TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ይሄ ፊልም አይደለም!! የግጭት እና የጦርነት ውጤት መሬት ላይ ያለው እውነታ ነው!! ጦርነት እና ግጭት #ፌስቡክ ላይ #ተዘፍዝፎ እንደመለፍለፍ ቀላል ከመሰለህ ሶሪያ፣ የመን፣ ደቡብ ሱዳን ጎራ በል በጥይት ድምፅ ስትሳቀቅ፤ ያቀረብከውን ምግብ ለመብላት ሲያቅትህ፤ ብር ኖሮህ ምግብ ለመግዛት ከቤትህ ለመውጣት ሲከብድህ፤ መብራቱና ኔትዎርኩ ተቋርጦ ጨለማ ውስጥ ስትቀመጥ ያኔ #ግጭት እና #ጦርነት ትርፉ ምን እንደሆነ ይገባሃል!!
.
.
#ሰላም_ብቻዋን_ታዋጣለች!!
#TIKVAHETHIOPIA #ቲክቫህኢትዮጵያ

#ሼር #share
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ፈጣሪ ያውቃል⁉️

በረሐ እና ባሕር አቋርጠው ወደ ሳዑዲ አረቢያ የሚተሙት ኢትዮጵያውያን በየመን ጦርነት እንዳለ እንኳ አያውቁም። አንድ ወደ #ጅቡቲ የተሰደደ #የመናዊ በመንገድ ያገኟቸውን ኢትዮጵያውያን «ወዴት ነው የምትሔዱት? በመንገዳችሁ ጦርነት አለ ስንላቸው ፈጣሪ ያውቃል» የሚል መልስ ሰጡን ሲል ለኢኤንኤን ተናግሯል።

የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ድረ-ገፅ እደሚጠቁመው በየመን የርስ በርስ #ጦርነት

•5,900+ ሰላማዊ ሰዎች #ተገድለዋል

•9,400+ ሰላማዊ ሰዎች #ቆስለዋል

•3 ሚሊዮን ከመኖሪያ ቀያቸው #ተፈናቅለዋል

•22.2 ሚሊዮን ሕይወታቸውን ለማቆየት የለት ደራሽ ዕርዳታ #ጥገኛ ናቸው

•2.5 ሚሊዮን ሕፃናት ከትምህርት ገበታ እርቀዋል፤ ቢሆንም #ኢትዮጵያውያኑ ፈጣሪ ያውቃል እያሉ መንገድ ላይ ናቸው።

Via Eshet Bekele
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የፌስቡክ ጦረኞች...

#የቃላት_ጦርነትና እስጥ አገባ ከሮና ገሮ ሲያበቃና ሲበጠስ ነው ሀገራት ወደ #ጦርነት ውስጥ የሚገቡት፡፡ ለዚህም ይመስላል የቻይናው ከሚኒስት መሪ የነበሩት ማኦ ዜዱንግ ጦርነት የፖለቲካ ትግሉ በሌላ መልኩ ቀጣይነት ነው ያሉት፡፡ ማሕበራዊ ድረገጾች ከፍተኛ የኃሳብ ፍልሚያ የሚካሄድባቸው ከጦርነት ያልተናነሱ አውድማዎች ናቸው፡፡ የማሕበራዊው ሚዲያ ጥይት ባይጮህበትም ከመድፍና ታንክ በላይ #በሰው_ሕሊና ውስጥ የሚያጓራ ከሚሳኤልም በላይ ተምዘግዝጎ የሚወነጨፍ፣ የሚጮህና አናዋጭ፤ በስሜታዊነት የሚነዳ ለጥፋትም የሚያነሳሳ ነው፡፡ #ፌስቡክ የኃሳብ ፍልሚያና ግብግብ የሚካሄድበት ጎራ መሆኑ በጀ እንጂ ሌላማ ቢሆን የከፋ እልቂትና ውድመት ሊያመጣ ይችል የነበረ የዘመኑ ሚዲያ ነው፡፡

ሙሉውን ፅሁፍ ያንብቡ👇

https://telegra.ph/የፌስቡክ-ጦረኞች-03-04
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
ግልፅ የሆነ ጦርነት ውስጥ እንገባለን...

