TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሁንም ጥንቃቄ📌 ከዝህ በፊት ብያለሁ። አሁንም ደግሜ እላለሁ! ከትናንሽ አጀንዳዎች እንዉጣ። ስለ ምልክት ሳይሆን ስለሀገር ከልብ እናስብ! #ሀገር ካለች #ባንዲራ መስቀል እና #ሀዉልት መገንባት አይከብድም! ሀገር #ከሌለ ግን ባንዲራ ብቻዉን ትርጉም የለዉም! አሁን #ሊቢያ ወይም #የመን ላይ ባንዲራ መያዝ ወይም ሀዉልት መትከል ምን ያደርጋል? ችግራችን በባንዲራ ወይም በሀዉልት አይፈታም። የግጭት ነጋዴዎችን ሴራ እናክሽፍ።

ጆሮ ያለዉ ይስማ!
.
.
Ammas of eeggannoo📌

Kanaan duras jedheera. Ammas irran deebi'a! Ajandaa xixinnoo keessaa haa baanu. Waan mallattoo dhiifnee waan biyyaa onnee irraa haa yaannu! Biyyi yoo jiraatte alaabaa fannisuu fi siidaa dhaabuun hin dhibu. Yoo biyyi hin jirre garuu alaabaan qophaatti hiika hin qabu! Amma #Liibiyaa ykn #Yemen keessatti alaabaaqabatuun ykn siidaa dhaabuun maal godha? Rakkoon keenya alaabaa ykn siidaan hin hiikkatu! Shira diinaa haa fashalsinu!

Dubbii kana qalbisaa!

©አቶ ታዬ ደንደአ (የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አሁንም ጥንቃቄ📌 ከዝህ በፊት ብያለሁ። አሁንም ደግሜ እላለሁ! ከትናንሽ አጀንዳዎች እንዉጣ። ስለ ምልክት ሳይሆን ስለሀገር ከልብ እናስብ! #ሀገር ካለች #ባንዲራ መስቀል እና #ሀዉልት መገንባት አይከብድም! ሀገር #ከሌለ ግን ባንዲራ ብቻዉን ትርጉም የለዉም! አሁን #ሊቢያ ወይም #የመን ላይ ባንዲራ መያዝ ወይም ሀዉልት መትከል ምን ያደርጋል? ችግራችን በባንዲራ ወይም በሀዉልት አይፈታም። የግጭት ነጋዴዎችን ሴራ እናክሽፍ።

ጆሮ ያለዉ ይስማ!
.
.
Ammas of eeggannoo📌

Kanaan duras jedheera. Ammas irran deebi'a! Ajandaa xixinnoo keessaa haa baanu. Waan mallattoo dhiifnee waan biyyaa onnee irraa haa yaannu! Biyyi yoo jiraatte alaabaa fannisuu fi siidaa dhaabuun hin dhibu. Yoo biyyi hin jirre garuu alaabaan qophaatti hiika hin qabu! Amma #Liibiyaa ykn #Yemen keessatti alaabaaqabatuun ykn siidaa dhaabuun maal godha? Rakkoon keenya alaabaa ykn siidaan hin hiikkatu! Shira diinaa haa fashalsinu!

Dubbii kana qalbisaa!

©አቶ ታዬ ደንደአ (የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር)

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሊቢያ

የዓረፋ በዓልን ምክንያት በማድረግ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲደረግ ተጠየቀ!

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሊቢያ ተፋላሚ ሃይሎች የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያደርጉ ጥሪ አቀረበ፡፡ ተፋላሚዎቹ የኢድ አል አድሃ(ዓረፋ) በዓልን ምክንያት በማድረግ የተኩስ አቁም ስምምነት እንዲያደርጉ ነው በመንግስታቱ ድርጀት ጥሪ የቀረበው፡፡

እስከ ዛሬ ምሸት ድረስም ሁለቱ ተፋላሚዎች ጥሪውን ስለመቀበል አመቀበላቸው ለመንግስታቱ ድርጅት የሊቢያ መልዕክተኛ የጽሁፍ ማረጋገጫ ያቀርባሉ ተብሎ ይጠበቃል። ከአውሮፓውኑ ሚያዚያ ወር ጀምሮ በጄኔራል ከሊፋ ሃፍጣር የሚመራው ሃይል የሊቢያን መዲና ትሪፖሊን ለመቆጣጠር በሚያደርገው ዘመቻ በተመድ እውቅና ከተሰጠው የፋይዝ አል ሳራጅ አስተዳደር ጋር ግጭት ውስጥ ገብቷል።

