

ህዝቡ ከተጠቀሰው ቀን ጀምሮ ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብት እጩ ኮሚሽነር አቅራቢ ኮሚቴ በሚከተሉት ዘዴዎች ማቅረብ ይችላሉ ተብሏል፡፡
በስልክ 0111241036 ፤በፋክስ 0111241060 ፤ ኢሜል hprhumanright@gmail.comPo box:- 80001 መላክ ይቻላል ተብሏል፡፡

ምንጭ፦ ኢ.ፕ.ድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia