TIKVAH-ETHIOPIA
1.48M subscribers
56.4K photos
1.4K videos
202 files
3.83K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
#HawassaUniversity #StopHateSpeech

እናት ሀገር ኢትዮጵያ
ኢትዮጵያ የኛ መመኪያ


የTIKVAH-ETH የStopHateSpeech የዩኒቨርሲቲ እንቅስቃሴዎችን በዚህ የዩትዩብ ቻናላችን ማግኘት ትችላላችሁ፦ https://www.youtube.com/channel/UCbHAotwR_yPhyv5lliObk6w
#HawassaUniversity

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ከቀን 08-12/2012 ዓ/ም ትምህርት አይኖርም በማለት አንድ አንድ ተማሪዎች የተሳሳተ መረጃ እያሰራጩ መሆኑን ደርሼበታለሁ፤ እንዲያህ ያለ ነገር እያሰራጩ ያሉ አካላት ከድርጊታቸው ይቆጠቡ ሲል አስጠንቅቋል። በተሰራጨው የተሳሳተ መረጃ ግቢው ለቀው እየወጡ ያሉ ተማሪዎች እንዳሉ አረጋግጠናል ብሏል ተቋሙ። የትምህርት ስርዓቱ እንደማይቋረጥ የገለፀው ዩኒቨርሲቲው ግቢውን ጥለው የሄዱ ተማሪዎችም በትምህርታቸው ላይ በሚደርስባቸው እክል ሃላፊነቱን እራሳቸው ይወስዳሉ ሲል ገልጿል።

@tikvahethiopiabot @tikvahethiopia
አልፈልግም ማለት አልፈልግም ነው!

• "አቁም" ማለት አልፈልግም ነው!
• "መሸሽ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "እምቢ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "መግፋት/መገፍተር" ማለት አልፈልግም ነው!
• "ዝግጁ አይደለሁም" ማለት አልፈልግም ነው!
• "ተወኝ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "ዞር በል" ማለት አልፈልግም ነው!
• "መጮህ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "እረፍ" ማለት አልፈልግም ነው!
• "ማልቀስ" ማለት አልፈልግም ነው!

የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ያንቺ ንቅናቄ ( Yanchi movement ) ለሶስት ቀን በሚቆየው የሴት ልጅ ጥቃትን በመቃወም የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጅተዋል፡፡ ዝግጅቱ ትላንት የተጀመረ ሲሆን በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው የ16 ቀን ንቅናቄ አንድ አካል እንዲሆን ታስቦ የተዘጋጀ እንደሆነ አዘጋጆቹ ገልጸውልናል፡፡ በዚህ ንቅናቄ በዩኒቨርሲቲው የሚገኙ ሌሎች ክበባትም ተሳታፊ ሆነዋል፡፡

በሌላ በኩል በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሚገኘው "መራሂት ክበብ" አትኩሮቱን ሴት ተማሪዎችን በማብቃት ላይ አድርጎ እየሰራ ሲሆን ለሴት ተማሪዎች የፅዳት መጠበቂያ የሚሆን 88 ካርቶን ሞዴስ በመግዛት ለሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሴቶች ህፃናት ወጣቶች እና ኤችአይቪ ኤድስ ዳይሬክትቶሬት አስረክበዋል። የመጀመሪያውን ድጋፋቸውንም የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ቅርንጫፍ በሆነው በአዋዳ ካምፓስ አድርገዋል።

- በቲክቫህ ኢትዮጵያ ስም እየሰራችሁት ላለው መልካም ስራና ለሌሎች ወጣቶች ትምህርት የሚሰጥ ተግባር ላይ በመሳተፋችሁ ያለንን አክብሮት እና ምስጋና እናቀርባለን!

#HawassaUniversity

በርቱልን!
@tikvahethiopia @tikvahethiopia
#AGIIBARIIS #HawassaUniversity

በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የተሰራ ድራማቲክ ፋንታሲ ዘውግ ያለው ፊልም ሊመረቅ መሆኑን ሰምተናል፡፡ አግባሪስ ከተለመደው የሰው ልጅ አኗኗር መስመር ገለልተኛ የሆኑ ነገሮችን ይቃኛልም ተብሏል። የምረቃት ዝግጅቱ ቅዳሜ 8:00 ሰዓት ላይ የተለያዩ ጥበብ ተኮር ዝግጅቶች ፉሽን ሾው እና ስነ–ፁሁፍ ዝግጅቶችን ጨምሮ ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በአዲሱ ሀዋሳ ሌዊ ሲኒማ ይመረቃል።