"....ሳታሸንፍ አሁን ባላደራ፤ ባደራ እንደሚባለው አይነት ጨዋታ ምትጫወት ከሆነ ግን ግልፅ የሆነ #ጦርነት ውስጥ እንገባለን ማለት ነው። ምክንያቱም... ለምሳሌ አዲስ አበባ የሆነ ሺ ሰው ሰብስቦ ባላደራ ካለ፤ ኦሮሚያም ይሄ ኦዲፒ የሚባል የኛ መንግስት አይደለም፤ ፍላጎቻችን ይሄ አይደለም ባለዳራ ነው #ተገንጥለናል ካለ ኢትዮጵያ አትኖርም፤ እንደዚህ አይነት ድራማ አያስፈልገንም።
.
.
የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ከየትኛውም ብሄር ብትሆኑ አሁን ያለው መንግስት መልካም ሲሰራ ደግፉት፤ መልካም ነገር ካልሰራ ንቀፉት፤ ነቅፋችሁ ማረም ካልቻለ በድምፅ በምርጫ ጣሉት፤ ከዛ ውጭ ያለ ድራማ ተገቢ አይደለም፤ #ወደማንፈልገው ነገር ያስገባናል ፕላስ የአዲስ አበባ ሰላምና ነፃነት ኦሮሚያ ሰላም ከሆነች፤ አማራም ሰላም ከሆነ፤ ደቡብ ...ትግራይም ሰላም ከሆነ ነው እንጂ አዲስ አበባ ብቻዋን የሆነ አምባሳደር ሹማ የሰላም ባለቤት መሆን አትችልም!" ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
በመጨረሻም መልዕክት ለቲክቫህ አባላት፦

#FightCOVID19

እያንዳንዳችን #ጦርነት ላይ እንደሆንን አምነን መቀበል ይኖርብናል። መዘናጋት የህይወት ዋጋ ነው የሚያስከፍለን። የኛ ጤና መሆን የምንወዳቸው፣ በዙሪያችን ያሉ ሰዎች ሁሉ ጤና መሆን ነው። የምናደርገውን በመጠንቀቅ እናድርግ። በጤና ባለሞያዎች የሚሰጠውንም ትዕዛዝ እናክብር!

ኮሮና ቫይረስ እስካሁን መድሃኒት አልተገኘለትምና በተሳሳቱ አረዳዶች ተዘናግተን ጦርነቱን እንዳንሸነፍ፣ እጃችንንም ለኮሮና ቫይረስ [ኮቪድ-19] እንዳንሰጥ አደራ! አደራ!

መንግስት ለህዝብ የሚሰጣቸው መረጃዎች ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያደርግ በዚህ አጋጣሚ እናስገነዝባለን። የሚሰጡት መረጃዎችም ወቅታቸውን የጠበቁ ቢሆን መልካም ነው።

ጦርነቱን ከፊት ሆነው ህይወታቸውን ሰጥተው የሚመሩት፣ የሚታገሉና የሚያታግሉት የጤና ባለሞያዎቻችን አስፈላጊው ሁሉ የህክምና ቁሳቁሶች እንዲሟላላቸው ካልተደረገ እጅግ በጣም ከፍተኛ ዋጋ መክፈላችን አይቀርምና ይታሰብበት!

ረጅም እድሜን ከጤና ጋር እንመኝላችኃለን!
ሰላም እደሩ!
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት፦

"ከምንም ነገር በላይ ኮቪድ-19ኝን ለመግታት የሚደረገውን #ጦርነት ከፊት ሆነው ለሚመሩት የጤና ባለሞያዎቻችን በቂ የህክምና ቁሳቁስ ካልተሟላ የሚከፈለው ዋጋ ከባድ ነው። በተለይ ደግሞ ከከተማ ውጭ ያሉ የጤና ባለሞያዎች ሁኔታ በእጅጉ ያሳስበናል።"