በዚህ ግጭት ሳቢያም ከ1 ሺህ በላይ ዜጎች ህይወት ሲያልፍ 5 ሺህ 700 ያህሉ ለአካል ጉዳት ዳርጓል፡፡ ከዚህም ሌላ 120 ሺህ ያህል ነዋሪዎችን ከመኖሪያ ቀያቸው ማፈናቀሉን የዓለም ጤና ድርጅት መረጃ ያመላክታል፡፡

ምንጭ፡- ሲ ጂ ቲኤ ን/fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በሊቢያ የመጀመሪያው ሰው ከቫይረሱ አገገመ!

አንድ (1) ሞትና አስራ ዘጠኝ (19) በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች የተመዘገቡባት #ሊቢያ በትላንትናው ዕለት የመጀመሪያውን ከኮሮና ቫይረስ ያገገመ ሰው ሪፖርት አድርጋለች።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አሜሪካ የተሳተፈችባቸው ጦርነቶች ...

በ21ኛው ክፍለ ዘመን የዓለም ኃይል እንደሆነች የሚነገርላት አሜሪካ በበርካታ ሀገራት ውስጥ በተደረጉ ጦርነቶች እጇን አስገብታለች።

በጥቂቱ...

#አፍጋኒስታን

አል-ቃይዳ መስከረም 11 ቀን 2001 በአሜሪካን ላይ ጥቃት ከሰነዘረ በኋላ አሜሪካ ታሊባንን ከስልጣን ለማስወገድ አሜሪካ የአፍጋኒስታንን ወረራ መርታለች። 20 ዓመታት የዘለቀ እጅግ ዋጋ ያስከፈለ ጦርነት ነበር። በመጨረሻ ግን ታሊባን ወደቦታው ተመለሰ። አሜሪካም ጓዛን ጠቅልላ ወጣች።

#ኢራቅ

በፕሬዚዳንት ጆርጅ ቡሽ ዘመን አሜሪካ እ.ኤ.አ. በ 2003 ኢራቅን በመውረር ሳዳም ሁሴን ከሥልጣን አስነስታለች። በኢራቅ ጦርነት በርካቶች አልቀዋል፣ ከፍተኛ ውድመት ደርሷል። ኢራቅ ዛሬም አስተማማኝ ሙሉ ሰላም የላትም። ለዳግም ግንባታም ደፋ ቀና እያለች ነው።

#የድሮን_ጥቃቶች

አሜሪካ ሽብርን ለመዋጋት በሚል በፓኪስታን፣ የመን፣ ሱማሊያ፣ ሊቢያ የድሮን ጥቃቶችን ፈፅማለች (አሜሪካ ከፍተኛ የሰራዊት ቁጥር አላሰፈረችም)።

እነሊቢያ፣የመን፣ ሱማሊያ በጦርነት ምስቅልቅላቸውን አውጥቶት ዛሬም ማገገም ያልቻሉ ለደህንነት አስጊ ሀገራት ሆነው ቀርተዋል።

#ሊቢያ

የአሜሪካና የአውሮፓ አጋሮች እኤአ በ 2011 በሊቢያ የአየር ዘመቻ ከፍተው ነበር ፤ ጥቃቱ ሙአመር ጋዳፊ በአረብ አብዮት ለመቃወም በተነሳሱ ተቃዋሚዎች ላይ የደረሰውን ግፍ ለመከላከል በሚል ነው ፤ የእነ አሜሪካ መዘቻ ጋዳፊን አወረደ ፣ ሊቢያ ግን ወደ ትርምስና ቀውስ ገባች፤ ዛሬም እዛው ናት።

አሜሪካ እጇን ባስገባችባቸው ሀገራት ትክክለኛ ውሳኔ እንደሆነ የምትሞግት ሲሆን በምታካሂዳቸው ዘመቻዎች ከሽብር ጥቃት ዜጎቿን መከላከል /የሀገሯን ደህንነት ማስጠበቅ እንደቻለች በተለያየ ጊዜ ታነሳለች።

@tikvahethiopia
አሜሪካ የተሳተፈችባቸው ጦርነቶች ...

#Repost

በ21ኛው ክፍለ ዘመን አሜሪካ በበርካታ ሀገራት ውስጥ በተደረጉ ጦርነቶች እጇን አስገብታለች።

በጥቂቱ...

