TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.3K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#CHINA

ቻይና በኢትዮጵያ 🇪🇹 እየተሻሻለ መጥቷል ያለችውን የሀገር ውስጥ ሁኔታና መንግስት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ ቀነ ገደብ ከመድረሱ በፊት እንዲያበቃ ያሳለፈው ውሳኔ ደስ እንዳሰኛት ገልፃለች።

የኢትዮጵያ ህዝብ የውስጥ ጉዳዩን በአግባቡ የመቆጣጠር ጥበብና ብቃት እንዳለውም አምናለሁ ስትል አስታውቃለች።

@tikvahethiopia
#CHINA

ሹዌ ቢንግ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሆነው ተሾሙ።

#ቻይና በአሁኑ ወቅት በግጭት እየታመሰ ላለው የአፍሪካ ቀንድ ሹዌ ቢንግን ልዩ መልዕክተኛ አድርጋ መሾሟ ታውቋል።

ሹዌ ቢንግ ቀደም ሲል በፓፑዋ ኒው ጊኒ የቻይና አምባሳደር በመሆን አገልግለዋል። በአፍሪካ፣ በአሜሪካ እና በኦሺንያ የመሥራት ልምድ እንዳላቸው የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ዛሬ ማክሰኞ አስታውቋል።

@tikvahethiopia
#US #CHINA

ቻይና በአሜሪካ ውስጥ ያሉ ዜጎቿ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳሰበች።

በአሜሪካ የሚገኘው የቻይና ኤምባሲ በሀገሪቱ ያለው የደህንነት ሁኔታ ለቻይናውያን ዜጎች አሳሳቢ ነው ብሏል።

በመሆኑም አሜሪካ የሚገኙ ቻይናውያን ዜጎች ለግል ደህንነታቸው ጥንቃቄ ሊያደርጉ እንደሚገባ ኤምባሲው አሳስቧል።

በአሜሪካ የሚገኙ የቻይና ዜጎች እና የእሲያ ፊት ያላቸው ሰዎች ላይ የሚንፀባረወቅ ጥላቻ እየጨመረ መሆኑን ኤምባሲው ገልጿል።

በቻይና ዜጎች እና የእሲያ ፊት ያላቸው ሰዎች ላይ ሆን ተብሎ የሚፈፀሙ " ተንኮል አዘል " ጥቃቶች የቻይና ዜጎች ላይ ጉዳት እያስከተለ መሆኑንም ኤምባሲው አስታውቋል።

የጥቃቱ ሰለባ ከሆኑ መካከልም በቻይና የገንዘብ ድጋፍ እየተደረገላቸው በአለም አቀፍ ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎችን እና ሰራተኞችን እንደሚገኙበትም ጠቅሷል።

በቻይናውያን ዜጎች ላይ የሚፈፀሙ መሰል ጥቃቶች በአሜሪካ እየተበራከቱ መሆኑን ያስታወቀው ኤምባሲው፤ በአሜሪካ የሚገኙ የቻይና ዜጎች በሀገሪቱ ውስጥ በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ ለግል ደህንነታቸው ጥንቃቄ እንዲያድርጉ አሳስቧል።

መረጃውን ሮይተርስን ዋቢ አድርጎ አል ዓይን ኒውስ ነው ያስነብበው።

@tikvahethiopia
#CHINA #USA

ቻይና ለአሜሪካ ባለስልጣት የቪዛ አገልግሎት ላለመስጠት ወሰነች።

ይህ ውሳኔ አሜሪካ ለቻይና ባለሰልጣናት ቪዛ እንደማትሰጥ ከገለፀች በኃላ በቻይና የተሰጠ ተመሳሳይ የአፀፋ ምላሽ ነው።

አሜሪካ ሰኞ ዕለት በሚፈጸሙ የሰብዓዊ መብት ረገጣዎች ላይ እጃቸው አለበት ባለቻቸው የቻይና ባለስልጣናት ላይ ነው የቪዛ እገዳ ጥላ ነበር።

