TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ማሳሰቢያ📌ውድ የአጠቃላይ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት /የ10ኛ ክፍል/ ተፈታኝ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች ከግንቦት
22-24/2010 ዓ.ም የኢትዮጵያ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሰርተፍኬት /የ10ኛ ክፍል ፈተና/ ለ1,200,676 ተማሪዎች እንዲሁም ከግንቦት 27-30/2010 ዓ/ም የኢትዮጵያ ዩንቨርስቲ መግቢያ ፈተና (የ12 ክፍል ፈተና) 284,312 ተማሪዎች መሰጠቱ ይታወሳል፡፡

የፈተናውን መሰጠት ተከትሎም ወደ እርማት ስራው በመግባት ከምንጊዜውም በፈጠነ መልኩ የ12ኛ ክፍል ውጤት በ24/11/2010
ዓ/ም ይፋ የተደረገ ሲሆን አስከትሎም የ10ኛ ክፍልን ወደ ማረም ሂደት ውስጥ ተገብቷል፡፡

እንደ 12ኛ ክፍሉ ሁሉ የ10ኛውም ፈተና ጥንቃቄ በተሞላበት ሁኔታ ከጥቃቅን የዳታ ማጥራት ስራዎች በስተቀር በሰላም እየተጠናቀቀ መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን፡፡ ከነሐሴ 25-30/2010 ዓ.ም ይለቀቃል ተብሎ ተደራሽ ተደርጎ የነበረውን መረጃ መሰረት በማድረግ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች የተለያዩ አሉታዊ መረጃዎች በመሰራጨት ላይ መሆናቸውን በመረዳታችን ከላይ በተገለጸው አግባብ የፈተና እርማቱ በሰላም #በመጠናቀቅ ላይ እንደሚገኝ እና በቀጣዮቹ #ጥቂት ቀናት ውስጥ ውጤቱ ይፋ እንደሚሆን እየገለጽን #በትዕግስት ትጠባበቁን ዘንድ መልዕክታችንን እናስተላልፋለን፡፡

የውጤቱን መለቀቅ አስመልክቶም ለተለያዩ ሚዲያዎች መግለጫ የምንሰጥ መሆኑን እናሳውቃለን!

መልካም ዕድል!

©NEAEA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ክልል የመሆን ጥንያቄ ህገ መንግስታዊ መብት ነው። ማንም ህዝብ ክልል ልሁን ብሎ መጠየቅና በህግ አግባብ ጉዳዩን ማስፈፀም መብቱ ነውና አትችልም መጠየቅ አንለውም፤ ህገ መንግስትን መብቱ ነውን ይሄን ህገ መንግስታዊ መብት ህጋዊ የሆነውን ጥያቄ በህጋዊ መንገድ ብቻ ነው መልስ ማግኘት የሚችለው።

ህጋዊ ጥያቄን በግርግር ከፈለክ ዘላቂ መፍትሄ አታመጣም፤ ፍትህ እንኳን ብታመጣ ርትዕ አታመጣም። ፍትህም ርትዕም Equally exercise ለማድረግ ከፈለገ አንድ ማህበረሰብ በህግ የጠየቀውን በህግ እስኪመለስ መጠበቅ ያስፈልጋል። ምን ማለት ነው፤ አንድ ክልል እራሱን በራሱ ማስተዳደር ሲፈልግ ያንን ጉዳይ የሚያስፈፅመው የምርጫ ቦርድ ነው።...ይሄ ተቋም በሁለት እግሩ ሳይቆም ክልል የመፍጠር ጉዳይ ብንሞክር ግን ፍላጎት ብቻ ነው የሚሆነው።

...አሁን ደቡብ አካባቢ ያለውን ነገር መንግስት በክብር ተቀብሏል። ደኢህዴን የሚባለው ክልሉን የሚያስተዳድረው ድርጅትም ጥያቄውን ተቀብሎ በህግ እየመረመረ ይገኛል። ደኢህዴን የመጨረሻ ውጤቱን እስከሚያሳውቅ፤ምርጫ ቦርድ ዝግጅቱን እስከሚያሳውቅ በደቡብ ክልል ውስጥ ክልል ለመሆን የጠየቃችሁ ህዝቦች በከፍተኛ ትዕግስት እንድትጠብቁን በዚሁ አጋጣሚ ጥሪ አቀርባለሁ።

