TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በቴፒ በተፈጠረው ግጭት የሞቱት ሰዎች ቁጥር 3 መድረሱን የከተማው ነዋሪዎች ገልፀውልናል።

#ከመንግስት አካላት ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ጥረት እናደርጋለን።

©G
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በደቡብ ጎንደር ህገ ወጥ የጦር መሳሪያ ሲያዘዋውሩ የነበሩ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡

ህገ ወጥ የጦር መሳሪያዎችን እና የመገበያያ ገንዘቦችን የያዙ ግለሰቦች በተደረገ የፖሊስ ፍተሻ አንዳቤት ከተማ ላይ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የአንዳቤት ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ገልጿል።

ግለሠቦቹ ከጎንደር ጭነው ሲመጡ መጋቢት 10/2013 ዓ.ም ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት አንዳቤት ከተማ ላይ በተደረገ ፍተሻ ፦

- ከ1 ሽህ 500 በላይ ጥይቶች፣
- 3 ክላሽንኮቭ መሳሪያ ፣
- 1 ካዝናና 37 ሽህ700 ብር በቁጥጥር ስር እንደዋለ ፖሊስ አሳውቋል።

መሳሪያውን ሲያዘዋውሩ የተያዙት 3 ግለሰቦች እና የመኪና አሽከርካሪው በቁጥጥር ስር ውለው የማጣራት ስራ እየተሰራ ነው።

ግለሰቦቹ የሃሰት መረጃ በመያዝ ለማጭበርበር ሙከራ አድርገዋል ተብሏል።

የአንዳቤት ወረዳ የሰላምና ደህንነት ጽህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ሲሳይ እንየው ግለሰቦቹ የያዙት ህገ ወጥ ጥይት #ከመንግስት_ካዝና ጭምር የወጡ እንደሆነ መረጃው የሚያመላክት መሆኑን በመጥቀስ ግለሰቦቹም ህጋዊ ነን በማለት ለማጭበርበር ሙከራ አድርገዋል ብለዋል፡፡

መንግስት እንደዚህ አይነት ተግባር በሚፈፅሙ ግለሰቦች ላይ አስተማሪ የሆነ ርምጃ መውሰድ እንዳለበት የተጠቆመ ሲሆን
የሚመለከተው አካል የፍተሻና የቁጥጥር ስራውን አጠናክሮ መቀጠል አለበት ተብሏል።

አሽከርካሪዎች የሚጭኑትን እቃ በደንብ በመፈተሸ ከተጠያቂነትና ከህገ ወጥ ስራዎች ራሳቸውን መቆጠብ አለባቸው ተብሏል።

መረጃውን ከአንዳቤት ወረዳ ኮሙዩኒኬሽን ነው ያገኘነው።

@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#ሸገር

" እየፈረሱ ያሉት ቤቶች #አሁንም በመንግስት መዋቅር ዉስጥ ባሉ ሃላፊዎች ይሁንታ የተሰሩ ስህተቶች መሆናቸዉን እናምናለን " ሲሉ የሸገር ከተማ ከንቲባ አስታወቁ፡፡

በቅርቡ የተቋቋመውን የሸገር ከተማ ተከትሎ በተለይ ከቤት ፈረሳ ጋር ተያይዞ በርካታ ቅሬታዎች ከመነሳታቸው ባሻገር ዜጎች በመንግስት አካላት ፍቃድ ቤቱን እንደገነቡ ቢገልጹም መፍትሄ ማግኘት እንዳልቻሉ ይገለጻል፡፡

ፍቃዱን የሰጡ የመንግስት አካላት አሁንም በሃላፊነት ቦታ ላይ ሆነው የዜጎች ቤት እንዲፈርስ እያደረጉ ነው የሚለው ቅሬታም በተደጋጋሚ ጊዜ ይነሳል፡፡

ይህን ጉዳይ አስመልክቶ ከአሃዱ መድረክ ጋር ቆይታ ያደረጉት የሸገር ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ተሸመ አዱኛ  ፤ ባለፈው የመንግስት መዋቅር ውስጥ በነበሩ የስራ ሃላፊዎች ስህተት ቤቶቹ እንደተሰሩ እንደሚያምኑ አስታዉቀዋል፡፡

#አሁንም እነዛ ሃላፊዎች በመንግስት መዋቅር ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን በመግለጽ ሆኖም ግን ለሰሩት ስህተት እርምጃ አለመወሰዱ ጥያቄ እያሥነሳ ቢሆንም ካለፈው ይልቅ ስለ ወደ ፊቱ በማሰብ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ያለዉ መሰል ስህተቶች እንዳይደገሙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ቤት እየፈረሰባቸው ያሉ ዜጎች ለሚያነሱት ጥያቄ ምንም እንኳን በከተማዋ አስተዳደር ህገ ወጥ ስለሆናችሁ ነው የሚል ምላሽ ቢሰጣቸውም #ከመንግስት_አካላት ፍቃድ አግኝተው እንደሰሩ እየገለጹ ያሉ ግን በርካቶች ናቸው፡፡

Credit : Ahadu Mederk

@tikvahethiopia