መረጃው የአል ዓይን ኒውስ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝታቸውን አጠናቀው ታይዋንን ለቀው ወጥተዋል። የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ እና በሀገሪቱ የስልጣን እርከን ሶስተኛ ሰው የሆኑት ናንሲ ፔሎሲ ታይዋን ጎብኝተዋል። ትላንት ታይዋን ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል። የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ብዙ ሲባልለት የነበረ እና በአሜሪካ እና ቻይና መካከል የፈጠረው ከፍተኛ ውጥረት ዓለምን ያሰጋ ነበር። ቻይና ፔሎሲ ወደታይዋን እንደሚመጡ…
#US #CHINA

" ቻይና ማንንም መከልከል አትችልም " - ፔሎሲ

" ሀገሬን የሚዳፈሩ ሁሉ ይቀጣሉ " - ቻይና

በአሜሪካ በስልጣን እርከን 3ኛዋ ሰው ናንሲ ፔሎሲ ከታይዋን ጉብኝታቸው በኋላ " ቻይና የዓለም መሪዎችን ወይም ማንንም ወደ ታይዋን እንዳይጓዙ መከልከል አትችልም " ሲሉ ተናግረዋል።

ቻይና ፤ ከፔሎሲ ጉብኝት በፊት ጉብኝቱ እንዳይደረግ ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያና ዛቻ ብታሰማም ፔሎሲ ወደ ታይዋን ገብተው ፤ ጉብኝት አድርገው ባለስልጣናትን አነጋግረው ሄደዋል።

ምንም እንኳን የፔሎሲ ጉብኝት ቢጠናቀቅም በቻይና እና አሜሪካ መካከል ያለው ውጥረት የቀጠለ ሲሆን ቻይና " ሀገሬን የሚዳፈሩ ሁሉ ይቀጣሉ " ስትል ዝታለች።

በሌላ በኩል ወደ ታይዋን ትልክ የነበረውን የተፈጥሮ አሸዋ መላክ ያቆመች ሲሆን ፍራፍሬና የዓሣ ምርቶችን ከታይዋን ማስገባት አቁማለች።

ታይዋን አካባቢ አሁንም የቻይና ወታደራዊ እንቅስቃሴ መቀጠሉ ተነግሯል።

@tikvahethiopia
#China

ኢትዮጵያ ፣ ኤርትራ እና ሱዳን ስለ ቻይና-ታይዋን ጉዳይ ምን አሉ ?

#ኢትዮጵያ

ሀገራችን ኢትዮጵያ የሰሞኑን የቻይና-ታይዋን ጉዳይ የተከሰተውን ውጥረት በትኩረት እየተከታተለች መሆኑን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር መለስ አለም ለኢዜአ ተናግረዋል።

አምባሳደር መለስ ፤ ኢትዮጵያ ለረጅም ዓመታት ስታራምድ የቆየችውን የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋሟን እንዳጸናች መሆኑን ተናግረዋል።

" የኢትዮጵያ የአንድ ቻይና ፖሊሲ አቋም ዛሬ የተጀመረ አይደለም ያሉት " አምባሳደር መለስ፤ " ከቻይና ጋር በነበረን ግንኙነት ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስታት አፅንተው የያዙት አቋም ነው " ብለዋል።

አሁንም ቢሆን ኢትዮጵያ ለ #አንድ_ቻይና ፖሊሲ ፅኑ አቋም አላት ያሉ ሲሆን ፖሊሲውን ኢትዮጵያ አባል የሆነችባቸው የተመድና የአፍሪካ ህብረት የሚያራምዱት አቋም መሆኑን ገልፀዋል።

#ሱዳን

ሱዳን ለአንድ ቻይና መርህ ድጋፏን እንደምትሰጥ አሳውቃለች። ታይዋንም የቻይና ግዛት አካል መሆኗን ገልጻለች።

ሱዳን ፤ ቻይና ሉዓላዊነቷን እና የግዛት አንድነትዋን በመጠበቅ ረገድ የምታደርገውን እንቅስቃሴ እንደምትደግፍም አስታውቃለች።

#ኤርትራ

ኤርትራ የአሜሪካ አፈጉባዔ ወደ ታይዋን ያደረጉት ጉዞ ከዓለም አቀፍ ህግና መርህ ያፈነገጠ ነው ብላለች።

የአፈጉባኤዋ ድርጊት የቻይና መንግስት ሉዓላዊነት ደንቦችን እና ድንጋጌዎች እንዲሁም " የአንድ-ቻይና " ፖሊሲ የሚጻረር እና የቻይናውያን ውህደት ሂደትን የሚያደናቅፍ ነው ስትል ገልፃለች።