ከህጋዊ መንገድ ውጪ ምንም አይነት ሙከራ ማድረግ ሱማሌ እንደሆነው ደቡብም ይሆናል፤ በኢትዮጵያ አንድነት የሚደራደር መንግስት የለም። ጥንቃቄ ያስፈልጋል። ተቀብለናል #በትዕግስት መጠበቅ! አልተቀበልንም ሲባል በህጋዊ መንገድ እናስተካክለዋለን። በዚህ መንገድ ቢታይ ጥሩ ነው በደቦ፣ በጩኸት የሚፈጠር ነገር ከእንግዲህ በኃላ ማስተናገድ ትዕግስታችን አልቋል። ሁሉም ስርዓትን ጠብቆ ይሄዳል፤ በስርዓት እንመልሳለን ያን የማይጠብቅ ከሆነ በተለመደው መንገድ እናስተካክለዋለን!" ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ~#ቲክቫህ
TIKVAH-ETHIOPIA
#ሰበር_መረጃ ቅዱስ ፓትርያርኩን ጨምሮ ብፁዓን አባቶች ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጋር ውይይት እያካሔዱ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሕዝብ ግንኙነት አስቸኳይ ሰበር መግለጫ ሰጥቷል። በመግለጫው ፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በየካቲት 2 ቀን 2015 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መሠረት ቤተ ክርስቲያኒቱ መግለጫውን ባወጣች 72 ሰዓታት…
#በትዕግስት_ተጠባበቁ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ማሳስቢያ !

ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩን ጨምሮ አበው ሊቃነ ጳጳሳትን ያካተተ ልኡክ በቤተ መንግሥት ከጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ጋር ውይይት እያካሄደ ይገኛል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት ፤ ሕዝበ ክርስቲያኑ አባቶች #የደረሱበትን_ውጤት_እስኪያሳውቁ ድረስ በትእግስት ይጠባበቅ ዘንድ አሳስቧል።

@tikvahethiopia
#ETHIOPIA #AU #AddisAbaba

አዲስ አበባ ከአፍሪካ ህብረት ጉባኤ ጋር በተያያዘ እንግዶቿን ተቀብላ እያስተናገደች ትገኛለች።

የጸጥታና ደህንነት የጋራ ግብረ ሃይል፤ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ በሰላም እንዲጠናቀቅ አስፈላጊው ቅድመ ዝግጅት አድርጌያለሁ፤ ስምሪትም በመውሰድ ስራ ላይ እገኛለሁ ብሏል።

በጉባኤው ለመሳተፍ ከተለያዩ ሀገራት የመጡና አሁንም የሚመጡ መሪዎችን እና ዲፕሎማቶችን ደህንነት  ለመጠበቅ በቂ ዝግጅት ማድረጉን አመልክቷል።

- በሆቴሎች፣
- በመዝናኛ እና በገበያ ስፍራዎች
- እንግዶቹ ከቦታ ቦታ በሚንቀሳቀሱባቸው አካባቢዎች ላይ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሆነም አሳውቋል።

የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ወንጀሎች እንዳይፈፀሙ እና ምንም አይነት የደህንነት ስጋት እንዳይኖር ከፀጥታ አካላቱ ጋር ተቀናጅተው በመስራት እንደወትሮው ሁሉ አስፈላጊውን ድጋፍና ትብብር እንዲያደርጉ የጋራ ግብረኃይሉ ጠይቋል፡፡

በተለይ #መንገዶች_ዝግ በሚደረጉበት ወቅት አሽከርካሪዎች እና እግረኞች #በትዕግስት በመጠበቅ ወይም ሌሎች አማራጭ መንገዶችን በመጠቀም ለሀገር ገፅታ ግንባታ ላይ የበኩላቸውን አስተዋፅኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርቧል።

አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙና የፖሊስ አገልግሎት ለማግኘት በስልክ ቁጥር ፦
👉 011-111-01-11፣
👉 011-552-63-03፣
👉 011-552-40-77፣
👉 011-554-36-78
👉 011-5-54-36-81 እንዲሁም በ987፣ 991 እና 816 ነፃ የስልክ መስመሮች ጥቆማ መስጠት ይቻላል ተብሏል።

@tikvahethiopia
" እስካሁን ውጤት አልተገለፀም " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2015 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ውጤት እስካሁን #አልተገለፀም ሲል አሳውቋል።

ተፈታኞችና መላው የትምህርት ማህበረሰብ #በትዕግስት እንዲጠባበቁ ጠይቋል።

ከሁለት ሳምንት በፊት በፀጥታና ሌሎች ምክንያቶች ፈተና ሳይወስዱ የቆዩ ተማሪዎች ፈተናቸውን መውሰዳቸው ይታወቃል።

የነዚህ ተማሪዎችን ፈተና ውጤት በሐምሌ 2015 ዓ.ም ከተፈተኑ ተማሪዎች ጋር አብሮ ይፋ ለማድረግ እየተሰራ እንደሚገኝ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

ከዚህ ቀደም " እስከ መስከረም መጨረሻ ድረስ ውጤቱ ይፋ ሊደረግ እንደሚችል " የአገልግሎቱ ከፍተኛ ኃላፊ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

@tikvahethiopia