#FightCOVID19
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የአፋር ክልል "ህወሓት" ጦርነት ከፈተብኝ አለ። የአፋር ክልላዊ መንግስት ከደቂቃዎች በፊት ባወጣው መግለጫ በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ሽብርተኛ ድርጅት ተብሎ የተፈረጀው 'ህወሓት' ፥ "የሽብር ድርጊቱን ወደ አፋር በማስፋት የአፋር አርብቶ አደር ህዝብ ላይ ጦርነት ከፍቷል" ሲል ገልጿል። ክልሉ "ህወሓት" ጦርነት ከፈተብኝ ያለው በፈንቲ ረሱ ዞን ያሎ ወረዳ በኩል ነው። አፋር ክልል በመግለጫው ላይ ፥…
#Afar

ትላንት የአፋር ክልላዊ መንግስት በህ/ተ/ምክር ቤት ሽብርተኛ ድርጅት ተብሎ የተፈረጀው 'ህወሓት'፥ "የሽብር ድርጊቱን ወደ አፋር በማስፋት የአፋር አርብቶ አደር ህዝብ ላይ #ጦርነት ከፍቷል" ማለቱ ይታወሳል።

ክልሉ 'ህወሓት' ጦርነት ከፈተብኝ ያለው ፈንቲ ረሱ ዞን ያሎ ወረዳ በኩል ነው ፤ የክልሉ መንግስት የተከፈተበትን ጦርነት ከህዝብ ጋር በመተባበር እንደሚመክት መግለፁ አይዘነጋም።

የአፋር ክልል ሰላም እና አስተዳደር ቢሮም ትላንት ጧቱ 2 ሰአት ጀምሮ "ህወሓት" በያሎ ወረዳ በንጹሃን አርብቶአደሮች ላይ በከፈተዉ ድንገተኛ ጥቃት በሰዉና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን ሪፖርት አድርጓል።

ቢሮው፥ ህጻናትና ሴቶችን ጨምሮ አርብቶ አደሮች ላይ ጉዳት እንደደረሰ ያሳወቀ ሲሆን ቡድኑ የተለያዩ የግለሰብ ቤቶችን ላይ ዝርፊያ መፈፀሙን ገልጿል።

ህወሓት የከፈተውን ጥቃት ተከትሎ ወደስፋራዉ የደረሰዉ የአፋር ልዩ ሃይልና የአካባቢዉ ህብረተሰብ የመከላከል እርምጃዎችን በመውሰድ የቡድኑን አላማ ማክሸፍ መቻሉን አስረድቷል።

'ህወሓት' በአፋር ክልል በከፈተው ጥቃት ወደክልሉ ይጓጓዝ የነበረው የሰብዓዊ ድጋፍ ተስተጓጉሏል።

የህ/ተ/ም/ቤት ሽብርተኛ ብሎ የፈረጀው 'ህወሓት' አፋር ውስጥ ጥቃት መፈፀሙን አምኗል። ቡድኑ ጥቃት ፈፅመኩኝ ያለው የመንግሥት ደጋፊ ወታደሮች ላይ ነው።

አቶ ጌታቸው ረዳ ዛሬ ለAFP በሰጡት ቃል አፋር ክልል ውስጥ ጥቃት መፈፀማቸውን ገልፀው ጥቃቱ "ውስን ርምጃ ነበር" ብለዋል።

ጥቃቱ ያነጣጠረው በትግራይ እና አፋር ድንበር አካባቢ ተሰባስበው የነበሩ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ላይ ነበር ያሉት አቶ ጌታቸው፥ "ርምጃውን የወሰድነው እነዚህን ሃይሎች ወደ ኦሮሚያ እንዲመለሱ ለማድረግ ነበር፤ ይህም ተሳክቶልናል" ብለዋል።

telegra.ph/Afar-07-18

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ጎረቤት ሱዳኖች የጦርነት ጉሰማ ላይ ናቸው ! የሱዳን ጦር አዛዥ እና የሃገሪቱ ሉዓላዊ የሽግግር ምክር ቤት ሊቀመንበር ሌ/ጄ አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ከኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ የሚገኘውን የሃገራቸውን ጦር መጎብኛታቸው ተነግሯል። ቡርሀን ትንሹ ፋሻጋ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በሚገኙት አል ዑስራ እና ዋድ ኮሊ አካባቢዎች የሚገኘውን የሃገራቸውን ጦር ነው ዛሬ ሰኞ ሰኔ 20 ቀን 2014 ዓ/ም የጎበኙት፡፡…
#Update

በኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር እየተካሄደ ያለው ምንድን ነው ?