(በኩሉ ኢቨንት)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#HawassaUniversity

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በ2012 ዓ/ም ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች ነሐሴ 23 በVirtual Graduation Ceremony ያስመርቃል።

ተመራቂ ተማሪዎች የምረቃት ፕሮግራሙን በቤታቸው ሆነው በዩኒቨርሲቲው ይፋዊ ፌስቡክ (FaceBook) ገፅ በቀጥታ መከታተል እንደሚችሉ ተገልጿል።

ዩኒቨርሲቲው በላከልን መረጃ መሰረት ነሃሴ 23/2012 ዓ/ም የሚመረቁት 4,800 (አራት ሺህ ስምንት መቶ) ተማሪዎች ናቸው።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#HawassaUniversity

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በCOVID-19 ቫይረስ ወረርሺን ምክንያት የተቋረጠውን የ2012 ዓ.ም የሁለተኛ ሴሚስተር ት/ት ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ማጠቃለያ ውይይት ማካሄዱን ገልጾልናል።

በዩኒቨርሲቲው ባሉ ሁሉም ኮሌጆች የተቋረጠውን ትምህርት ማስቀጠልን በተመለከተ ፦

• ከመግበያ በሮች ጀምሮ በማደሪያ ክፍሎች፤
• በቤተመፃህፍት፤
• ቤተ ሙከራዎች እንዲሁም በካፍቴሪያዎች የተዘጋጀውን የCOVID19 መመሪያ በመከተል አገልግሎት ለመስጠት ዝግጅት የማድረግ ስራው በአብዛኛው ተጠናቋል።

በቀሩት ጥቂት ቀናት ደግሞ የተቀሩትን የዝግጅት ስራዎች በማጠናቀቅ ተማሪዎችን በታቀደው መርሀግብር መቀበል እንደሚቻል ውሳኔ ላይ ተደርሷል፡፡

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ነገ ተማሪዎቹን ያስመርቃል። ዩኒቨርሲቲው ነገ 6,263 ተማሪዎችን እንደሚያስመርቅ የዩኒቨርሲቲው የውጭ ግንኙነት እና ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ወ/ሮ አርማዬ አሰፋ አሳውቀውናል። ከተመራቂዎቹ መካከል 4,119 ወንዶች ሲሆኑ 2,144 ሴቶች ናቸው። • 5,135 - በመደበኛ • 624 - በማታ • 394 - በሳምንት መጨረሻ • 110 - በክረምት መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።…
#HawassaUniversity

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን እያስመረቀ ይገኛል።

ዩኒቨርሲቲው 6,263 ተማሪዎችን ነው እያስመረቀ የሚገኘው።

ከተመራቂዎቹ መካከል 4,119 ወንዶች ሲሆኑ 2,144 ሴቶች ናቸው።

ተመራቂዎች፣ የተመራቂ ቤተሰቦች፣ የሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ፣ የክብር እንግዶች የስነ ስርዓቱ ተሳታፊ ናቸው።

PHOTO : SRTA
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#HawassaUniversity

ዛሬ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ 270 የህክምና ዶክተሮችን አስመርቋል።

ከተመራቂዎቹ መካከል 48ቱ በተለያዩ የህክምና ስፔሻሊቲ ፕሮግራም የሰለጠኑ ናቸው።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ ዶክተሮችን ሲያስመርቅ የዛሬው ለ12ኛ ጊዜ ነው።

በሌላ በኩል ፦ ከ12ኛ ዙር ተመራቂዎች መካከል ዶክተር ዮናስ ንጉሴ 3 ነጥብ 87 ውጤት በማምጣት የወርቅ ሜዳሊያ ተሻላሚ መሆን ችሏል።

በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የህክምና ትምህርት ክፍል እስካሁን ከተመዘገቡ ውጤቶች ውስጥ ከፍተኛው በመሆንም ክብረወሰን ሆኖ ተመዝግቧል።

ምንጭ፦ SRTA
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBOT
* Congratulations !

