#ሸገር

" እየፈረሱ ያሉት ቤቶች #አሁንም በመንግስት መዋቅር ዉስጥ ባሉ ሃላፊዎች ይሁንታ የተሰሩ ስህተቶች መሆናቸዉን እናምናለን " ሲሉ የሸገር ከተማ ከንቲባ አስታወቁ፡፡

በቅርቡ የተቋቋመውን የሸገር ከተማ ተከትሎ በተለይ ከቤት ፈረሳ ጋር ተያይዞ በርካታ ቅሬታዎች ከመነሳታቸው ባሻገር ዜጎች በመንግስት አካላት ፍቃድ ቤቱን እንደገነቡ ቢገልጹም መፍትሄ ማግኘት እንዳልቻሉ ይገለጻል፡፡

ፍቃዱን የሰጡ የመንግስት አካላት አሁንም በሃላፊነት ቦታ ላይ ሆነው የዜጎች ቤት እንዲፈርስ እያደረጉ ነው የሚለው ቅሬታም በተደጋጋሚ ጊዜ ይነሳል፡፡

ይህን ጉዳይ አስመልክቶ ከአሃዱ መድረክ ጋር ቆይታ ያደረጉት የሸገር ከተማ ከንቲባ ዶ/ር ተሸመ አዱኛ  ፤ ባለፈው የመንግስት መዋቅር ውስጥ በነበሩ የስራ ሃላፊዎች ስህተት ቤቶቹ እንደተሰሩ እንደሚያምኑ አስታዉቀዋል፡፡

#አሁንም እነዛ ሃላፊዎች በመንግስት መዋቅር ውስጥ የሚገኙ መሆናቸውን በመግለጽ ሆኖም ግን ለሰሩት ስህተት እርምጃ አለመወሰዱ ጥያቄ እያሥነሳ ቢሆንም ካለፈው ይልቅ ስለ ወደ ፊቱ በማሰብ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ያለዉ መሰል ስህተቶች እንዳይደገሙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ቤት እየፈረሰባቸው ያሉ ዜጎች ለሚያነሱት ጥያቄ ምንም እንኳን በከተማዋ አስተዳደር ህገ ወጥ ስለሆናችሁ ነው የሚል ምላሽ ቢሰጣቸውም #ከመንግስት_አካላት ፍቃድ አግኝተው እንደሰሩ እየገለጹ ያሉ ግን በርካቶች ናቸው፡፡

Credit : Ahadu Mederk

@tikvahethiopia