#አፍጋኒስታን

አል-ቃይዳ መስከረም 11 ቀን 2001 በአሜሪካን ላይ ጥቃት ከሰነዘረ በኋላ አሜሪካ ታሊባንን ከስልጣን ለማስወገድ አሜሪካ የአፍጋኒስታንን ወረራ መርታለች። 20 ዓመታት የዘለቀ እጅግ ዋጋ ያስከፈለ ጦርነት ነበር። በመጨረሻ ግን ታሊባን ወደቦታው ተመለሰ። አሜሪካም ጓዟን ጠቅልላ ወጣች።

#ኢራቅ

በፕሬዚዳንት ጆርጅ ቡሽ ዘመን አሜሪካ እ.ኤ.አ. በ 2003 ኢራቅን በመውረር ሳዳም ሁሴን ከሥልጣን አስነስታለች። በኢራቅ ጦርነት በርካቶች አልቀዋል፣ ከፍተኛ ውድመት ደርሷል። ኢራቅ ዛሬም አስተማማኝ ሙሉ ሰላም የላትም። ለዳግም ግንባታም ደፋ ቀና እያለች ነው።

#ሊቢያ

የአሜሪካና የአውሮፓ አጋሮች እኤአ በ 2011 በሊቢያ የአየር ዘመቻ ከፍተው ነበር ፤ ጥቃቱ ሙአመር ጋዳፊ በአረብ አብዮት ለመቃወም በተነሳሱ ተቃዋሚዎች ላይ የደረሰውን ግፍ ለመከላከል በሚል ነው ፤ የእነ አሜሪካ መዘቻ ጋዳፊን አወረደ ፣ ሊቢያ ግን ወደ ትርምስና ቀውስ ገባች፤ ዛሬም እዛው ናት።

#ሶሪያ

አሜሪካ ከሌሎች አጋሮቿ ጋር ሆና በሶሪያ ጦርነት ውስጥም እጇ ያለበት ሲሆን በሶሪያ የሚንቀሳቀሱ የበሽር አል አሳድ ተቃዋሚዎችን ለማጥፋት በምትወስደው እርምጃ የሶሪያ ከተሞች ክፉኛ አውድማለች።

#የድሮን_ጥቃቶች

አሜሪካ ሽብርን ለመዋጋት በሚል በፓኪስታን፣ የመን፣ ሱማሊያ፣ ሊቢያ የድሮን ጥቃቶችን ፈፅማለች (አሜሪካ ከፍተኛ የሰራዊት ቁጥር አላሰፈረችም)።

እነሊቢያ፣የመን፣ ሱማሊያ ጦርነት ምስቅልቅላቸውን አውጥቶት ዛሬም ማገገም ያልቻሉ ለደህንነት አስጊ ሀገራት ሆነው ቀርተዋል።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ፎቶ ፦ " የአፍሪካ ሃገራት ቻምፒዮና/ቻን " እየተባለ በሚጠራው የአፍሪካ ሀገራት ውድድር ላይ ተሳታፊ የሆነው የሀገራችን ብሔራዊ ቡድን ለውድድሩ ዝግጅት ዛሬ ሞሮኮ ካዛብላንካ በሰላም መድረሱን የቲክቫህ ስፖርት ቤተሰብ አባላት አሳውቀዋል። ቡድኑ ወደ ሞሮኮ ከመሄዱ በፊት በሀገር ውስጥ ልምምድ ሲያደርግ ቆይቷል። በሞሮከ የብሔራዊ ቡድኑ ዝግጅት ለሚቀጥሉት ስምንት ቀናት የሚያደርግ ሲሆን የፊታችን ቅዳሜ…
#Update

የአፍሪካ ሃገራት ቻምፒዮና / CHAN AFRICA እየተባለ በሚጠራው የአፍሪካ ሀገራት ውድድር ላይ ተሳታፊ የነበረው የሀገራችን ብሔራዊ ቡድን ከምድቡ ማለፍ ሳይችል ቀርቷል።

ብሄራዊ ቡድኑ #ከሞዛምቢክ#አልጄሪያ እና #ሊቢያ ጋር በአንድ ምድብ ነበር የተደለደለው። ከሞዛምቢክ 0 ለ 0 ሲለያይ በአልጄሪያ 1 ለ 0 ተሸንፎ ነበር።