በዛሬው ዕለት ብቻ ከተለያዩት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ከ30,192 በላይ ተማሪዎች ተመርቀዋል።

የትኞቹ ዩኒቨርሲቲዎች ምን ያህል ተማሪ ? በምን ደረጃ እና የትምህርት ዘረፍ አስመረቁ ? ለጥያቄዎቹ መልስ ይህን አጭር ቁጥራዊ መረጃ አስቀምጠናል።

#HawassaUniversity

- አጠቃላይ 6 ሺህ 793 ተማሪዎችን አስመርቋል።
- ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 2 ሺህ 158ቱ ወይም 32 በመቶ ሴቶች ናቸው።
- ተመራቂዎቹ በመጀመሪያ፣ በ2ኛ እና በ3ኛ ዲግሪ በመደበኛና ተከታታይ መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

#BahirdarUniversity

- አጠቃላይ 5 ሺህ 586 ተማሪዎች አስመርቋል።
- ከተመራቂዎቹ 1 ሺህ 714ቱ ሴቶች ናቸው።
- በመጀመሪያ፣ በ2ኛ እና በ3ኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናሰቁ ናቸው።

#JimmaUniversity

- አጠቃላይ 696 ተማሪዎች አሰመርቋል።
- 450 ወንድ እና 246 ሴት ተማሪዎች ናቸው።
- በቅድመ ምረቃና በድህረ ምረቃ መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።
- ከተመራቂዎቹ 252 ተማሪዎች በአጠቃላይ ሕክምናና በጥርስ ሕክምና የሰለጠኑ ናቸው።
- ጅማ ዩኒቨርሲቲ በሶማሊላንድ ሀርጌሳ ካምፓሱ በ 'ኒውትሬሽን' የትምህርት ዘርፍ ያስተማራቸውን 19 የ2ኛ ዲግሪ ተማሪዎችንም አስመርቋል።

#AdamaScience_and_TechnologyUniversity (ASTU)

- አጠቃላይ 1 ሺህ 298 ተማሪዎች አስመርቋል።
- ሰባቱ በሦሥተኛ ዲግሪ (ፒኤችዲ) ተመራቂዎች ናቸው።
- 215ቱ በሁለተኛ ዲግሪ የተመረቁ ናቸው።
- 1 ሺህ 76 ተማሪዎች በመጀመረያ ዲግሪ የተመረቁ ናቸው።

#MettuUniversity

- አጠቃላይ 2 ሺህ 262 ተማሪዎች አስመርቋል።
- 116ቱ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።
- ተመራቂዎቹ በመደበኛ እና በተከታታይ መርሃ ግብሮች በመቱ እና በበደሌ ካምፓሶች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።

#ArsiUniversity

- አጠቃላይ 831 ተማሪዎችን አስመርቋል።
- በበቆጂ ካምፓስ የሰለጠኑ ናቸው።
- ተመራቂዎቹ በማህበራዊ ሳይንስ ዘርፍ በመደበኛና በተከታታይ መርሃ ግብሮች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።
- በመጀመሪያ እና በ2ኛ ዲግሪ ከተመረቁት መካከል 392ቱ ሴቶች ናቸው።

#AmboUniversity

- አጠቃላይ 4 ሺህ 524 ተማሪዎች አስመርቋል።
- በመጀመሪያ እና በሁለተኛ ዲግሪ የሰለጠኑ ናቸው።
- ከተመራቂዎቹ 1 ሺህ 980ዎቹ ሴት ተማሪዎች ናቸው።
- ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 450 የሚሆኑት የሁለተኛ ዲግሪ ተመራቂ ሲሆኑ 11 የደቡብ ሱዳን ስደተኛ ተማሪዎች ይገኙበታል።

#JigjigaUniversity

- አጠቃላይ 1 ሺህ 202 ተማሪዎችን አስመርቋል።
- ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 336ቱ ሴት ተማሪዎች ናቸው።
- 233ቱ በሁለተኛ ዲግሪ ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ሲሆን ቀሪዎቹ 969ኙ በመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።

* ከግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መካከል #AdmasUniversity

- አጠቃላይ ከ10 ሺህ በላይ ተማሪዎችን አስመርቋል።
- ከተመራቂዎቹ 67 በመቶ ሴቶች ናቸው።
- በቴክኒክና ሙያ፣ በመጀመሪያ ዲግሪ እና 2ኛ ድግሪ በቀንና በማታ ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።
- ከተመራቂዎቹ መካከል 1 ሺህ 532ቱ በ2ኛ ዲግሪ የተመረቁ ናቸው።

የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጉዳዮችን በ @tikvahuniversity ተከታተሉ።

@tikvahethiopia
#HawassaUniversity

ዛሬ ጠዋት መስከረም 30 ቀን 2015 ዓ/ም በሀዋሳ ዩኒቨርስቲ የሚፈተኑ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች የዩኒቨርስቲዉን ሁለት ካምፓሶች የሚያገናኝ ድልድይ በመፍረሱ ምክንያት ድልድዩን ሲሻገሩ በነበሩ የተወሰኑ ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