በምዕራብ ጎንደር ዞን የምዕራብ አርማጨሆ ወረዳ አስተዳዳሪ የሆኑት አቶ ደሳለኝ አያና ለቢቢሲ አማርኛ አገልግሎት የሰጡት ቃል ፦

- የሱዳን ሠራዊት በኢትዮጵያ በኩል ያሉ የድንበር አካባቢዎችን በከባድ መሳሪያ ደብድቧል። ድብደባው ለቀናት የዘለቀ ነው። እስከ ትላንት ማክሰኞ ከሰዓት ድረስ ሲደበድቡ ነበር።

- ነዋሪዎች ግጭቱ ሊባባስ ይችላል የሚል ስጋት አላቸው። አንዳንዶችም በአቅራቢያ ወዳሉ አካባቢዎች የመሄድ ሃሳብ አላቸው።

- ባለፉት ሶስት ቀናት በተፈጸመው የከባድ መሳሪያ ጥቃት #በሰው_ላይ_ጉዳት_አልደረሰም። የከባድ መሳሪያዎቹ በእርሻ ቦታዎችና የግብርና ካምፖች ላይ ጉዳት አድርሰዋል።

- በሱዳን የከባድ መሳሪያ ጥቃት ምክንያት ነዋሪዎች ባለፉት ቀናት በእርሻ ማሳቸው ላይ የተለመደውን የዕለት ከዕለት ሥራቸውን ከማከናወን ተቆጥበዋል።

- የንግድና የሥራ እንቅስቃሴ ተስተጓግሏል። ሱዳንና ኢትዮጵያ የሚገናኙበት የድንበር ከተማ የሆነችው የገለባት መተላለፊያ #ተዘግቷል

- የሱዳን ክስን ተከትሎ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን በሁለቱ አገራት ወታደሮች መካከል ከሰኞ ወዲህ #ጦርነት እየተካሄደ መሆኑን ሲዘግቡ የቆዩ ቢሆንም በአካባቢው ጦርነት አልተካሄደም፤ ያለው ሁኔታ ከሱዳን በኩል የሚፈጸመው የከባድ መሳሪያ ጥቃት ነው።

ያንብቡ : https://telegra.ph/BBC-06-29-2

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update በደቡብ አፍሪካ ፤ ፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት የኢትዮጵያ መንግስትን ወልክለው ፊርማቸውን ያኖሩት አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን ከዛሬው የናይሮቢው ስምምነት በኃላ ቃላቸውን ሰጥተው ነበር። አምባሳደር ሬድዋን ፤ ከዛሬው የቀጠለ ውይይት (በወታደራዊ ኃላፊዎች መካከል) የዛሬ ወር ገደማ (mid-December) በትግራይ ክልል መዲና #መቐለ ላይ ሊደረግ እንደሚችል ጠቁመዋል። ዋናውና የውይይቶቹ ፍፃሜ…
#Update

በኬንያ ናይሮቢ ከህወሓት አመራሮች ጋር ውይይት ላይ የቆየው እና በኢፌዴሪ ጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ የተመራው የመንግስት ልዑክ ዛሬ አዲስ አበባ ገብቷል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ወደ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ቃል ተከታዩን ብለዋል ፦

- የኢፌዴሪ መከላከያ ሠራዊት የተፈራረመውን የሰላም ስምምነት ለመተግበር ቁርጠኛ ነው።

- ለሰላም እና ለህዝቡ ስንል የተፈራረምንባትን #እንፈፅማለን ፣ ለተግባራዊነቱም #እንታገላለን

- በውይይቱ በተሻለ ሁኔታ መግባባት ላይ ተደርሷል።

- ከሀገራዊ ለውጡ በኋላ ኢትዮጵያ ብዙ ፈተናዎች ተፈትናለች ፤ ተገድዳ ወደ ጦርነት ገብታለች ፤ በተደረገው ውግያም በርካታ ውድመቶች ደርሰዋል።

- በርካታ የሰላም አማራጮች አምልጠዋል ፤ ከቅርብ ታሪኮቻችንን ተጠቅመን ወደ ቀደመ ሰላማችን ለመመለስ ዛሬ የተገኘውን የሰላም ንግግር ወደ ተግባር ለማውረድ ትልቅ ጥረት እየተደረገ ነው።