በምድብ የመጨረሻው ጨዋታ #ከሊብያ ጋር የገጠመው ብሔራዊ ቡድናችን 3 ለ 1 በሆነ ውጤት ተሸንፎ ከወዲሁ ከውድድሩ ተሰናብቷል።

ቡድኑ በውድድሩ ላይ በአጠቃላይ 4 ጎሎች ሲቆጠሩበት ማስቆጠር የቻለው አንድ ጎል ብቻ ነው።

በተመሳሳይ ምድብ ውስጥ የነበሩት አልጄሪያ እና ሞዛምቢክ ከምድቡ ማለፋቸውን አረጋግጠዋል።

የዘንድሮው የአፍሪካ ሃገራት ቻምፒዮና እየተካሄደ የሚገኘው በአልጄሪያ ነው።

ተጨማሪ : https://publielectoral.lat/+VvwzStMNcNHmhK0x    

@tikvahethiopia
#ሊቢያ

በምስራቃዊ ሊቢያ የምትገኘውን " ዴርና " ከተማን በመታው ኃይለኛ አውሎ ንፋስ እና ጎርፍ ምክንያት 2000 የሚደርሱ ሰዎች ሳይሞቱ እንዳልቀረ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን እየዘገቡ ይገኛሉ።

7000 ሰዎችም የገቡበት አይታወቅም ተብሏል።

በቤንጋዚ የሚገኘው የቀይ ጨረቃ ኃላፊ ካይስ ፋከሪ እንደተናገሩት " ዳንኤል " በተባለው አውሎ ንፋስ በዴርና ከተማ ባደረሰው ጥፋት ቢያንስ 150 ሰዎችን ሞተዋል።

በከተማዋ ሁለት ግድቦች መደርመሳቸውም ተነግሯል።

ከቀናት በፊት በሌላኛዋ የአፍሪካ ሀገር #ሞሮኮ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ ከ2000 በላይ ሰዎች ሞተዋል።

@tikvahethiopia
#IOM

" በቅርብ ከደርሱት #አስከፊ አደጋዎች አንዱ ነው " - የተመድ የስደተኞች ድርጅት

ስደተኞችን ይዞ ሲጓዝ የነበረ ጀልባ በሊቢያ ባሕር ዳርቻ ተገልብጦ፣ ሕፃናትና ሴቶችን ጨምሮ ከ60 ሰዎች በላይ መሞታቸውን የተመድ የስደተኞች ድርጅት አስታውቋል።

ቅዳሜ የደረሰው አደጋ፣ ወደ #አውሮፓ ለመሻገር በሚሹ ስደተኞች ላይ በሜዲትሬንያን ባሕር ላይ በቅርቡ ከደርሱት አስከፊ አደጋዎች አንዱ ነው ተብሏል።

የተመድ ዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት (IOM) እንዳለው፣ 86 ሰዎችን ይዛ ስትጓዝ የነበረው ጀልባ፣ ከፍተኛ ማዕበል ገጥሟት በሊቢያ ምዕራባዊ ባሕር ዳርቻ በምትገኘው " ዙዋካ " ከተሰኘች ከተማ አቅራቢያ ስትገለበጥ 61 ሰዎች #ሰምጠዋል

ድርርቱ ማዕከላዊው የሜዲትሬንያን ባሕር፣ ለፍልሰተኞች አደገኛ የጉዞ መሥመር መሆኑ ቀጥሏል ብሏል።

#ሊቢያ በጦርነት በመታመስ ላይ ያለች አገር ብትሆንም፣ ከአፍሪካ እና ከመካከለኛው ምሥራቅ፣ #ሁከትን እና #ድህነት በመሸሽ ወደ አውሮፓ መሻገር ለሚፈልጉ ስደተኞች ተመራጭ መተላለፊያ ሆናለች፡፡

የስደተኞች ድርጅቱ እንደሚለው፣ በመጠናቀቅ ላይ ባለው የፈርንጆች 2023 ብቻ ከ2 ሺሕ 500 በላይ ፍልሰተኞች ወደ አውሮፓ ለመሻገር ሲሞክሩ በባሕር ላይ #ሕይወታቸውን_አጥተዋል

መረጃው የቪኦኤ ነው።

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
የግብፁ መሪ ምን አሉ ? የግብፁ ፕሬዜዳንት አብዱል ፈታህ አልሲሲ ከሶማሊያው ፕሬዝዳንት ጋር የሁለቶሽ ምክክር ካደረጉ በኃላ በጋራ ሆነው መግለጫ ሰጥተው ነበር። በዚህም ወቅት የግብፁ መሪ ፤ " የአረብ ሊግ ቻርተር በሉዓላዊነታቸው እና በግዛታቸው ላይ ጥቃት የሚደርስባቸውን የአረብ ሀገራት እንድንከላከል ያስገድደናል " ሲሉ ተደምጠዋል። " ግብፅ በሶማሊያ ደህንነት ላይ ምንም አይነት ስጋት እንዲፈጠር…
ራስ ገዟ ሶማሌላንድ ስለ ግብፅ ምን አለች ?