ሚኒስቴሩ በደረሰው ጉዳት አዝናለሁ ብሏል።

ጉዳት የደረሰባቸው ተማሪዎች በሀዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸዉ እንደሚገኝ ሚኒስቴሩ ገልጿል።

" ሁኔታቸዉን መላዉ የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ እና የትምህርት ሚኒስቴር ግብረሀይል በቅርበት እየተከታተለ " ነው ያለው ትምህርት ሚኒስቴር " ወላጆች እንዳይደናገጡ እንጠይቃለን " ብሏል።

ጉዳት የደረሰባቸዉ ተማሪዎች በቀጣይ በሚሰጠዉ ፈተና የሚፈተኑ መሆኑን የገለፀው ሚኒስቴሩ ሌሎች ተማሪዎች በአጋጣሚዉ ሳይረበሹ ተረጋግተዉ እንዲፈተኑ አሳስቧል።

ሁኔታዉን በሚመለከት ዝርዝር መረጃዎችን በቀጣይ እንደሚያሳውቅም የትምህርት ሚኒስቴር ገልጿል።

ፎቶ ፦ክብሩ ግዛቸው

@tikvahethiopia
#HawassaUniversity

ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በከፍተኛ ሁኔታ በዝርፊያ እየተፈተነ ይገኛል።

አላግባብ ለእስር ታዳረግን ያሉ ሰራተኞችም ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ አቅርበዋል።

ለአመታት በሚሰጠዉ ትምህርትና ለማህበረሰቡ በሚያደርገዉ ድጋፍ  የሚታወቀዉ የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ በዝርፊያ ምክኒያት አየተፈተነ ነዉ።

አሁን ላይ ዩኒቨርሲቲዉ ከኮምፒዉተር እስከ ቀላልና ከባድ ማሽኖች ከመንገድ ላይ መብራት እስከ ግድግዳ ላይ የተገጠሙ ሶኬቶች ሳይቀር አየተዘረፈበት ሲሆን ዳፋዉ የደረሳቸዉ ተማሪዎችም ዘግተዉት የወጡት በር እየተሰበረ ከአልባሳት እስከ ኤሌክትሮኒክስ ከመማሪያ ቁስ እስከ መመረቂያ ሱፍ መዘረፋቸውን ይጠቁማሉ።

ችግሩን ዉስብስብ ያደረገዉ ደግሞ ዝርፊያዉን ለመመርመር የሚመጡት የህግ አካላት በተደጋጋሚ የግቢዉን ሰራተኞች ማሰራቸዉ እንደሆነ ቅሬታች አቅራቢዎች ገልጸዋል።

ከዚህዉ ጋር በተያያዘ በቅርቡ ለእስር መዳረጉን የገለጸልን የዩኒቨርስቲው መምህር በስሙ የነበሩ ኮምፒዉተሮች ተሰርቀዉ ማደራቸዉን ተከትሎ ለዘጠኝ ቀናት ለእስር መዳረጉን ይገልጻል።

መምህሩ እንደሚገልጸዉ " ስንት ጥበቃ ባለበት ግቢ ዉስጥ እቃ ተሸክሜ መዉጣት እንደማልችል እየታወቀ የተያዝኩበት መንገድ አሳፋሪና አግባብነት የጎደለዉ ነበር " ሲል ያስታዉሳል።

ሌላኛዉ ከዝርፊያ ጋር በተያያዘ ለሁለት ቀናት እስር መዳረጉን  የገለጸልን መምህር ደግሞ መምህራኑ የሚታሰሩት ሌሊት ተሰርቆ በሚያድር እቃ መሆኑን ገልፆ ጉዳዩ ተጣርቶ ከእስር ከተለቀቁ በኋላ ፋይላቸዉን ለመዝጋት የሚወስደዉ ጊዜ ከብዙ ጉዳይ እንደሚያስቀራቸዉና  ለእንግልት እየዳረጋቸዉ መሆኑን ያነሳል።

ከዚህዉ ጋር በተያያዘ አስተያየታቸውን ለቲኪቫህ ኢትዮጵያ የሰጡት የሀዋሳ ዩኒቨርስቲ  ምክትል ፕሬዚዳንት ዶር ሳሙኤል ጅሎ እንደሚገልጹት መምህራን ለእስር የሚዳረጉበት ምክኒያት ቢሯቸዉ በቁልፍ ተከፍቶ እቃዉ ጠፍቶ መገኘቱን ተከትሎ የምርመራ ትኩረት እነሱ ላይ የሚያነጣጥር በመሆኑ ነው በማለት ገልጸዋል ።