ኤርትራ፤ አሜሪካ ቻይናን ለመቆጣጠርና ለመያዝ ጥረት እያደረገች ነው ብላ ድርጊቱ አጸያፊ ነው ብላለች።

#CGTN #ENA #AlAIN #Shabait

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የቦሪስ ጆንሰን ተተኪ ተመረጡ። የብሪታንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ሊዝ ትረስ አዲሷ የብሪታንያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተመርጠዋል። ትረስ እድሜያቸው 47 ሲሆን የቦሪስ ጆንሰን ተተኪ ሆነዋል። ሶስተኛዋ የሀገሪቱ ሴት ጠቅላይ ሚኒስትርም እንደሆኑ ተገልጿል። ትረስ ተፎካካሪያቸው የነበሩት ሪሺ ሱናክን ሲሆኑ ያሸነፉት 57.4% ድምፅ በማግኘት እንደሆነ ዶቼ ቨለ ዘግቧል። @tikvahethiopia
#UK #China

ሪሺ ሱናክ የዩናይትድ ኪንግደም ቀጣዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሊሆኑ ነው።

ሊዝ ትረስ በተሾሙ በሰባት ሳምንት ስልጣን በቃኝ ያሉ ሲሆን እሳቸውን ለመተካት በተደረገው ውድድር ሪሺ ሱናክ አሸናፊ ሆነዋል።

ሱናክ ፤ የዩናይትድ ኪንግደም #የመጀመሪያው " እስያዊ " ዝርያ ያላቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናሉ።

ጠ/ሚ ቦሪስ ጆንሰንን ለመተካት ከሰባት ሳምንታት በፊት በተደረገ ፉክክር ሪሺ ሱናክ ተወዳድረው የነበረ ቢሆንም በሊዝ ትረስ ሊሸነፉ ችለዋል።

ሊዝ ትረስ ' ግብር እቀንሳለሁ፤ ንግድን አሳልጣለሁ " ያሉት አዲስ ፖሊሲ ፍጹም ያልተጠበቀ የገበያ ምስቅልቅልና ብሔራዊ ጦስ ይዞባቸው መጥቶ ነው ሥልጣን እንዲለቁ የሆኑት።
 
ለ45 ቀናት ያህል ስልጣን ላይ የቆዩት ሊዝ ትረስ በዩናይትድ ኪንግደም ታሪክ ለአጭር ጊዜ የቆዩ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነው ተመዝግበዋል። 

በሌላ መረጃ ፥  የቻይና ገዥ የሆነው ኮሚኒስት ፓርቲ ትላንት ባደረገው ጉባኤ ዢ ዢንፒንግን ዋና ጸሓፊ አድርጎ መምረጡን ተከትሎ ለ3ኛ ጊዜ ስልጣናቸው ተራዝሟል።

የፓርቲው #ዋና_ጸሃፊ በሃገሪቱ የመሪነት ቦታ የሚያስገኝ ሲሆን መጋቢት በሚደረገው የብሄራዊ ህዝቦች ጉባኤ በይፋ ስልጣናቸው ይጸድቃል ተብሎ እንደሚጠበቅ ቢቢሲ አስነብቧል።

@tikvahethiopia
#China

ቻይና ከ3 ዓመታት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ድንበሯን #ለጎብኚዎች ከፍት አድርጋለች።

ቻይና በመጋቢት 2020 ዓ/ም የኮቪድ  19 ወረርሽኝን ተከትሎ ነበር የጉዞ እግድ የጣለችው።

ከአሁን በኃላ ገቢ መንገደኞች ማቆያ ስፍራ መቆየት ሳያስፈልጋቸው በቀጥታ መግባት ይችላሉ። ይሁንና ገቢ መንገደኞች #በ48_ሰዓታት ውስጥ የወሰዱትን የክትባት ማስረጃ ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ቢቢሲ ፅፏል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚንስትር ወደ ኢትዮጵያ (አዲስ አበባ) እንደሚመጡ ተሰምቷል። የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኪን ጋንግ በቅርቡ የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው የተሾሙ ሲሆን ወደ አዲስ አበባ የሚመጡት በአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ይፋዊ የሥራ ጉብኝት ለማድረግ እንደሆነ ተሰምቷል። ኪንግ ጋንግ የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ከመሾማቸው በፊት በአሜሪካ የቻይና አምባሳደር ሆነው አገልግለዋል።…
#ETHIOPIA #CHINA