- ከዚህ በኋላ ይህን #ጦርነት ለመሸከም እንደ ኢትዮጵያ ማንም ጫንቃ የለም።

- የተበላሹ ነገሮች ወደ ነበሩበት እንዲመጡ መሠረት የጣለው የፕሪቶሪያው ስምምነት እና በናይሮቢ የተደረሰው ስምምነት የጋራ መግባባትን እንዲፈጠር ያደረገ ነው።

Credit : ኤፍቢሲ እና ኢብኮ

@tikvahethiopia
#አብን

የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ በዛሬው ዕለት በአማራ ክልል ወቅታዊ ሁኔታ ላይ መግለጫ አውጥቶ ነበር።

አብን በዚህ መግለጫው ፤ በየትኛውም አሰላለፍ እና አግባብ ስለአማራ ህዝብ የተሰለፉ ሀይሎች #ጦርነት ዘላቂ ጥቅምን ለማረጋገጥ አስቻይ እንዳልሆነ ሊገነዘቡት ይገባል ብሏል።

ይልቁን ጦርነት ህዝብን ለተደራራቢ የማህበራዊ ፣ ሰብአዊና ኢኮኖሚያዊ ድቀት ስለሚዳርግ ለሰላማዊ የፖለቲካ መፍትሄዎች ተገቢውን ስፍራ ሰጥተው ለክልሉ ሰላም መመለስ  ድርሻቸውን እንዲወጡ ሲል ጥሪ አቅርቧል።

" የአማራ ህዝብ ከሌላው የሀገሪቱ ህዝብ ጋር ያለውን የወንድማማችነት እሴቶች ከሚንዱ ቅስቀሳዎች ፣ በራሱ እና በልጆቹ የተመሰረቱ ተቋማትን በተለይም የሀገር መከላከያ ሰራዊት ከሚያጠለሹ መልዕክቶች እንዲሁም የአማራ ህዝብ ማህበራዊ ረፍት እንዲያጣ ከሚመኙ አካላት በስልት የሚሰጡትን አጀንዳዎች በመጸየፍ ወደ ሰላም መድረክ የሚያመሩ መንገዶችን ሁሉ ለመጥረግ አቅሙ የፈቀደውን ርብርብ እንዲያደርግ " ሲል አብን አሳስቧል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia
#አሜሪካ

" የዋሽንግተን አጠቃላይ የመሳሪያ ሽያጭ መጠን 238 ቢሊየን ዶላር ደርሷል " ተባለ።

አሜሪካ በፈረንጆቹ 2023 ከፍተኛ የጦር መሳሪያ ሽያጭ አስመዝግባለች።

" የዋሽንግተን አጠቃላይ የመሳሪያ ሽያጭ መጠን 238 ቢሊየን ዶላር ደርሷል " የተባለ ሲሆን፤  ይህም በ2022 ከነበረው የ50 በመቶ ብልጫ ማሳየቱ ተመላክቷል።

ለሽያጩ መጨመር የሩሲያ ዩክሬን #ጦርነት ከፍተኛ ድርሻ አለው የተባለ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ የአሜሪካ መከላከያ ኩባንያዎች ለውጭ ሀገራት በቀጥታ ያደረጉት ሽያጭ እንደሆነ ነው።

ፖላንድ የአሜሪካን የጦር መሳሪያ በመግዛት ቀዳሚ ሀገር እንደሆነች ለተቀናጀ የአየር እና የሚሳኤል መከላከያ የውጊያ ትዕዛዝ ስርዓትም 4 ቢሊየን ዶላር ማውጣቷ ተመላክቷል።

"አሜሪካ ለውጭ ያቀረበችው የጦር መሳሪያ ሽያጭ ባለፈው ዓመት በከፍተኛ ሁኔታ ጨምሯል ሲል ፖለቲኮ ዘግቧል፡፡

ተጨማሪ መረጃዎችን በዚህ ይከታተሉ ፦ https://publielectoral.lat/+LM-bJ8NzZMcxMjA8

@ThiqaMediaEth
ዘማሪ ሙሉቀን መለሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ።