" በስምምነቱ ዙሪያ የሚነሱ ማንኛውንም የውጭ #ጣልቃገብነቶችን እንቃወማለን " - ሶማሌላንድ

ዛሬ የራስ ገዟ ሶማሌላንድ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል መግለጫ አውጣለች። በዚህ መግለጫም ስለ ለሰሞነኛው የግብፅ ሁኔታ ምላሽ ሰጥታለች።

ምን አለች ?

ሶማሌላንድ ፤ ከግብፅ ጋር ያላትን ታሪካዊ ግንኙነት ከፍ አድርጋ እንደምትመለከት ገልጻ በአፍሪካ ቀንድ መረጋጋት ላይ ያላትን ስጋትም እውቅና እንደምትሰጥ ገልጻለች።

" ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከተከሰቱ ክስተቶች አንፃር ቀጠናዊ ጉዳዮችን በውይይት እና በትብብር ለመፍታት ያለኝን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጣለሁ " ብላለች።

ይሁን እንጂ በሶማሌላንድ ሪፐብሊክ እና በ #ኢትዮጵያ 🇪🇹 መካከል ከተፈረመው የመግባቢያ ስምምነት (MoU) በኋላ የሚነሱ ማንኛውንም አይነት የውጭ #ጣልቃገብነቶችን እንድምትቃወም በድጋሚ አረጋግጣለች።

በመግለጫዋ ፤ " የሶማሌላንድ ሪፐብሊክ እንደ አንድ ሉዓላዊ ሀገር በተቋቋሙ ዓለም አቀፍ ማዕቀፍ ውስጥ ያሉትን ሁሉንም ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቶች አከብራለሁ " ስትል ገልጻለች።

" ሁሉም ፍላጎት ያላቸው አካላት ቀጠናዊ መረጋጋትን እና ገንቢ አጋርነትን በማስፈን ላይ እንዲያተኩሩ አበረታታለሁ " ያለችው ሶማሌለንድ ፤ " በዚህ መንፈስም #ግብፅ በቅርብ ጎረቤቶቿ እንደ ፦
* #ሱዳን
* #ሊቢያ
* #ጋዛ ያሉ ግጭቶችን ለመፍታት ዲፕሎማሲያዊ አቅጣጫዋን እንድትቀይር እናበረታታታለን " ብላለች።

" እነዚህ አካባቢዎች (ሱዳን፣ ሊቢያ፣ ጋዛ) በአሁኑ ጊዜ ጉልህ ከሆኑ ተግዳሮቶች ጋር #እየታገሉ ነው ፤ እናም የግብፅ ገንቢ ተሳትፎ ለዘላቂ ሰላም እና ደህንነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደርጋል ብለን እናምናለን " ስትል ገልጻለች።

የሶማሌለንድ መንግሥት በአፍሪካ ቀንድ ሰላምና ልማትን ለማስፈን ከሁሉም ሀገራት ጋር ዲፕሎማሲያዊ ውይይቶችን እና ትብብርን ያደርጋል ስትል አሳውቃለች።

" የጋራ ጂኦፖለቲካዊ አካባቢያችንን ሁኔታ ለማሻሻል ከግብፅ እና ከሌሎች ተባባሪዎች ጋር #በመከባበር እና #በጋራ_ጥቅም ላይ የተመሰረተ ገንቢ ግንኙነትን ለመፍጠር እንሰራለን " ስትል ገልጻለች።

@tikvahethiopia
#IOM

" እ.ኤ.አ ከ2014 እስከ 2023 ቢያንስ 63,285 ሰዎች ሞተዋል / የገቡበት አይታወቅም " - IOM

እ.ኤ.አ. ከ2014 እስከ 2023 ባለው ጊዜ ውስጥ ቢያንስ 63,285 ሰዎች በዓለም ላይ ባሉ ስደተኞች በሚጓዙበት መስመር ህይወታቸውን አጥተዋል ወይም ጠፍተዋል።