የቻይና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቺን ጋንግ ኢትዮጵያ ይገኛሉ።

ሚኒስትሩ በኢትዮጵያ ይፋዊ የሆነ የሥራ ጉብኝት እያደረጉ እንደሚገኙ የተገለፀ ሲሆን ዛሬ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ በኃላ ከኢትዮጵያ ጠ/ሚ ዶ/ር ዐቢይ አህመድ እንዲሁም ከምክትል ጠ/ሚ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ጋር ተገናኝተው መክረዋል።

ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ከሚኒስትሩ ጋር ያደረጉትን ውይይት ተከትሎ ባሰራጩት አጭር ፅሁፍ ፤ " የሁለቱ ሀገራት ግንኙነት አሁንም ጸንቶ ቀጥሏል " ብለዋል። " የዛሬው ውይይት ይህንን እና በልማት የምንጋራውን ስልታዊ የጋራ ዓላማ፤ እንዲሁም አህጉራዊ እና ዓለም አቀፋዊ ትብብርን አጉልቶ አሳይቷል " ሲሉ ገልፀዋል።

የቻይናው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ከአቶ ደመቀ ጋር በተገናኙበት ወቅት የፖለቲካ ምክክር ማድረግ የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት እና ከፊል የዕደ ስረዛ ስምምነት ተፈርሟል።

ስምምነቱ የሁለቱን አገራት ጠንካራ ግንኙነትን ለማስቀጠል እና ወደ ተሻለ ደረጃ ለማሸጋጋር እንደሚረዳ ተገልጿል።

የቻይናው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በሁለትዮሽ ፣ቀጣናዊ እና በዓለም አቀፍ መድረኮች ቻይና ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር መስራቷን አጠናክራ እንደምትቀጥል አሳውቀዋል።

ቺን ጋንግ በቅርቡ ወደ ስልጣን የመጡ ሲሆን የመጀመሪያ ጉብኝታቸውን በ #ኢትዮጵያ እያደረጉ ናቸው።

መረጃው ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የተገኘ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#China ቻይና ከ3 ዓመታት በኋላ ለመጀመርያ ጊዜ ድንበሯን #ለጎብኚዎች ከፍት አድርጋለች። ቻይና በመጋቢት 2020 ዓ/ም የኮቪድ  19 ወረርሽኝን ተከትሎ ነበር የጉዞ እግድ የጣለችው። ከአሁን በኃላ ገቢ መንገደኞች ማቆያ ስፍራ መቆየት ሳያስፈልጋቸው በቀጥታ መግባት ይችላሉ። ይሁንና ገቢ መንገደኞች #በ48_ሰዓታት ውስጥ የወሰዱትን የክትባት ማስረጃ ማቅረብ እንደሚጠበቅባቸው ቢቢሲ ፅፏል። @tikvahethiopia
#Ethiopia 🛫 #China 

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ #ቻይና ሳምንታዊ የበረራ ምልልሱን ከፍ ሊያደርግ ነው።

በቻይና መንግስት ተጥለው የነበሩ የኮቪድ-19 ክልከላዎች መነሳታቸውን ይታወሳል።

ይህን ተከትሎ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከመጪው የካቲት ወር 2015 ዓ.ም ጀምሮ ቻይና ወደሚገኙ መዳረሻዎቹ የሚያደርገውን ሳምንታዊ የበረራ ምልልስ ከፍ በማድረግ አገልግሎት መስጠት የሚጀምር መሆኑን አየር መንገዱ ዛሬ አሳውቋል።

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

@tikvahethiopia
ቱርክ #ኢትዮጵያም ያለችበትን የBRICS ስብሰብ ትቀላቀል ይሆን ?