ዘማሪው ወደ መንፈሳዊው ህይወት ሳይገባ በፊት ለረጅም ዓመታት ዘፋኝ የነበረ ሲሆን በሙዚቃ አድማጮች ዘንድ እጅግ ተወዳጅ የሆኑ ስራዎች ነበሩት።

ሙሉቀን መለሰ የዘፈንን ህይወት እርግፍ አድርጎ ከተወ እና ዘማሪ ከሆነ በኃላ የተለያዩ የመዝሙር ስራዎችን ለወንጌል አማኞች አቅርቧል።

ዘማሪው ከሀገር ወጥቶ አሜሪካ መኖር ከጀመረ ረጅም ዓመታት ያለፈው ሲሆን በዛው ባለበት ሀገር አሜሪካ ነው ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው።

ከዘማሪ ሙሉቀን መለሰ ስራዎች አንዱ ፦

ኢትዮጵያ !

" ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያ ፈጥነሽ እጆችሽን ወደ እግዚአብሔር ዘርጊ፤
በመከራሽ ዘመን የሚረዳሽ አምላክሽ ነውና ወደእርሱ ተጠጊ።

አድገዋል አውቀዋል ያልሻቸው #ልጆችሽ
ሁሉም እሾህ ሆነው እየወጉ #አደሙሽ
የአንድነት ማሰሪያው መቀነት ይኑርሽ ይኑርሽ፤
እግዚአብሔር ነይ ይላል ወደእሱ ተመለሽ።

#ጦርነት #ረሃብ #ስደት ደርሶብሻል፤
ችግር በየፈርጁ ተፈራርቆብሻል፤
በመከራሽ ብዛት የአፍረት ማቅ ለብሰሻል፤
የሚታደግ አዳኝ ኃያል ብሩት አጥተሻል።

ኢትዮጵያ ፈጥነሽ እጆችሽን ወደ እግዚአብሔር ዘርጊ፤
በመከራሽ ዘመን የሚረዳሽ አምላክሽ ነውና ወደእርሱ ተጠጊ። "

#TikvahEthiopia

@tikvahethiopia
#Sudan #Ethiopia

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፤ ሱዳን ከኢትዮጵያ በቀን የምትወስደው የኤሌክትሪክ ኃይል ከ200 ሜጋዋት ወደ 50 ሜጋዋት መውረዱን ገለጸ።

በእርስ በርስ ጦርነት ውስጥ ያለችው ሱዳን ከኢትዮጵያ የምትወስደው የኤሌክትሩክ ኃይል በእጅጉ መቀነሱን ተነግሯል፡፡

ሱዳን #ጦርነት_ውስጥ_ከመግባቷ_በፊት ከኢትዮጵያ የምትገዛው የኤሌክትሪክ ኃይል በቀን እስከ 200 ሜጋዋት የነበረ ሲሆን አሁን ላይ ግን 50 ሜጋዋት እና ከዚያ በታች ሆኗል ሲል አገልግሎቱ አስረድቷል፡፡

ለሱዳን የሚቀርበው ኃይል ከመውረዱም በላይ " ለተጠቀሙት የኤሌክትሪክ ኃይል እየከፈሉ አይደለም " ብሏል።

በታሰረው ውል መሰረት #ለተጠቀሙበት_ካልከፈሉ አገልግሎቱን ማቋረጥ የሚቻል ቢሆንም ግንኙነቱ እንዳይሻክር ኢትዮጵያ ይህንን አላደረገችም ሲል ገልጿል።

ኢትዮጵያ ከሱዳን ከጅቡቲ እና ከኬኒያ የኃይል ትስስር ያላት ሲሆን በቀን እስከ ሁለት ቴራ ዋት ሀወር ለሶስቱ ሀገራት ኃይል እንምድታቀርብ ተነግሯል።

ጅቡቲ የምትጠቀመው የኤሌክትሪክ ኃይል አብዛኛው ከኢትዮጵያ የሚሄድ ሲሆን ኬኒያም ከምትጠቀመው የኤሌክትሪክ ኃይል 10 ከመቶ ከኢትዮጵያ የሚሄድ ነው ተብሏል፡፡

#ShegerFM

#Sudan #Ethiopia

@tikvahethiopia