ዶ/ር ሳሙኤል አክለዉም መምህራን በሚያዙበት ወቅት በአግባቡና በክብር እንዲሆን የጸጥታ አካላትን እያነጋገሩ መሆናቸዉን ገልጸዉ ምርመራዎች በአጭር ጊዜ ዉስጥ እንዲያልቅና ፋይላቸዉ አንዲዘጋም ጥረት እንደሚያደርጉ አመላክተዋል።

በግቢዉ ዉስጥ የሚስተዋለዉን ዝርፊያ ለመቆጣጠር አሁን ላይ የጥበቃ አሰራሩን አዉትሶርስ ለማድረግ ጨረታ ላይ መሆናቸዉን የሚገልጹት ዶክተር ሳሙኤል አዉትሶርስ በማይደረጉ ክፍሎችም የጥበቃ ቁጥር ለመጨመር መታሰቡን ገልጸዋል።

ከዚህ በተጨማሪ አሁን ላይ ዩኒቨርስቲው ችግሩን ለመቅረፍ አንዳንድ ህንጻዎችን የስማርት ሴኪዉሪቲ ሲስተም መጠቀም መጀመሩን ተከትሎ ለዉጦች ቢኖሩም የስማርት ሲስተሞች የራሳቸዉ ክፍተት መኖርና የችግሩ ስር መስደድ ግን ሁኔታዉን ከባድ ሆኖ ይቀጥል ዘንድ ምክንያት ሆኗል።

@tikvahethiopia
#HawassaUniversity

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ አገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መውጫና የሙያ ፈቃድ ፈተና ከወሰዱት የህክምናና ጤና ሳይንስ ተመራቂ ተማሪዎቹ 99% ተፈታኞች ፈተናውን አልፈው ለመመረቅ ብቁ መሆናቸውን አሳውቋል።

ተቋሙ ይፋ ባደረገው ዳታ ፤ በ ' ዶክተር ኦፍ ሜዲስን ' ካስፈተናቸው 190 ተመራቂዎች 189 ተመራቂዎች የተሰጣቸውን ፈተና አልፈዋል።

More 👉 @tikvahuniversity
#HawassaUniversity

በህክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የተለጠፈው ማስታወቂያ ምንድነው ? ዩኒቨርሲቲውስ ምን ምላሽ ሰጠ ?

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሚማሩ ተማሪዎች ቅሬታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ሲልኩ ነበር።

ለዚህ ቅሬታ መነሻቸውም አንድ ተለጥፎ ያዩት ማስታወቂያ ነው።

ማስተወቂያው ፦

° በ12ኛ ክፍል ፈተና ምክንያት ተማሪዎች ወደቤት መሄዳቸውን ይጠቁማል።

° የገበያው አለመረጋጋት አቅራቢዎች ላይ በፈጠረው ከፍተኛ ጫና እና በቀን ለ1 ተማሪ የተወሰነው 22 ብር ዕለታዊ ወጪ ጋር ተመጣጣኝ ባለመሆኑ ላልተወሰነ ጊዜ የመግቢያ ቀን መራዘሙን ያሳያል።

° ኢንተርን ሽፕ ላይ ያሉ እና ካፌ ተጠቃሚ የነበሩ እጩ ዶክተሮች በምግብ ምትክ የሚሰጠውን የነን ካፌ ፎግም ሞልተው ተጠቃሚ እንዲሆኑ ይላል።

° የተማሪዎች መግቢያ እስኪገለጽ ከቀን 29 /11/ 2016 ዓ/ም ጀምሮ የምግብ እና የመኝታ አገልግሎት ላልተወሰነ ጊዜ በመቋረጡ በተለያዩ ምክንያቶች ግቢ ያሉ ተማሪዎች በ4 ቀን ለቀው እንዲወጡ ይላል።

የተማሪዎች ቅሬታስ ምንድነው ?

መልክዕታቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የላኩ ተማሪዎች ትልቅ ቅሬታ እንዳላቸው ይገልጻሉ።

ቅሬታቸው ፦

- ላለፉት ስምንት ዓመታት ትምህርት ላይ ብንሆንም አሁንም በተለያየ መልኩ ጊዜያችን እየተቃጠለ ነው።
- የመመረቂያ ጊዜያችን አሳሳቢ ሆኗል።
- መግቢያችን ለሁለተኛ ጊዜ መራዘሙ ትክክል አይደለም።
- በኮቪድ-19 ለአስር ወራት እንዲሁም በ12ኛ ክፍል ፈተና ምክንያት የትምህርት ጊዚያችን ተቃጥሏል። ወሁን የመመረቂያ ጊዚያችን ተራዝሟል።
- በዚህ ዓመት ለ12ኛ ክፍል ፈተና እንድንወጣ ተደርገን ሐምሌ 17/2016 ዓ.ም ነው የተጠራነው። በኋላም ወደ ሐምሌ 25/2016 ዓ.ም ተገፋ። አሁን ደግሞ ላልተወሰነ ጊዜ መራዘሙን ሰማን። ይህ ትክክል አይደለም።
- የሚመለከተው አካል መፍትሔ ይስጠን።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተማሪዎች ቅሬታን እንዲሁም የተለጠፈውን ማስታወቂያ ይዞ ዩኒቨርሲቲው አለኝ የሚለውን ማብራሪያ ለተማሪ እንዲሰጥ ጠይቋል።

የሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ  ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ተባባሪ  ፕሮፌሰር አለሙ ጣሚሶ ምን አሉ ?

የቀረበዉ መረጃ ትክክል አይደለም።

ኢንተርን ሀኪሞች ከግቢ አይወጡም። ዶርማቸውንም አይለቁም። ይልቁንም ለተወሰነ ጊዜ የዩኒቨርስቲው የምግብ አገልግሎት በመቋረጡ በጀታቸዉን እንዲጠቀሙ ነው የተገለጸው።

ይህ የሆነው አሁን ላይ ለ3 አመት ውል የገቡ ነጋዴዎች በእቃ መወደድ ምክኒያት ምንም አይነት የምግብ ግብአት ሊያቀርቡልን ባለመቻላቸዉና ይህን ችግር  ተወያይተን መፍትሄ እስክንሰጠዉ ነው።

ሌሎች ተማሪዎች ቅድመ ዝግጅት ከተጠናቀቀ በቅርቡ ወደ ትምህርት ገበታቸው ይመለሳሉ። ትክክለኛ ቀኑንም  ለተማሪዎች በይፋ ይነገራቸዋል።

ተማሪዎችን አሁን ላይ መቀበል ያልተቻለው ከምግብ አቅርቦትና አንዳንድ ማስተካከያ የሚፈልጉ ጉዳዮች ስላሉ ነው።

በየጊዜዉ ለ12ኛ ክፍል ፈተና ሲባል ከግቢ መውጣታቸውን ሆነ አሁን ላይ በቶሎ አለመግባታቸው የሚወስድባቸውን ጊዜ  ለማካካስ ዩኒቨርሲቲው መፍትሄዎችን አስቀምጧል። በዛ ይሄዳል።

ተማሪውን የሚያደናግር ማስታወቂያ ያወጣዉ አካል ከኛ እውቅና ዉጭ በመሆኑ ማንነቱን አጣርተን እርምጃ የምንወስድ ይሆናል።

በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ሳይንስ ተማሪዎች ህብረት ፕሬዝደንቱ ተማሪ ደረጀ መንገሻ ምን አለ ?

👉 ኢንተርን ዶክተሮች ከግቢ ባለመውጣታቸዉ እስካሁን መጉላላት አልደረሰባቸውም። ማስታወቂያውም ያለኛ እውቅና ነው የተለጠፈው።

👉 ተማሪውን ሳይፈልግ ወደነን ካፌ መቀየር አግባብ ስላልሆነ ለዩኒቨርሲቲዉ አመራሮች ውሳኔዉ ልክ አለመሆኑን የሚገልጽ ደብዳቤ አስገብተን ምላሽ እየጠበቅን ነው።

👉 ተማሪዎች ሐምሌ 25 ቀን 2016 ዓ/ም ያልገቡበት ምክኒያት ዩኒቨርሲቲዉ ከበጀት ማስተካከያና ካምፓስ ውስጥ ከሚያስተካክላቸው አንዳንድ ነገሮች ጋር በተያያዘ ምክኒያት ነው።

👉 ተማሪዎች በጊዜ ወደ ግቢ ባለመግባታቸው በቀጣይ ተማሪዎች ላይ የሚከሰተዉን ጫና በተመለከተ ዩኒቨርሲቲው እንዲያስብበት ተነጋግረናል።

#TikvahEthiopiaFamilyHW

More - @tikvahuniversity

@tikvahethiopia