ባለፈው ሳምንት የቱርክ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሃካን ፊዳን የBRICS አባሏን ቻይናን ጎብኝተው ነበር።

በጉብኝታቸው ወቅት ከቻይና ባለስልጣናት ጋር መክረዋል።

በወቅቱ ሀገራቸው ቱርክ የBRICS ስብስብን የመቀላቀል ፍላጎት እንዳላት ተጠይቀው ፥ " በእርግጥም #እንፈልጋለን። ለምን አንፈልግም ? " ብለዋል።

" በእርግጥም ፤ የBRICS አባል መሆን እንፈልጋለን " ያሉት ፊዳን " ስለዚህ በዚህ አመት እንዴት እንደሚሄድ እናያለን " ሲሉ ተናግረዋል።

ተጨማሪ ነገር ከመናገር ግን ተቆጥበዋል።

አናዱሉ እንደዘገበው ደግሞ ቱርክ የBRICS  አባላት ሀገራትን ትብብር እየተመለከተች ነው።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ከሁለት ቀን በፊትም ወደ ሩስያ አቅንተው ከBRICS አባሏ ሩስያ ፕሬዜዳንት ቭላድሚር ፑቲን ጋር በዝግ በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ መክረዋል።

በBRICS አባል ሀገራት ስብሰባ ላይ ተገኝተዋል።

ፑቲን ከሚኒስትሩ ጋር በነበራቸው ስብሰባ ቱርክ ስብስቡን ለመቀላቀል (አብሮ ለመስራት) ያሳየችውን ፍላጎት በደስታ ተቀብለው ፤ ወደ ስብስቡ እንድትቀላቀል ሙሉ ድጋፋቸውን እንደሚሰጡ ገልጸዋል።

የቱርክ መንግሥት BRICS'ን ለመቀላቀል ርምጃ ይወስድ እንደሆነ እስካሁን የሚታወቅ ነገር የለም። ከዚህ ቀደም በይፋ ስብሰቡን ለመቀላቀል ያለውን ፍላጎት በይፋ አሳውቆ አያውቅም።

ቱርክ የ #NATO አባል ሀገር እንደሆነች ይታወቃል።

#BRICS+ ኢትዮጵያን ጨምሮ የሩስያ ፣ የብራዚል ፣ የቻይና ፣ የህንድ ፣ የደቡብ አፍሪካ ፣ የኢራን ፣ የግብፅ ፣ የዩናይትድ አረብ ኤሜሬትስ ስብስብ ነው።

#BRICS
#Turkey
#China
#Russia

@tikvahethiopia
#Ethiopia 🇪🇹 #Africa #China

የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ቻይና ውስጥ ተሰባስበዋል።

በቻይና የተሰባሰቡት ለቻይና አፍሪካ የመሪዎች መድረክ ነው።

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና ሉዑካቸው ቻይና ይገኛሉ።

ጠ/ሚ ዐቢይ (ዶ/ር) ፥ የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ ደማቅ አቀባበል እንዳደሩጉላቸው ገልጸዋል።

ጠቃሚ ውይይት ማድረጋቸውንም አመልክተዋል።

" ኢትዮጵያ የቻይናን ያልተቋረጠ ዘርፈብዙ ድጋፍ በእጅጉ ታደንቃለች። " ያሉት ጠ/ሚኒስትሩ " እንደ ሀገር የተለያዩ ተግዳሮቶችን ብናስተናግድም በግብርና፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ በኢንደስትሪ፣ በቱሪዝም፣ በቴሌኮሙኒኬሽን እና ሌሎች ዘርፎች ትርጉም ያላቸው የለውጥ ርምጃዎች ተራምደናል " ብለዋል።

" በዚህ የእድገት ጎዳና የቻይና ኢንቨስትመንቶች ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል ፤ በቱሪዝም ብሎም በወረቀት እና እንደ ፐልፕ ያሉ ተያያዥ ግብዓቶች ኢንደስትሪንም ለማሳደግ እምቅ አቅም አለ። " ሲሉ ገልጸዋል።

በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ትብብር የበለጠ ለማጠናከር እንደሚሰራ አረጋግጠዋል።

@tikvahethiopia