አብዛኞቹ ህይወታቸውን ያጡት ደግሞ በውሃ መስጠም ምክንያት ነው።

እንደ ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (አይኦኤም) ሪፖርት መሰረት 28,854 ሰዎች የሞቱት እና የት እንደገቡ ያልታወቀው በሜዲትራኒያን ባህር ላይ ነው።

ከተመዘገቡት የሟቾች ቁጥር ወደ 60 በመቶ የሚጠጋው ከመስጠም ጋር የተያያዘ ሲሆን ከየት እንደሆነ ከተለዩት ውስጥ ደግሞ ከአንድ ሶስተኛ በላይ የሚሆኑት በግጭት ውስጥ ካሉ ሀገራት ማለትም ፦
- አፍጋኒስታን፣
- ማይንማር፣
- ሶሪያ
- #ኢትዮጵያ የሄዱ ናቸው።

ከባለፉት አስርት ዓመታት ውስጥ ለስደተኞች በጣም ገዳይ እና የከፋ የነበረው 2023 ሲሆን 8,541 ሞት ተመዝግቧል።

ዓመቱ በሜዲትራኒያን ባህር በከፍተኛ ሁኔታ ሞት የጨመረበትም ነው።

እጅግ በርካታ አፍሪካውያን የተሻለ ኑሮ ፍለጋ በሚል በህገወጥ መንገድ እጅግ አስከፊ በሆነ መንገድ ወደ #ሊቢያ ሄደው በባህር ተጉዘው አውሮፓ ለመግባት በሚያደርጉት ጥረት የባህር ሲሳይ ሆነው ቀርተዋል።

እንደ ዓለም አቀፍ ተቋማት መረጃ ፥ አስከፊው ጉዞ አድርገው እድለኛ ሆነው በህይወት ዛሬም ድረስ መረጋጋት ወደሌላት #ሊቢያ የሚገቡ ከሆነ እገታ ፣ ስቃይ ፣ ድብደባ  አለፍ ሲልም ግድያ ሊፈፀምባቸው ይችላል።

በኃላም በባህር ጉዞ ከሊቢያ አውሮፓ ለመግባት በሚያደርጉት ጉዞ ህይወታቸውን ያጣሉ።

#ቲክቫህኢትዮጵያ
@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
" 480 ስደተኞች #በሊቢያ የባህር ጠረፍ ላይ ተይዘዋል " - IOM ባሳለፍነው ሳምንት ብቻ 480 ስደተኞች በሊቢያ የባህር ጠረፍ ላይ መያዛቸው ተነግሯል። የዓለም አቀፍ የስደተኞች ድርጅት/IOM ሰኞ'ለት ባወጣው መግለጫ 480 ስደተኞች በባህር ላይ ጠባቂዎች መያዛቸውን አስታውቋል። ድርጅቱ "ከመጋቢት 24 እስከ 30,2024 ውስጥ 480 ስደተኞች ተይዘው ወደ ሊቢያ ተመልሰዋል " ነው ያለው። ከተያዙት…
#ሊቢያ #ግሪክ

እንደ ጣሊያን የባሕር ጠረፍ ጥበቃ መረጃ ፥ ባለፈው ሳምንት የሜዲትሬንያን ባሕርን አቋርጠው ወደ #አውሮፓ ለመሻገር በመሞከር ላይ የነበሩ ፍልስተኞች ጀልባቸው ተገልብጦ 1 ህጻንን ጨምሮ 9 ሰዎች ሞተው አስክሬናቸው ተገኝቷል።

15 የሚሆኑ ፍልሰተኞች የደረሱበት አይታወቅም። 22 ሰዎችን ደግሞ መታደግ ተችሏል።

ከላምፔዱሳ ደሴት 50 ኪ.ሜ. ላይ ማዕበል በማየሉ ነው አደጋው የደረሰው። ላምፔዱሳ ወደ አውሮፓ ለመሻገር ለሚሞክሩ ፍልሰተኞች የመጀመሪያ ማረፊያ ነች፡፡

በሌላ በኩል ፤ ባለፈው ሳምንት ግሪክ የ3 ታዳጊዎችን አስከሬን ስታገኝ ፤ 19 ፍልሰተኞችን ደግሞ ታድጋለች።

ፍልሰተኞቹ ይጓዙበት የነበረው ጀልባ ከቋጥኝ ጋራ በመጋጨቱ አደጋው ሊደርስ የቻለው።

ግሪክ ከአፍሪካ፣ እስያ እና መካከለኛው ምሥራቅ ወደ አውሮፓ ለመሻገር ለሚሹ ፍልሰተኞች አማራጭ ናት።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia